የኢትዮጵያ አርበኞች ቀን ሚያዚያ 27፤2009 የተከበረበትን ዕለት ምክንያት በማድረግ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በዕለቱ (May 5, 2017) “የኢትዮጵያ አርበኞች ውለታና የባንዳዎች ዕዳ!” በሚል ርዕስ አንድ ጽሁፍ ለኅትመት አቅርቦ ነበር፡፡ የጽሁፉ ዓላማ በዚህ መልኩ ቀርቦ ነበር፤ “በየዓመቱ ሚያዝያ 27 የሚከበረው የድል ቀን በኢትዮጵያ የቀን መቁጣሪያ (ካሌንደር) ላይ ሥራ ተዘግቶ እንዲከበር ቢደረግም ትውልዱ የቀደሙ እናትና አባቶቹን የተጋድሎ ታሪክ እንዲያወቅ የሚያስችል የበዓል አከባበር አይታይም፡፡ ዕለቱም እንደአንድ ተራ የረፍት ቀን ያልፋል፡፡ በአንጻሩ አንዳች አገራዊ ፋይዳ የሌላቸው የህወሃት፣ የብአዴን፣ የኦህዴድ፣ … የምሥረታ ቀን እየተባለ በብዙ ሚሊዮን ገንዘብ የሚወጣባቸው ለወራት በዕቅድ ተይዘው የሚደገሱ በዓላት በድምቀት እንዲከበሩ ይደረጋል፡፡ “አዲስ አበባ አራት … [Read more...] about ራስ እምሩን በተመለከተ፤
Opinions
የሳውዲ የተራዘመ የምህረት አዋጅ እንዴት እንጠቀምበት?
* የተራዘመው የምህረት አዋጅ * የ90 ቀኑ ምህረት አዋጅ አስተምሮቱ .. * አጭሩን ጊዜ በአግባቡ ለመጠቀም .. * የበረራ ፈቃድ እና የአሻራ አሰጣጡ ተጠያቂ ማነው? * በቂ ድጋፍ ለማድረግ የሰው ሃይልን ስለማደራጀት .. * ስራው በማን ነው የሚሰራው? የዲፕሎማቶች? መኖሪያና የስራ ፈቃድ የሌላቸው ሳውዲን በ90 ቀን ውስጥ ለቀው እንዲወጡ የተሰጠው ቀነ ገደብ ለ30 ቀናት ተራዝሟል ። በሳውዲው ንጉሳዊ ቤተሰቦች አመራሮች ይሁንታ አግኝቶ በሀገር ውስጥ ሚኒስትሩ ትዕዛዝ ማምሻውን በፖስፖርት የበላይ ዳይሬክተር በሜጀር ጀኔራል ሱሌማን የህያ ይፋ የሆነው መረጃ ይፋ ይፋ ሆኗል። ይፋ የሆነው የምህረት አዋጅ የ90 ቀኑ የምህረት አዋጅ ካለቀበት እአአ ከሰኔ 25 ጀምሮ እስከ ቀጣዩ ሐምሌ 25 ቀን 2017 ድረስ የሚቆይ እንደሆነው ታውቋል። ፖስፖርት የበላይ ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል … [Read more...] about የሳውዲ የተራዘመ የምህረት አዋጅ እንዴት እንጠቀምበት?
ይድረስ ለአርበኛው ጸሐፊ ዕዝራ ዘለቀ (ዕዝራ አስቻለው ዘለቀ)
በተከታታይ የጻፍካቸውን ሁለት ግሩም መጣጥፎች በፍቅር አነበብኳቸው፡፡ በነዚህ ጽሑፎች እንደተረዳሁት ጥሩ አንባቢ ነህ፤ የብዕር አጣጣልህም ውብ ነው፡፡ ሀገርህንም እንደምትወድ በጽሑፍህ ብቻ ሣይሆን በረሃ መውረድህ ራሱም በቂ ምሥክር ነው፡፡ ማቄን ጨርቄን ሳትል ለአንዲት እናትህ ኢትዮጵያ ስትል እያሳለፍከው ያለኸውን መከራና ስቃይ መረዳት እችላለሁና የእምዬ አምላክ ይከተልህ፡፡ አንተን ብቻም ሣይሆን ለተመሳሳይ በጎ ዓላማ የተሰለፋችሁትን ጓዶችህንም ሁሉ ፈጣሪ ይጠብቃችሁ፤ ያሰባችሁትንም ያሳካላችሁ፡፡ በረከቱ የሁላችንም ነውና፡፡ እኛም በጸሎት ከጎናችሁ አለን፡፡ ይሁንና በግልጽ መነጋገር ለሁሉም ወገን የሚበጅ እንደመሆኑ ከጽሑፍህ ለመረዳት የሞከርኩትን በግልጽ የተነገሩና ያልተነገሩ አንዳንድ ነጥቦችን ማንሳት ወደድኩ፡፡ ከብረት ዝገት ከሰው ስህተት እንደመገኘቱ ተሳስቼ የተረዳሁብህ ነገር … [Read more...] about ይድረስ ለአርበኛው ጸሐፊ ዕዝራ ዘለቀ (ዕዝራ አስቻለው ዘለቀ)
“ተዋከበና!”
ለቴዲ አፍሮ ዉበት ያምራል እንዴ? ቁንጅናስ ያምራል? አንዳንድ ጊዜ ሰዎች “I didn’t do nothing” ወይም “I didn’t say nothing” ሲሉ መስማት አዲስ አይደለም። እጅግ በጣም አልፎ አልፎ ቢሆንም፣ እንግሊዝኛ ያፍ መፍቻ ቋንቋቸው የሆኑ ሰዎችም ሲሉት ይሰማሉ። በቋንቋው ህግ መሰረት ይህ አ/ነገር ጎደሎ ነው። “double negative” የሚፈጥረው የ“positive” ትርጉም/ፍቺ ግድፈት ይመስለኛል። ሁለት ነጌቲቭ (“didn’t” እና “nothing”) ቃላት/ሃረጎች፣ አንዳንዴ ፖዚቲቭ ትርጉም የሚያስከትሉ መሆኑ ነው። “I didn’t do nothing” ወይም “I didn’t say nothing” በሚሉት ዓ.ነገሮች ውስጥ ለማለት የተፈለገው “ምንም አላደረግሁም”/“ምንም አልተናገርኩም” ሲሆን፣ ትርጉሙ ግን የተገላቢጦሹ ሊሆን እንኳን ባይችልም፣ በጣም ያደናግራል። እናም … [Read more...] about “ተዋከበና!”
አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ አወጣ
የዚህች ጦማር ዋና ዓላማ፡ “ያዲስ አበባው ሲኖዶስ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ከቀሩት አኀት አብያተ ክርስቲያናት ተነጥላ ከሀያ በላይ ስህተት ሰርታለችና ትመርመር የሚል ክስና ወቀሳ አቀረበ” ብሎ ሀራ ዘተዋህዶ ባቀረበው ዜና፤ ግራ የተጋባችሁ ክርስቲያኖች፤ “በአኀት አብያተ ክርስቲያናት ሐዋርያዊ ትውፊት አንጻር እንዴት ትመለከተዋለህ“ ብላችሁ ላቀረባችሁልኝ ጥያቄ ለመመለስ ነው። ይህ የቀረበው ሀሳብ የሀራ ዘተዋህዶ ድረ ገጽ ፈጠራ ከሆነ፡ ”አባት ሆ ይ!እኔ በአንተ አንተ በእኔ እንዳለህ እነርሱም በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ”(ዮሐ 17፡ 21“)በሚለው ክርስቶሳዊ ቃል፤ አንድነታቸውን አጽንተው በኖሩት በአኀት አብያተ ክርስቲያናት ላይ እየዘመተ ነው ማለት ይቻላል። ምናልባትም ከጥንት ጀምሮ እነዚህን ጥንታውያት አብያተ ክርስቲያናትን ለማጥፋት የሚታገሉት የሰባልዮስ ወይም የአርዮስ ተከታዮች ሊሆን … [Read more...] about አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ አወጣ
የሻለቃ ዳዊት የዋሽንግተን ሲያትል ንግግር በሞረሽ ዕይታ!
ሰዎች መልካም ሢሠሩና ሲናገሩ ማመስገን፣ መጥፎ ሢሠሩና ሲናገሩ ደግሞ መምከርና መገሰጥ ተገቢ ነው። ምንጊዜም ሁሉም ሰው ሕይዎቱን ሙሉ ስሕተት ብቻ እየሠራ አይኖርም። መልካም ነገሮችም ይሠራል። ልዩነት የሚኖረው የትኛው ሥራው ነው የሚያመዝነው? መልካሙ ወይስ መጥፎ የሚለውን መመዘኑ ላይ ነው። በዚህ ረገድ የሻለቃ ዳዊትን ሥራዎች መዝኖ፤ የማሞገሱም ሆነ የመውቀሱ ተግባር፣ እርሳቸውን የሚያውቁ፣ አብረዋቸው የሠሩ፣ የትaምህርትና የሥራ ባልደረቦቻቸው ተግባር ይሆናል። ሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ለዐማራ ነገድ ድምፅ ለመሆን የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ላይ ያለ ድርጅት ነው። ስለዚህ ሻለቃውን በዚህ ንግግራቸው፣ ላለፉት 5 ዓመታት ሲጮኽባቸው የነበሩ አንኳር ጉዳዮችን እያነሱ፣ ዐማራውን ሲያወግዙ፣ በጠላትነት ፈርጀው የዘር ፍጅት በፈጸሙ ግለሰቦችና ስብስቦች ፊት በኩራት ቆመው በመናገራቸው ከልብ … [Read more...] about የሻለቃ ዳዊት የዋሽንግተን ሲያትል ንግግር በሞረሽ ዕይታ!
አንድነት ከማን ጋር? አንድነት ለምን? አንድነት መቼ?
ዐማራው በባህሉ፣ በሥነ-ልቦናውና በፖለቲካ ታሪኩ እንዲሁም በሚጋራቸው የወል ዕሴቶቹ፣ በእሱነቱና በኢትዮጵያዊነቱ መካከል የተሰመረ ልዩነት ባለመኖሩ፣በዘር ጠላትነት ተፈርጆ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ሲፈጸምበት ፣ወንጀሉ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚፈጸም ነው በማለት፣ለምን? እንዴት? ብሎ ለመጠየቅ ከሁለት ዓሥርተ ዓመታት በላይ እንደፈጀበት በግልጽ ይታወቃል። ይህም ዘረኛው የትግሬ ወያኔ ቡድንና አጋሮቹ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዐማሮች ከምድረ ኢትዮጵያ እንዲጠፉ ሠፊ ዕድልና አጋጣሚ እንዲያገኙ ረድቷቸዋል። ይህን ያህል ቁጥር ያለው ከትግሬ፣ ከሶማሌ፣ ከጉራጌ፣ ከሲዳማ፣ ከወላይታ ቢጠፋ ሁሉም የነገዱ አባሎች ጠፉ ማለት ነበር። ዐማራው ይኸን ያህል ቁጥር የሰው ኃይል ጠፍቶበት፣ ምንም ያልመሰለው ከጣና ሐይቅ በጭልፋ ውኃ የመቀነስ ያህል ሆኖ በመታየቱ፣ የሁሉንም የዐማራውን ነገድ ጆሮ … [Read more...] about አንድነት ከማን ጋር? አንድነት ለምን? አንድነት መቼ?
ሁለት የኢትዮጵያ ሴት ሯጭ ስፖርተኞች በኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ያሳዩት ጋጠወጥ ባሕሪና ፖለቲካዊ ምርጫ!
ይህ ትችት የኔን ጽሑፍ በሚያስተናግዱ እንደሚለጠፍ ባውቅም፤ ለሌሎቹ ተቃዋሚ ድረገፆች በሙሉ ተልኳል። ቢያወጡት አስተማሪ ነው። ብዙዎቹ ግን እንደማያውጡት ጥርጣሬ አለኝ። ምክንያቱም የፖለቲካ መሪዎቻቸውና ድርጅቶቻቸውን ጨምሮ በዚህ ትችት ስለተካተቱ ወገንተኛነታቸው ከሉጓም በበለጠ ይስባቸዋል። ለማንኛወም ለታሪክ ልኬአለሁ። አሁን ወደ ርዕሱ ልግባ። በትግርኛ በምንመስለው ምሳሌ ልጀምር፡ {ዝፀገባ ደራሁስ ምስ ፀኻድም ማሕበር ይኣትዋ} “የጠገቡ ዶሮዎች ከጭልፊቶች ጋር ማሕበር ይገባሉ” ይባላል። ሁለቱ ዓለም አቀፍ የሴቶች እውቅ ሯጮች ከጭልፊቶች ጋር ማሕበር መግባቱ ምርጫቸው አድርገው ይሆናል። የጭልፊቶቹ እና የዶሮዎቹ ማሕበር የሚቆየው ዕድሜ አብረን የምናየው ይሆናል። ሰሞኑን በአጋጣሚ “ዩቱብ” ድረገጽ ላይ አንድ ማሕደር ለመፈተሽ ጎራ ስል ድንገት ያላሰብኩበትን እና አስደንጋጭ … [Read more...] about ሁለት የኢትዮጵያ ሴት ሯጭ ስፖርተኞች በኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ያሳዩት ጋጠወጥ ባሕሪና ፖለቲካዊ ምርጫ!
Many into one Africa, one into many Africans
“I know no national boundary where the African is concerned. The whole world is my province until Africa is free.” - Marcus. M. Garvey. The expression of many identities is seen as the celebration of diversity and a legitimate vehicle for claims to political and other forms of rights. The resolution of diverse identities into compound /combined identities and unities is often suspect bearing the implication that rights and diversity might be sacrificed in the process of bringing about a new … [Read more...] about Many into one Africa, one into many Africans
የጋራ የሆነች ኢትዮጵያ እንዴት እንመሠርታለን?
እስካሁን ለምን በተደጋጋሚ ከሸፍን? እንደምን አላችሁ፣ አሰላሙ አሌይኩም፣ አካም ጂርቱ፣ እንደምን አረፈዳችሁ (good afternoon everyone)። የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ጉባዔ በዚህ ስብሰባ ላይ እንድናገር ስለ ጋበዘኝ ልባዊ ምስጋናዬን ላቀርብ እወዳለሁ። ከእናንተ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጋር በመሆን ስለምትወዷት አገራችን የወደፊት ሁኔታ ለመወያየት መብቃት ታላቅ ዕድል ነው። በአሁኑ ወቅት አገራችን በከባድ ቀውስ ውስጥ እንደምትገኝ ሁላችንም የምናውቀው ሃቅ ነው፤ ይህም ቀውስ በአንድ ጊዜ የተከሰተ ሳይሆን ለዓመታት ሲጠራቀምና ሲከማች የቆየ ነው። የአገራችን የወደፊት ሁኔታ ሁላችንንም የሚያሳስበን በመሆኑ እናንተም ይህንኑ ሃሳብ እንዳቀርብ በጠየቃችሁኝ መሠረት እኛ ኢትዮጵያውያን በኅብረት በመሥራት ለአገራችን የተሻለ የወደፊት ተስፋ ማምጣት እንዴት እንደምንችል ሃሳቤን … [Read more...] about የጋራ የሆነች ኢትዮጵያ እንዴት እንመሠርታለን?










