• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጋዛ ፍልስጥኤማውያን የደም እንባ!

July 18, 2014 04:56 pm by Editor Leave a Comment

የእስራኤል የ10 ቀናት የአየር ድብደባ ከ220 በላይ ፍልስጥኤማውያን የጋዛ ነዋሪዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በሚወሰደው ዘመቻ ነገን ላያዩ መቀጠፋቸውን እየሰማን ነው: (ከአንድ ሽህ በላይ የዘለቁ በጠና የቆሰሉትን እና ከቀያቸው የተፈናቀሉት ዜጎችን መከራ እያየንም ነው። እኒህኞቹን በራሳቸው ሀገር ስደተኛ የሆኑትንማ ፍዳ ማየቱ ከሞቱት በላይ ያማል።

ሰቆቃው በዚህ ቢያቆም መልካም ነበር ፣ ግን አልሆነም ።  በሳምንቱ መጀመሪያ የፍልስጥኤማውያን ሃማስ የጦር ክንፍ ሰው አልባ ሚጢጢ አውሮፕላን Drone …በእስራኤል ሰማይ መስፈንጠሩን አስታወቀ። ይህም የሃማስን የሚሳኤል ሮኬት ውንጨፋ ለወረራው ምክንያት ላደረጉት እስራኤሎች ከስጋት ባለፈ ጥሩ የመልሶ ማጥቂያ ምክንያት ሆነና ነገሮችን ሁሉ በፍጥነት መቀያየር ይዘዋል።

ብቻ …ዛሬ ሃሙስ ለአርብ በደረቁ ሌሊት የደረሰን ሰበር ዜና አስራኤል እግረኛ ጦር ወደ ጋዛ ማሰማራቷን ጠቁሟል። ሃማስም ከእግረኛው ጦር ጋር ፍልሚያው መጀመሩን ከዛቻ ጋር አስታውቋል። የተፈራው አደጋ  የፍጥጫ እልህ ውዝግቡ የፍጻሜ ውጤት አቅጣጫ እዚህ ላይ ደርሷል።  የቦንብ ናዳ  ያላባራባት ጋዛና የጋዛ ነዋሪ በሰማዩ ስር በሃዘን ድባብ ተውጦ ምድር ገሃነብ ሆኖበት ሰንብቷል። የሃማስ ተወንጫፊ ሚሳኤሎች ጎድተው ላይጎዱ በተለያዩ የጽዮኗ ምድር ከመዝነብ  ያቆማቸው የለም። እስካሁን ሞቶ የሰማነው እስራኤላዊ ቁጥር ግን አንድ ብቻ ነው።

እስራኤል  “ነውጠኛ አሸባሪው ሃማስን የማጽዳት ዘመቻ” በማለት በያዘችው ማጥቃት በምክንያትነት ከሚጠቀሱት  ኢላማዎች መካከል እስካሁን ተገደሉ የተባሉ ቁጥር ፣ ከተገደሉት ንጹሃን ጋር ሲወዳደር እዚህ ግባ አይባልም። በዋይታ ይህችን ፍትህ የጎደላት አለም እየተለዩ ያሉት ፍልስጥኤማውያን አቅመ የእድሜ ባለጸጋዎች፣ ህጻናትና አባወራ የቤተሰብ አባላት ናቸው። ይህ ልብን በሃዘን ቆልፎ ይሰብራል  🙁

ከሁሉም የሚዘገንነው በእስራኤል ዘመቻ የተቀጠፉት “ጦር ሰባቂ ፣ ቆስቋሽ ” የሚባሉት የሃማስ ሚሊሻዎች አለመሆናቸው ሲሆን ሚሊሽያ ታጣቂዎች እንደ ዶፍ በሚዘንበው አረር  ኢላማ የገቡ አይመስልም። “ለሃጥአን የመጣ ለጻድቃን ” እንዲሉ  በአዋጅ ነጋሪት ክተት ተብሎ የተዘመተባቸው ሃማሶች ሳይገደሉ ንጹሃን በግፍ እያለቁ ነው። ከሃማስ ሸማቂ በኩል ሞቱ የተባሉት ከቆሰሉት ጋር ቢደመሩ ከሃያ ፈቀቅ ለማለቱ መረጃ አላየሁም። ድብደባውም ሃማስን ሚሊሻዎች ሚሳኤል ከመወንጨፍ አላስቆማቸውም። ይህ ምልክት ያን ሰሞን ” የመከራ ደወል !” ያልኩትን የአደጋ ስጋት ሲያዘክር ዛሬ የስጋቱ ጊዜ አክትሞ መከራ ሰቆቃውን እያየነው ነው።  እየሆነ ያለው አሳዛኙ ውጤት ፍጻሜ ይህ ይመስላል !  ዳሩ ግን ሃማስን ለማንበርከክ የግዛት ክልሉንና የሚያስተዳድረውን ህዝብ በአየርና በምድር ጦር በትምክህት ደፍጥጦ መበቀል ከሆነ ሌላ ነገር ነው።

የሃማስ የጦር ክንፍ መክቶ  ላይመክት ፣ ጎድቶ ላይጎዳ ባስፈነጠራቸው ሮኬቶች ሌላ አደጋ በህዝቡ ላይ እያስከተለ ነው። በአጣብቂኝ ስርቻም ሆኘ በራሪ Drone  ሰራሁ ብሎ ማወጁ ለፍልስጥኤማውያን የፈየደው ወረራውን ማፋጠን ነው። ብቻ ሃማስ ከእስራኤል ጦር ጋር ተፋጦ በሚያደርገው መቆራቆስ የንጹሃን ደም ግብር የማከፈልበት መቸ ለሚመጣው፣  ማን ለሚኖርበት ትንሳኤ እንደሆነ አልገባኝ …

አረቦች ለፍልስጥኤም ግፉአን ወንድሞቻቸው መከታ እንዳይሆኑ በልዩነት ተበታትነዋል።  የአለም መንግስታት በአንጻሩ ይህ መሰሉ ግፍ በጋዛ ፍልስጥኤም ሲፈጸም ዛሬም መሸምገል ገዷቸው ደም ሲፈስ የግፍ ተመልካች ሆነዋል። በሩዋንዳው የጅምላ ጭፍጨፋ እልፍ አእላፍ አልቀው ፣ በትኩሱ ሬሳ ላይ ቆመው ያነቡት የአለም መራሔ መንግስታት  “ይህ ግፍ ፈጽሞ አይደገምም” Never Again ብለው ያፈሰሱት እንባ “የአዞ እንባ” መሆኑን ዛሬም ሆነ ትናንት በጋዛ ፍልጥኤማውያን እየሆነ ባለው “የአዛኝ እንባቸውን” እያየነው ነው: (

የእስራኤልን ዘመቻ ፣ የንጹሃንን እልቂት ፣ የሃማስን ስልት የጎደለው መከላከል በሉት ማጥቃት አልገባህ ብሎኛል። ይህንን ንጹሃን የሚቀጠፉበትን ዘመቻ ለማውገዝ ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው። ይህ ሁሉ ውስብስብ ያልሆነ ግን ቅንነት ጠፍቶ የአለም  ማህበረሰብ መፍታት ባልቻሉት ውዝግብ በዚህ ዘመን ይህን ግፍ አለም ማስተናገድ ነበረባት?  ይህ ግልጽ የሃይል ሚዛን እና የተጽዕኖ መፍጠር ጫና  ለፍልስጥኤም ንጹሃን ማለቅና ለአለም ዝምታ መምረጥ ምክንያት አይደለምን ?  ይህስ በራሱ ግፍ አይደለምን ? ግልጽ የሚታየው እንቆቅልሽ መፈቻው ጊዜ መቸ ይሆን?  በሁለት ጽንፈኞች መካከል ታርቀው የሚረግፉት የፍልስጥኤማውያን እንባስ ማቆሚያው መቸ ነው?

እስኪ ቸር ያሰማን …

ነቢዩ ሲራክ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule