* “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” ህወሃት ለነዋሪዎች የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በሚገዛት ትግራይ ድርቅ በአስከፊ ሁኔታ ህይወት እየቀጠፈ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ለእንስሳትም ሆነ ለሰው ዕርዳታ መስጠት ገና ባይጀመርም በሚደረገው ዕርዳታ የመስጠት ዕቅድ ውስጥ የዓረና-መድረክ አባላት የሆኑ ነዋሪዎች “ዓረና ይርዳህ” በመባል ከዕርዳታው አሠጣጥ ዕቅድ ውጪ ተደርገዋል፡፡ የህወሃት ካድሬዎች ነዋሪ ገበሬዎችን “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” በማለት መመሪያ እየሰጡ ነው፡፡ አምዶም ገብረሥላሴ በፌስቡክ ገጹ ላይ ያወጣው መረጃ እንዲህ ይነበባል፡- ድርቅ በትግራይ አስከፊ ሁኔታ ላይ በመድረሱ የቤት እንስሳ ህይወት እየቀጠፈ ነው። በትግራይ አብዛኛው ወረዳዎች የድርቅ አደጋ የተጠቁ ሲሆኑ እጅግ አስከፊ የሚባል ጉዳት ያደረሰባቸው ወረዳዎች ግን አፅቢ ወንበርታ 12 ቀበሌዎች፣ የክልተ … [Read more...] about በትግራይ ድርቅ ህይወት እየቀጠፈ ነው!
Opinions
ስለ ክህደት ምንነት ልምዴን ላካፍላችሁ
ከአመታት በፊት በምርጫ ዘጠና ሰባት አካባቢ አዋሳ ከተማ ውስጥ የገጠመኝ ነገር ትዝ ይለኛል። በአዋሳ ከተማ ቆይታየ ጊዜ ከአንድ ታዋቂ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ እሳተፍ ነበር። በዚህ ድርጅት መሳተፍ እንደጀመርኩ ብዙም ሳልቆይ የወጣቶች ጉዳይና የድርጅት ጉዳይ ሆኘ ተመደብኩ።ታዲያ በዚያ አጭር ጊዜ ቆይታየ የመንግስትን የስለላ ስራና ተፈጥሮ እንድረዳ እድል ስለሰጠኝ ያ ጊዜ አስተማሪየ ሆኖ ይሰማኛል። በውነት ለመናገር ያ የአዋሳ ቆይታየ ስለ ወያኔ ያለኝን መረዳት አራምዶት ነበር። ዛሬ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (TPDM) መሪ የነበረው ሞላ የተወሰኑ ታጋዮችን ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ገባ የሚለው ዜና ከተሰማ በሁዋላ ያ የአዋሳው ትዝታየ የኋሊት በምናብ ታወሰኝ። በተለይም የሞላ አስገዶምን ኢንተርቪው ሳይ “እኛ ከመንግስት ጋር ስንሰራ ቆይተናል። ግንኙነት ነበረን” ሲሉ … [Read more...] about ስለ ክህደት ምንነት ልምዴን ላካፍላችሁ
“የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሙስሊሙ ኅብረተሰብ ላይ በደል እየፈጸመ ነው” ተጓዦች
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚጓዙ መንገደኞችን በአሮጌው ተርሚናል በኩል በማስተናገድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜጎች በማንነታቸው ተለይተው እየተዋከቡ መሆኑን መንገደኞቹ የደረሰባቸውን በደል ዋቢ በማድረግ ምንጮች ገልጸዋል። በተለይ ከሳውዲ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ተጓዦችን በአየር መንገዱ የሚገኙ የደኅንነት ሰዎች ግልጽ ጉቦ እየጠየቁ እንደሆነ ተነገረ፡፡ በተለይ ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚጓዘው ኢትዮጵያውያዊ አብዛኛው ሙስሊም ማህበረሰብ እንደመሆኑ መጠን ጥብቅ ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚደረግባቸው የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች ዜጎች በገዛ አገራቸውና አየር መንገዳቸው እንደ ሁለተኛ ዜጋ መታየታችው የመንግስት እጅ እንዳለበት አመላካች መሆኑን ይጠቁማሉ። በአሮጌው ተርሚናል የሚስተናገድ እነዚህ የአየር መንገዱ ተገልገላይ ኢትዮጵያውያን ደምበኞች ይዘውት በሚወጡትና … [Read more...] about “የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሙስሊሙ ኅብረተሰብ ላይ በደል እየፈጸመ ነው” ተጓዦች
በመተማ ከተማ “በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች” በሚል የሕወሃት/ብአዴን ታጣቂዎች 2 ነዋሪዎችን ገደሉ፣ ከ50 በላይ አቆሰሉ
የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ሕወሃት) የፈጠረው የብአዴን ታጣቂዎች በመተማ ከተማ "በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች" በሚል ሁለት ነዋሪዎችን መግደላቸው፣ ሶስት ለሞት የሚያደርስ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሳቸው እንዲሁም ከሃምሳ በላይ ማቁሰላቸው ተሰማ። የብአዴን አባላት እና መሪዎች የዐማራን ሕዝብ እያሰቃዩ እና እያስፈጁ የሚያካብቱት ማንኛውም ሃብት በክህደትና በግፍ የተሰበሰበ በመሆኑ ለህዝብ የሚያስረክቡበት ግዜ ሩቅ አይደለም። ለዚህ የክህደት ተግባራችው ተገቢውን ቅጣት ያገኛሉ፣ በባህርዳር እና በጎንደር በሰፊው እየተሳሳቡ አገር እየዘረፋ መሆኑን እያንዳንዷንም ተግባራቸውንም እየተከታተልን ዝርዝር ይፋ እናደርጋለን። እነኝህ ስግብግቦች በሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ፣ በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች ናቸው ያሏቸውን ቤቶች ለማፍረስ በሚሞክሩበት ጊዜ፣ ከነዋሪው በተነሳዉ ተቃዉሞ … [Read more...] about በመተማ ከተማ “በሕግ ወጥ መንገድ የተሰሩ ቤቶች” በሚል የሕወሃት/ብአዴን ታጣቂዎች 2 ነዋሪዎችን ገደሉ፣ ከ50 በላይ አቆሰሉ
OPEN LETTER OF APPEAL TO POPE FRANCIS I REGARDING JUSTICE FOR ETHIOPIA
Your Holiness, The Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause presents its compliments, in our most humble and respectful manner, to Your Holiness and submits this petition for a formal Vatican apology to the Ethiopian people for its complicity with Fascist Italy in the war crimes perpetrated in Ethiopia by the Italian regime then led by Benito Mussolini during 1935-41. We take this opportunity to express our joy and sincere appreciation of Your Holiness’ formal apology to the people of … [Read more...] about OPEN LETTER OF APPEAL TO POPE FRANCIS I REGARDING JUSTICE FOR ETHIOPIA
ችግሩ ወያኔን በማስወገድ ብቻ የሚፈታ አይደለም!!
መግቢያ በየጊዜው ለመጻፍ ብዕሬን በመቃጣት ላይ እያለሁ እመለሳለሁ። ይህንን የማደርግበት ምክንያት በእንግሊዘኛም ሆነ በአማርኛ በየድህረ-ገጾች ላይ ተጽፈው ለንባብ የሚቀርቡ ጽሁፎች ስለማያረኩኝ ነው። ይህንን የምልበት ምክንያት እኔ ብቻ በትክክል የምጽፍ ሆኖ ስለሚሰማኝ ሳይሆን የጽሁፎቹን ዓላማ ለማወቅም ሆነ ለመረዳት ስለሚያስቸግረኝ ነው። ሁለተኛ፣ አብዛኛዎች ጽሁፎች በተወሰነ ሃሳብ ላይ ያተኮሩና በዚያው ላይ የሚሽከረከሩ አይደሉም። በሌላ አነጋገር እንድንወያይበትና እንድንከራከርበት በር የሚከፍቱ አይደሉም። ሁሉም እንደፈለገውና እንደመሰለው የሚጽፍ እንጂ ከተጨባጭ ሁኔታዎችና ከህሊና ሁኔታ በመነሳት ችግራችንን የሚተነትን አይደለም። በሶስተኛ ደረጃ፣ በአንዳንድ ድህረ-ገጾች ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በአንድ ግለሰብ ሃሳብና ርዕይ ላይ ያተኮሩ ሳይሆኑ፣ የግለሰብን ስም የሚያጎድፉ ወይም ሞራሉ … [Read more...] about ችግሩ ወያኔን በማስወገድ ብቻ የሚፈታ አይደለም!!
ጥቂት ስለ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ
ተግባቢና በሳል ነው፤ ረጋ ባለ አንደበቱ የሚሰማውን በጥሞና መናገር ልዩ ያደርገዋል ፡፡ እምነቱን አጥበቆ ይወዳል፤ የእስልምና ሃይማኖት የሚያዛቸውን ተግባራት (ሶላት መስገድ፣ መጾም…) ፈጽሞ ሌሎች መሰሎቹ እንዲፈጽሙ ማድረግን ያውቅበታል፡፡ ከሌሎች የእምነት ተከታዮች ጋር የመግባባቱና ከሁሉም ጋር በአብሮነት መኖሩ ባጠቃላይ ማህበራዊ ኑሮ የሚጠይቀውን ግዴታ የመወጣት ልዩ ችሎታ አለው፡፡ ከማንም ሰው ጋር የመግባባት፣ ተጫውቶ የማጫወት ክህሎት አለው፡፡ ከቀለሙ በተጓዳኝ ሀይማኖታዊ እውቀቱም የተመሰከረለት ነው፡፡ ሙስሊም ተማሪዎችን በመሰብሰብ በስነ ምግባር እንዲታነጹና ለሀገራቸው ተቆርቋሪ እንዲሆኑ ያስተምራል፡፡ በግቢው ውሰጥ ተሰሚነት ካላቸው የሀይማኖት ሰዎች አንዱ ነበር፡፡ ካሚል ሽምሱን መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ሳለ አውቀው ነበር፤ አንድ ባችም ነበርን፤ በህግ ፋከልቲ ተደልድለን ለአምስት … [Read more...] about ጥቂት ስለ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ
አዲስ ዓመት ያለ ተስፋ!?
የተወደዳችሁ የአገራችን የሃይማኖት መሪዎች እንዲሁም የየእምነቱ ምዕመናን፡- ይህንን መልዕክት የምጽፍላችሁ ወንድማችሁ ይህንን ጥሪ የማቀርብላችሁ እንደ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር ለእናንተ ሃሳቤን ለማቅረብና እንደ እምነቴ ደግሞ በጌታችን የሱስ ክርስቶስ ባለኝ እምነትም ጭምር ነው። ይህንን ስል ሌሎች እንደ እኔ ዓይነት እምነት የሌላችሁን የሃይማኖት መሪዎችና ተከታዮች ያገለልኩ መስሎ እንዲሰማችሁ ወይም ከእኔ ጋር ተመሳሳይ እምነት በሌላችሁ ላይ ጫና ለማድረስ በጭራሽ ምኞቴ እንዳልሆነ አስቀድማችሁ እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ። የራሴን መግለጼ እንደ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር እና እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ማንነቴን አሳውቄ ሃሳቤንም በዚያው መልኩ እንድትረዱልኝ ከማድረግ አኳያ ነው። ኢትዮጵያ በምንላት አገራችን ሁላችንም የተለያየ ሃይማኖት እንከተላለን፤ እንደየ እምነታችንም የአምልኮ ሥርዓታችንን … [Read more...] about አዲስ ዓመት ያለ ተስፋ!?
“ታማኝ ካድሬዎችና አባላት በህወሃት ስብሰባ ላይ ተቃውሞ አሰሙ”
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በመቀሌ ከተማ ባደረገው ስብሰባ ላይ በጥንቃቄ ተመርጠው የተጠሩ ታማኝ ካድሬዎችና አባላት የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ የትግራይ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በአባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት አንጃ አሳወቀ። አንጃው ይህንን አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀው “12ተኛ ጉባኤ እንዴት አለፈ …?" በሚል አጀንዳ በየመንግሥት መስርያ ቤቶች፣ ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች፣ የክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ካድሬዎችና ነዋሪዎች ውይይት በተካሄደበት ጊዜ ነው። በመቀሌ ማዘጋጃ ቤት ማክሰኞ 3/13/2007 ዓም በአቶ ተስፋአለም ተወልደብርሃን (የመቀሌ ከንቲባ)፣ አቶ አሰፋ ተገኝ ምክትል ከንቲባ የተመራ ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን “የህወሓት ጉባኤ ምን ይመስላል?” የሚል አጀንዳ ተሰጥቶት ነበር። የትግራዩ አንጃ በጉባኤው ወቅት … [Read more...] about “ታማኝ ካድሬዎችና አባላት በህወሃት ስብሰባ ላይ ተቃውሞ አሰሙ”
ጀርመን አገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኮፐቲክ ቤተክርስቲያን የጋራ ሲኖዶስ አቋቋሙ!
በጀርመን የኦርየንታል (የመካከለኛው ምስራቅ) ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያናት አንድ የጋራ ሲኖዶስ ለመመስረት ስለፈለጉ፤ ትላንት የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያውን እርምጃ ወስደዋል። በዚህም መሰረት ጳጳስ አንባ ዳሚያን (የኮፐት ኦርቶዶክስ) እና ሊቀጳጳስ ሙሴ (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ) ውል ተፈራርመዋል። በኮፕት ገዳም የውል ሰነድ ፊርማ፤ ሊቀጳጳስ ሙሴ (2. ከገራ ወደቀኝ) እና ጳጳስ አንባ ዳሚያን (የመካከለኛው ) (ከመሃል) ፊረማቸውን በውሉ ሰነድ ላይ አስቀመጡ። በዚሁ ጊዜ በቦታው የነበሩ፤ አባ ዳዊት ሙሳ ከግብጽ እንዲሁም የገዳሙ ጎብኝ እንግዶች/ካቶሊኮች/ ሞሲኞር ፔተር ፎን ሸታይኒትጽ (ከግራ) እና ዲያቆን ክርስቶፍ ፐሪንስ ቤተልሄም (ከቀኝ) እንዲሁም ሚዛን ገብሩ (ሁዋላ ከግራ) ማግዳሌና ግርማ፤ ሳራ ኪዳኔ እና ሞገስ ተሾመ … [Read more...] about ጀርመን አገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኮፐቲክ ቤተክርስቲያን የጋራ ሲኖዶስ አቋቋሙ!










