• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወራቱ ረመዷን ነው! ፍቷቸው!

July 11, 2014 09:59 am by Editor 2 Comments

ወራቱ ረመዷን ነው፡፡ በዚህ ወር ሰላም፣ ማርታ፣ ይቅርታ እና ምሕረት ነው የሚለመነው፡፡ አዲስ ሰው ለመሆን ነው ጥረት የምናደርገው፡፡ ባለፉት ሶስት ዓመታት ባሳለፍኳቸው ረመዳኖች የሚሰሩት ነገሮች ግን ከዚህ ቅዱስ ወር የምናገኘውን በረከትና ጸጋ በአግባቡ እንዳንቋደስ እና ቀልባችንን ሙሉ በሙሉ ወደ ፈጣሪያችን እንዳንመልስ ጋሬጣ እየሆኑብን ተቸግረናል፡፡

ወራቱ ረመዳን ነው፡፡ ትናንት ሰዎች ታስረዋል፡፡ ማን እንደታሰረም ስለሚታወቅ መግለጹ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ነገር ግን በየጊዜው ሰዎችን ማሰር የምንመኛት ኢትዮጵያ እንድትመጣ ለማድረግ አንዳች ጠቀሜታ የለውም፡፡ ገዥው ፓርቲ የሚያልመውን የኢትዮጵያ ራዕይን በ2020 ለማሳካትም ሆነ ሌሎች በተለየ መንገድ የሚመኟትን ለሁላችንም የምትሆነውን ኢትዮጵያን ለመፍጠር ምንም አይፈይድም፡፡ በሰከነ መንፈሰ መደማመጥና ችግሮችን በውይይት ለመፍታት መጣር ነው ለሁሉም የሚበጀው፡፡

ወራቱ ረመዷን ነው፡፡ ይህ የተቀደሰ ወር ሸይጣን የሚታሰርበት እንጂ የሰው ልጅ ወደ ወህኒ የሚወረወርበት ወር አይደለም፡፡ ስለዚህ ትናንት የታሰረውን አብረሃ ደስታን ጨምሮ አላግባብ የታሰሩት ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በአስቸኳይ ይፈቱ ዘንድ በሀያሉ ፈጣሪያችን ስም እንጠይቃችኋለን፡፡ ሌላም እስር በዚህ ወር እንዳይደገም ይደረግልን!!

ወራቱ ረመዷን ነው፡፡ ይህንን የእስር እርምጃ ተከትሎ በኢንተርኔት የሚካሄዱት አንዳንድ ልብ የሚነኩ ስድቦች እንዲቆሙም እንጠይቃለን፡፡ በተለይ የዘረኝነት ስድቦች እጅግ አሳፋሪና ደረጃችንን ዝቅ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ ስለዚህ ሌላ ሌላውን መጻፍ እንጂ ስድቦቹን ማቆም ይገባል፡፡ “እምቢ!” ቢባል እንኳ እኛ ፈልገን ባላገኘነውና ከፈጣሪ በተሰጠን ዘር፣ ጎሳና ብሄረሰብ መሰዳደቡ ይቁምልን (በተለይ አንዳንዶች በተከበረው የትግራይ ህዝብ ላይ የሚያካሄዱት አስጸያፊ ስድብ በአስቸኳይ መገታት አለበት)፡፡

ወራቱ ረመዳን ነው! በአማን ጀምረነዋል፡፡ በአማን እንጨርሰው ዘንድ ነገሮች በጥንቃቄ ይያዙልን፡፡ አላህ ለሁላችንም ልቦና ይስጠን፡፡ አሚን!!

ወራቱ ረመዷን ነው!!

—–

አፈንዲ ሙተቂ በፌስቡክ ከጻፈው የተወሰደ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. shimon says

    July 11, 2014 10:52 am at 10:52 am

    ‘ክርስቲያንም ሆንክ ኢስላም ይሁዲም ሆንክ ፓጋን ለኢትዮጲያ ክፉ አትመኝ ለምን እልከኝ .. ይህ ህዝብ መንግስት ላይ ቢያምፅ ፈጣሪ እጁን እንደሚያስገባ ታውቃለህ ልክ እንደናንተ ከላይ … ካላመንክ ጠይቅ ..¡¡

    Reply
  2. Abbaa says

    July 11, 2014 11:28 am at 11:28 am

    Afendi, tiru hedeh mecheresha lay “beteley betekeberew yetigray hizb” yalkew, Tetekami, Tikim felagi, weyim Feri asmesiloshal.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule