ዛሬም እንደሳምንቱ መብታችንን እያሉ ኢትዮጵያዊያን በየመስጊዱ ተሰብሰበዋል። በየቀኑ በየቤተክርስትያኑ ጸሎታቸውን ያደርሳሉ። በየትምህርት ቤቱ በራቸው ተንኳኩቶ እንዳይወሰዱ ተደብቀው ያጠናሉ። መምህራን በፍራቻ፤ ለተማሪዎቻቸው ሳይሆን ለካድሬዎቹ ይሽቆጠቆጣሉ። አርሶ አደሮች ለሚያርሱበት መሬት፣ ለማዳበሪያና ለካድሬ ሲሉ አንገታቸውን ደፍተዋል። ላብ አደሮች የሥራ ዋስትና አንገታቸውን አንቆ ወገባቸውን አጉብጦታል። ነጋዴዎች ከኤፈርት ጋር ውድድሩ ራቁታቸውን አስቀርቷቸዋል። ጋዜጠኞች ዓይኖቻችሁን ጨፍናችሁ እኔ የምላችሁን ካላደረጋችሁ ተብለው እስር ቤቱን ሞልተውታል። ማን ተርፎ? የፖለቲካ ምኅዳሩን ማነቆ የጨበጠው መንግሥት አምልኩኝ ብሏል። ሀገራችን ባለችበት የፖለቲካ ሀቅና እኛ አሁን ባለንበት ድንዘዛ፤ አንድ የሚያነቃ ብራቅ ብልጭ ሊልብን ይገባል። የአንድነት ውይይት የግድ ነው። ይቺ ሀገራችን … [Read more...] about በውጭ ያለነው ኢትዮጵያዊያን ምርጫዎች አሉን
Opinions
ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከጥፋት የሚያድነው ብቸኛው መንገድ!!!
ዛሬ እውነት እውነቱን እንቅጭ እንቅጩን እንነጋገራለን፡፡ እንዴ! ይሄ ሰው ከዚህ ቀደም ሲያወራልን የኖረው ቅጥፈት ነበር እንዴ? እንዳትሉ፤ አለ አይደል ይሄ መፏከቱን መሸራደዱን መበሻሸቁን ትተን እንደ ባለ አእምሮና ኃላፊነት እንደሚሰማው ዜጋ በንጹሕ በቅዱስ ልቡና ልዕልና ያለውን ሐሳብ አንሥተን እንወያያለን ለማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያ አምላክ ዐይነ ሕሊናችንን ያብራልን እዝነ ልቡናችንን ይክፈትልን አሜን!! ሀገራችን ኢትዮጵያ የዘውግ ፖለቲካ (እምነተ-አስተዳደር) ወይም ብሔር ተኮር የሆነ ከፋፋይና አጥፊ የአገዛዝ ሥርዓት ውስጥ በግዳጅ እንድትዘፈቅ ከተደረገች 24ኛ ዓመታችንን ይዘናል፡፡ በዚህ ዘመን ውስጥ አንድነት የነበረው ሕዝብ በግድ ካልተነጣጠልክ፣ በጎሪጥ ካልተያየህ፣ እንደ አንድ ሀገር ሕዝብ ሁሉ ለእኛ ለእኛ ሳይሆን ለእኔ ለእኔ (ለብሔረሰቡ ብቻ) ካላልክ ተብሎ እየተወተወተ ወዶ … [Read more...] about ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከጥፋት የሚያድነው ብቸኛው መንገድ!!!
Center for the Rights of Ethiopian Women (CREW) Fundraising Event
አራዊታዊ መንግሥታት
አራዊታዊው ኢሀደግ እና የየመን መንግሥት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ በፈጸሙት አራዊታዊ ተግባር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስት ዶክተር ቀሲስ አማረ ካሣየ ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ አባ ኃ/ሚካኤል የሰጡት መግለጫ፦ በአገራችን ላይ ክፉ ዘመን የወለደው አራዊታዊው መንግሥትና የየመን መንግሥት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የፈጸሙት አራዊታዊ ተግባር በፈጣሪና በፍጡሩ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው፤ የሰው ጥንተ ጠላት የሆነው የሰይጣን ተግባር ስለሆነ፤ በቅድስት ቤተ ክርስቲያችን የሚወገዝ ነው። ሕዝባችንም የዜግነት ከለላ ከሰጣቸው ከእንግሊዝ መንግሥት ጋራ በመተባበር አቶ አንዳርጋቸውንና በተመሳሳይ አራዊታዊ አደና የተያዙትን ሁሉ ኢትዮጵያውያን ለማስለቀቅ የጀመረውን ጥረት አስፈላጊ በሆነው ሁሉ መንገድ እንዲቀጥል እግዚአብሔር የሚቀበለውና የቅድስት ቤተ ክርስቲያንም … [Read more...] about አራዊታዊ መንግሥታት
ነጻነትን ለመጎናጸፍ ባሩዷን ማሽተት የግድ ነው !!!
የወያኔ የግፍ ስርዓት በህዝብ ትከሻ ላይ ድሩን አድርቶ ፤ የማይጠረግ እስኪመስለን ድረስ ሁለት አስርት አመታቶችን በላያችን ላይ ዘልቋል ።በሰላማዊ መንገድ የግፉ ስርዓት ተቋጭቶ ፍትህና እኩልነት በሀገራችን ይሰፍን ዘንድ ብዙ ተሞክሯል ። ነገር ግን በወያኔ ስልጣን አልጠግብ ባይነት እና የሰላማዊው መንገድ ክርችም ብሎ በመዘጋቱ ባሩዷን ማሽተት ግድ የሆነበት ጊዜ ላይ ከደረስን ከራርመናል ።ትግሉ ከኛ ምን ያህል የአላማ ጽናትን ይፈልጋል ? ምን ያህልስ መስዋእትነትን ያስከፍለናል ? እንዴትስ ብንታገል ካሰብነው የነጻነት ደጃፍ ባጭሩ ያደርሰናል ብለን ብንጠያየቅ ትክክለኛ ጊዜው አሁን ይመስለኛል። አብዛኛው ኢትዮጵያዊም በተለይም በወጣትነት የእድሜ ክልል ያለው የህብረተሰብ ክፍል ስልጣንን ከህወሃት መዳፍ ውጭ አይቶት ስለማያውቅ ፤ ሀገሪቱን እነሱ ብቻ እንዲመሩ መለኮታዊ የሆነ ፈቃድ ያላቸው … [Read more...] about ነጻነትን ለመጎናጸፍ ባሩዷን ማሽተት የግድ ነው !!!
የጋዛ ፍልስጥኤማውያን የደም እንባ!
የእስራኤል የ10 ቀናት የአየር ድብደባ ከ220 በላይ ፍልስጥኤማውያን የጋዛ ነዋሪዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በሚወሰደው ዘመቻ ነገን ላያዩ መቀጠፋቸውን እየሰማን ነው: (ከአንድ ሽህ በላይ የዘለቁ በጠና የቆሰሉትን እና ከቀያቸው የተፈናቀሉት ዜጎችን መከራ እያየንም ነው። እኒህኞቹን በራሳቸው ሀገር ስደተኛ የሆኑትንማ ፍዳ ማየቱ ከሞቱት በላይ ያማል። ሰቆቃው በዚህ ቢያቆም መልካም ነበር ፣ ግን አልሆነም ። በሳምንቱ መጀመሪያ የፍልስጥኤማውያን ሃማስ የጦር ክንፍ ሰው አልባ ሚጢጢ አውሮፕላን Drone ...በእስራኤል ሰማይ መስፈንጠሩን አስታወቀ። ይህም የሃማስን የሚሳኤል ሮኬት ውንጨፋ ለወረራው ምክንያት ላደረጉት እስራኤሎች ከስጋት ባለፈ ጥሩ የመልሶ ማጥቂያ ምክንያት ሆነና ነገሮችን ሁሉ በፍጥነት መቀያየር ይዘዋል። ብቻ ...ዛሬ ሃሙስ ለአርብ በደረቁ ሌሊት የደረሰን ሰበር ዜና አስራኤል … [Read more...] about የጋዛ ፍልስጥኤማውያን የደም እንባ!
የማይጮኹት . . . በዓሉ ግርማን የበሉት ጅቦች
“ይህችን ውድ የሆነች ትንሽ ቁራሽ ሕይወት እንደ አብርሃም ቤት የለኝ፣ እንደ ሙሴ መቃብሬ ላይታወቅ፡፡ መኖር - መጻፍ - ሕይወትን በተስፋ ወደፊት እየኖርኩና ወደኋላም እያስተዋልኳት፡፡” በዓሉ ግርማ - ደራሲው እውቁን ጋዜጠኛና ደራሲ በዓሉ ግርማን በአጸደ ሕይወት ካጣነው፤ በዘንድሮው የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ሠላሳ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ውድ ባለቤቱ ወይዘሮ አልማዝ አበራ በዘመነ ኢሕአዴግ ስለ ባለቤቷ ከቤት እንደወጣ መቅረት ጉዳይ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ቀርባ የጠቅላይ አቃቤ ሕግ ምስክርነቷን እንድትሰጥ ተደርጋ ነበር፡፡ ያንን የእሷን የፍርድ ቤት የምስክርነት ቃል የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አቅርቦ ካስደመጠንም ሁለት አሠርታት ዓመታት እንደዋዛ ሊቆጠሩ ነው፡፡ ውድ ባለቤቱ ወ/ሮ አልማዝ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ያቀረበችውና እልክና ቁጭት የተመላበት የምስክርነት ቃሏ አንድምታ እንዲህ … [Read more...] about የማይጮኹት . . . በዓሉ ግርማን የበሉት ጅቦች
የዘር ማጥፋት ወንጀሎች በአማራ ሕዝብ ላይ በታሪክ ሂደት ውስጥ ከጥንት እስከ ዛሬ!
ይሄንን ጽሑፍ ታች አምና ከጉራፈርዳና አካባቢው አማራ በመሆናቸው ምክንያት ብቻ ሕጋዊነታቸውን የሚያረጋግጡ ሰነዶችን ይዘው እያለ ሕጋዊ ሆነው የየክልሉ መንግሥት አውቋቸው በሥርዓቱ ግብር እየከፈሉ እየኖሩ የነበሩ ምስኪን ገበሬዎችን “ሕገ ወጥ ሰፋሪዎች” በሚል ሕገ ወጥነታቸው አግባብነት ባለው የሕግ አካል (ፍርድቤት) ክስ ተመስርቶባቸው ሳይረጋገጥባቸው በጅምላ በግፍና በሕገ ወጥ መንገድ ንብረታቸውን ሁሉ ተወርሰው እንዲወጡ በተደረገ ጊዜ ጽፌው ለጥቂት መደበኛና ኢመደበኛ (Conventional and Social Media) ልኬው ነበር እስከማውቀው ድረስ ለሕዝብ ይፋ አድርገውት ያስነበቡት ወይም ያስደመጡት አልነበሩምና ሕዝብ ሊያውቃቸው የሚገባ በርካታ ቁምነገሮች ስላሉት እንዳያመልጣቹህ በማሰብ ወደ እናንተ አድርሸዋለሁ መልካም ንባብ፡፡ የዐፄ ዮሐንስ 4ኛ መንግሥታዊ (official) ቋንቋ … [Read more...] about የዘር ማጥፋት ወንጀሎች በአማራ ሕዝብ ላይ በታሪክ ሂደት ውስጥ ከጥንት እስከ ዛሬ!
ወራቱ ረመዷን ነው! ፍቷቸው!
ወራቱ ረመዷን ነው፡፡ በዚህ ወር ሰላም፣ ማርታ፣ ይቅርታ እና ምሕረት ነው የሚለመነው፡፡ አዲስ ሰው ለመሆን ነው ጥረት የምናደርገው፡፡ ባለፉት ሶስት ዓመታት ባሳለፍኳቸው ረመዳኖች የሚሰሩት ነገሮች ግን ከዚህ ቅዱስ ወር የምናገኘውን በረከትና ጸጋ በአግባቡ እንዳንቋደስ እና ቀልባችንን ሙሉ በሙሉ ወደ ፈጣሪያችን እንዳንመልስ ጋሬጣ እየሆኑብን ተቸግረናል፡፡ ወራቱ ረመዳን ነው፡፡ ትናንት ሰዎች ታስረዋል፡፡ ማን እንደታሰረም ስለሚታወቅ መግለጹ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ነገር ግን በየጊዜው ሰዎችን ማሰር የምንመኛት ኢትዮጵያ እንድትመጣ ለማድረግ አንዳች ጠቀሜታ የለውም፡፡ ገዥው ፓርቲ የሚያልመውን የኢትዮጵያ ራዕይን በ2020 ለማሳካትም ሆነ ሌሎች በተለየ መንገድ የሚመኟትን ለሁላችንም የምትሆነውን ኢትዮጵያን ለመፍጠር ምንም አይፈይድም፡፡ በሰከነ መንፈሰ መደማመጥና ችግሮችን በውይይት ለመፍታት … [Read more...] about ወራቱ ረመዷን ነው! ፍቷቸው!
መንግስታዊ ሽብርተኝነትን የሚሸከም ትከሻ አይኖረንም!!!
የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት መሪዎችን እና በአገዛዙ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ማሰሩን፣ ማሰቃየቱንና ግድያውን ተያይዞታል፡፡ በህገ መንግስቱ የተካተቱ የሰብዓዊ መብቶችንና ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በሙሉ የሚጥሰውና የአምባገነንነት ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ያፀደቀው የፀረ-ሽብር አዋጅ ከፀደቀበት እለት አንስቶ ኢህአዴግ ለስልጣኔ … [Read more...] about መንግስታዊ ሽብርተኝነትን የሚሸከም ትከሻ አይኖረንም!!!










