• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ ድርቅ ህይወት እየቀጠፈ ነው!

September 23, 2015 09:43 pm by Editor Leave a Comment

* “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” ህወሃት ለነዋሪዎች

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በሚገዛት ትግራይ ድርቅ በአስከፊ ሁኔታ ህይወት እየቀጠፈ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ለእንስሳትም ሆነ ለሰው ዕርዳታ መስጠት ገና ባይጀመርም በሚደረገው ዕርዳታ የመስጠት ዕቅድ ውስጥ የዓረና-መድረክ አባላት የሆኑ ነዋሪዎች “ዓረና ይርዳህ” በመባል ከዕርዳታው አሠጣጥ ዕቅድ ውጪ ተደርገዋል፡፡ የህወሃት ካድሬዎች ነዋሪ ገበሬዎችን “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” በማለት መመሪያ እየሰጡ ነው፡፡ አምዶም ገብረሥላሴ በፌስቡክ ገጹ ላይ ያወጣው መረጃ እንዲህ ይነበባል፡-

ድርቅ በትግራይ አስከፊ ሁኔታ ላይ በመድረሱ የቤት እንስሳ ህይወት እየቀጠፈ ነው። በትግራይ አብዛኛው ወረዳዎች የድርቅ አደጋ የተጠቁ ሲሆኑ እጅግ አስከፊ የሚባል ጉዳት ያደረሰባቸው ወረዳዎች ግን አፅቢ ወንበርታ 12 ቀበሌዎች፣ የክልተ አውላዕሎ በርካታ ቀበሌዎች፣ አብዛኛው ራያ ዓዘቦና ራያ አለማጣ ቀበሌዎች፣ የኦፍላ ግማሽ ቀበሌዎች፣ አብዛኛው ሕንጣሎ ወጀራት፣ ከግማሽ በላይ ሳምረ ሰሓርቲ፣ አብዛኛው ጣንቋ አበርገለ ወረዳ፣ የምዕራባዊ ዞን የርካታ ቀበሌዎች ናቸው።

በተጠቀሱት ወረዳዎች በድርቁ ምክንያት የእንስሳት ምግብ እጥረት አጋጥሞ በርካታ የቤት እንስሳት ለሞት ተዳርገዋል።

የትግራይ ክልል መስተዳድር ምንም ዓይነት የህይወት አድን ስራ መስራት አልቻለም። በጣም የሚያሳዝነው (አገዛዙ) ሃላፊነቱን በመዘንጋት በድርቅ ለተጠቁ አካባቢ ነዋሪ ገበሬዎች “በድርቁ ምክንያት ከብቶቻችሁን ሸጣቹችሁ ተገላገሉ” የሚል መመሪያ መስጠቱ ነው።

በጣም የሚገርመው እስካሁን ለእንስሳም ይሁን ለሰው እርዳታ ማቅረብ ያልተጀመረ ሲሆን በድርቅ የተጠቁ ቀበሌዎች ነዋሪ የሆኑት የዓረና አባላት ከጥናቱ ውጭ እያደረጓቸው ይገኛሉ።

ለምሳሌ በኦፍላ ወረዳ ዓረና-መድረክን ወክሎ ለክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ የነበረው አቶ ጡዕማይ ስዩም “ዓረና ይርዳህ” በማለት ከእርዳታው ውጭ በማድረግ ከነፍስ ማጥፋት የማይተናነስ ወንጀል እየፈፀሙ ይገኛሉ።

ከድርቅ አደጋ በተጨማሪ በርካታ ቀበሌዎች በበረዶና በጎርፍ አደጋ ሰብላቸው ከጥቅም ውጭ ሆኖባቸዋል። የህወሓት አገዛዝ ለእነዚህ ተጎጂዎች “እርዳታ ስጡኝ” ብሎ ለልመና ለዓለም ማህበረሰብ እጁ ዘርግቷል።

ይሁን እንጂ አስቸኳይ እርዳታው ለፖለቲካዊ ጥቅሙ እያዋለው ይገኛል። የዚህ ወንጀል ሰለባ ከሆኑት በዓብይ ዓዲ-ሃገረሰላም ምርጫ ክልል የዓረና-መድረክ የክልል ምክርቤት እጩ ተወዳዳሪ የነበሩት አቶ ኪሮስ ታደስ እንደሌሎች የደጉዓ ተምቤን ወረዳ ደጎል ወያነ ቀበሌ ነዋሪዎች ሰብላቸው በበረዶ ከጥቅም ውጭ የሆነባቸው ሲሆኑ ለዚህ ጉዳት ለመከላከል ጥናት የሚያደርጉ የወረዳው ሹመኞች የቀበሌው ህዝብ እንደተሰበሰበ “ዓረና ይርዳህ” ተብለው ከነቤተሰባቸው ከሞት የማይተናነስ ፖለቲካዊ ውሳኔ ተወስኖባቸዋል።

ይህ ስራ በ1977 አስከፊው ድርቅ ወቅት በትግራይ ህዝብ ላይ ሻእብያ የወሰደው አስነዋሪ ውሳኔ በህወሓት እየተደገመ መሆኑ የሚያመላክት ነው።

የትግራይ ክልል መንግስት በድርቅ ለተጠቁ አከባቢዎች የውሃና ሳር ድጋፍ እስካሁን አላደረገምና እየጠፋ ያለው የእንስሳ ህይወትና በጠኔና ረሃብ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ እያለ ያለው ህዝብ አስቸኳይ እርዳታ ማድረግ ይገባዋል።

ከኦሮምያና ዓፋር ክልሎች ተሞክሮ እንዲወስድም እንጠይቃለን።

ነፃነታችን በእጃችን ነው…!

IT IS SO…!

(ፎቶ፡ ከቀድሞው ድርቅ ለማሳያነት የቀረበ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule