• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንገዳችን በፍጥነት ይቃና!

September 30, 2018 02:02 am by Editor Leave a Comment

በብዙ ዓይነት ወንጀሎች የሚታሙት የወያኔ አዛዦች ሥልጣናቸውን እንደያዙ ከሥልጣን ወረዱ ቢባል ግራ ይሆናል፤ ነገር ግን ሆነ! በሕጋዊ ምርመራ ሳይጣራና ከሳሾቹን በፍርድ ቤት ሳይሞግት የሰው ልጅ እንደከብት ከመንገድ በጉልበተኞች እየተያዘ መታሰር የቀረ መስሎን ነበር፤ አልቀረም አሉ! ጉልበተኞች በወንጀላቸው ክብደት ከሕግ ይከለላሉ ይባል ነበር፤ አሁንም ያው ይመስላል! ያነበብሁትን በትክክል ካስታወስሁት በጥንታውያን ግሪኮች ሰርቀው መያዝ እንጂ መስረቅ ወንጀል አልነበረም (የምታስታውሱ አርሙት)፤ የምንመሳሰለው በጥንታዊነት ብቻ መስሎኝ ነበር!

ከዚህ ቀደም ጸጋዬ ገብረ መድኅን (ይመስለኛል) ተረግመናል ብሎ፤ ነበር፤ እኔንም መሰለኝ! ኢትዮጵያውያን መልካቸውን፣ ነብሮች ቆዳቸውን እንዴት ይለውጣሉ ያለው መልካችንን ነበር፣ ወይስ ጠባያችንን ማለቱ ነበር!

ነገሬ ሁሉ የጥንቶቹን አባትና እናት ይህንን የተሸከምነውን ጉድና ነውር ጫኑብን ለማለት እንዳመስላችሁ፤ እነሱ ሊጭኑብን የፈለጉት ክብርንና ኩራትን ነበር፤ ነገር ግን አህያ ወላጆቻችንን እያገለገለች ዱላን የመቻል ትእግስትዋና በዘመናት ለከፈለችው መስዋዕትነት ክብርንና ኩራትን ስትወርስ አበሻ ‹‹አባባ እግርዎትን!›› (ከቃሊቲ የደረጀ ሀብተ ወልድ ትምህርት ቤት የተገኘ እውቀት!) እያለ መለቃቀሙን መረጠ!

የወደቀ ከማንሣት የጣሉትን ማንሣት የሚያኮራና የሚያስከብር ይመስለኛል፤ የጣሉትን ማንሣት ራስን የማረም እርምጃም ነው፤ ራስን ማረም ራስን ማቃናት ነው፡፡

ላለፉት ሦስት ወራት የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍቅር፣ በምሕረትና በይቅርታ፣ በመረዳዳትና በተስፋ ንግግሮችና በማይናቁ ድርጊቶች አንገቱን ቀና፣ ደረቱን ነፋ ማድረግ ጀምሮ ነበር፤ ለአዲስ ሥራና ለአዲስ እድገት በአዲስ መንፈስና ደበአዲስ ኃይል ታጥቆ እየተሰናዳ ነበር፤ ለማ መገርሳና ዓቢይ አህመድ የእግዚአብሔር መልእክተኞች መስለው የታዩበት ጊዜ ነበር፤ ነገር ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ ላባቸው እየረገፈ ለብዙው ሰው ከመሬት መነሣት እያቃታቸው እየመሰለ ነው፡፡

የአገሩ ችግር ውስብስብ መሆኑ እየታወቀ ብዙ ቡድኖች የበለጠ ውስብስብ እያደረጉት ነው፤ ምክንያቱ የተሰወረ አይደለም፤ የሥልጣን ሰይፍና የጠገራ ብር ቀልቀሎ ነው፤ ሁለቱንም እየተስገበገቡ በመሻማት እርስበርሳቸው ለመጠፋፋት የሚተራመሱት ከራሳቸው በላይ ነፋስ ነው!

ለማና ዓቢይ አዲሱ የፖለቲካ ፍልስፍነናቸው ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳለው ያውቃሉ፤ ሁላችንም እናውቃለን፤ ለማና ዓቢይ በስንት ወራት የሁለት ሺህ ዓመታቱን ትምህርት ሊያገባድዱ እንዳቀዱ የሚያውቁት እነሱና የላካቸው አምላክ ብቻ ነው፤ እንደጅምራቸው ከሆነ ግን ለማና ዓቢይም እንደክርስቶስ ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ሳያስፈልጋቸው አይቀርም! እግዚአብሔር አቋራጩን መንገድ ይግለጽላቸው፡፡

ሕግና ሰይፍ የባሕርይ ዝምድና አላቸው፤ ዝምድናቸውም በጣም የጠነከረ ከመሆኑ የተነሣ አንዱ በሌለበት ሌላኛውም የለም፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
መስከረም 2011

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column, prof mesfin

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule