የገቢዎች ሚኒስቴር 60 ሚሊዮን ብር የሚሆን የውጭ ሃገራት ገንዘብና ሰባት ኪሎግራም ወርቅ ጥር 29/2011 ዓ.ም መያዙን ገለፀ። አራት ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል። የገቢዎች ሚኒስቴር ቶጎ ውጫሌ ኬላ ላይ ሰባት ኪሎ ግራም ወርቅና ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ሃገራት ገንዘብ መያዙን ገልጿል። የአሜሪካ፣ የካናዳና የአውስትራሊያ ዶላር፣ ዩሮ፣ ድርሃምና የሌሎች ሃገራት ገንዘብ ነው የተያዘው ብሏል ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ። ትናንት ምሽት ሰባት ኪሎ ግራም ወርቅና መጠኑ ከፍተኛ የሆነ የውጪ አገር ገንዘብ ከአራት ተጠርጣሪ ኮንትሮባንዲስቶች ጋር በቶጎ ዉጫሌ ኬላ በጉምሩክ ሰራተኞች ተይዟል። የተያዙት ከሚል ዑመር፣ መሃሪ አብዱ፣መሃዲ ዑመር እና ካልድ አብዲ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ናቸው፡፡ ዘጋቢ፦ ጋሻው ፈንታሁንና ራሔል ደምሰው (አብመድ) … [Read more...] about ከአገር ሊሸሽ የነበረ ሃብት ተያዘ
News
ክሱ “የተቀነባበረ ውሸት ነው” አብዲ ኢሌ
የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሐመድ የቀረበባቸው ክስ “የተቀነባበረ ውሸት ነው” አሉ። አቶ አብዲ ይህን ያሉት ጉዳያቸውን እየተመለከተ ላለው ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት ነው። ችሎቱ ለዛሬ ቀጠሮ ይዞ የነበረው አቶ አብዲን ጨምሮ በ47 ተጠርጣሪዎች ላይ የቀረበባቸውን ክስ በንባብ ለማሰማት ነበር። የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በይፋ ክስ የመሰረተው ባለፈው ረቡዕ ጥር 22 የነበረ ቢሆንም የተከሳሽ ጠበቆች በችሎት ባለመገኘታቸው የክስ ንባቡ ለዛሬ ተላልፏል። ጠቅላይ አቃቤ ህግ ተከሳሾቹ በሐምሌ 2010 ዓ. ም. በሶማሌ ክልል 59 ሰዎች እንዲገደሉ እና 412 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት እንዲወድም አድርገዋል በሚል ነው ክሱን ያቀረበው። በዛሬው የችሎት ውሎ ክሳቸውን ያደመጡት አቶ አብዲ ክሱን ተረድተውት እንደሆነ በመሐል ዳኛው … [Read more...] about ክሱ “የተቀነባበረ ውሸት ነው” አብዲ ኢሌ
ህወሓት በክህደት አከርካሪው ተመታ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) በማለት ራሱን የሚጠራው የበረሓ ወንበዴዎች ስብስብ አባል የነበረው ዛዲግ አብርሃ ከድርጅቱ አባልነት ለቋል። በህወሓት ታሪክ ዓይነተኛ ቦታ የሚሰጠው ይህ ክህደት ድርጅቱን ክፉና ጎድቶታል። ዛዲግን የሚከተሉ ይኖራሉ ተብሎ ይጠበቃል ተብሏል። በጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ ግንቦት 2፤ 2010 በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊ ሆኖ የተሾመው ዛዲግ አብርሃ የካቲት 5፤2011ዓም ከድርጅቱ መልቀቁን በጻፈው አምስት ገጽ ደብዳቤ ገልጾዋል። ከዚህኛው ሹመቱ በፊት ዛዲግ፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጦር እንዲዘምት ትዕዛዝ በሰጠው የጦር ወንጀለኛ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ዘመን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ኃላፊ የነበረው ነገሪ ሌንጮ ምክትል በመሆን ሠርቷል። ከዚያም በፊት “የሕዳሴ ግድብ” አስተባባሪ ኃላፊ ሆኖ መሥራቱ … [Read more...] about ህወሓት በክህደት አከርካሪው ተመታ
አወዛጋቢውና ባለጉዳዮች ያልመከሩበት የስደተኞች ሕግ ጉዳይ
የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ባለፈው ሳምንት ያፀደቀው “የስደተኞች አዋጅ” ከሚመለከታቸው ባለጉዳዮች ከፍተኛ ተቃውሞ እየደረሰበት ነው። በተለይ የስደተኛ ቁጥር በብዛት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የኅልውና ጥያቄ እንዳለባቸው ይናገራሉ። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችም ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። በፀደቀው አዋጅ መሠረት ማንኛውም ዕውቅና የተሰጠው ስደተኛ ወይም ጥገኝነት ጠያቂ፤ በመረጠው የአገሪቷ አካባቢ የመዘዋወር፣ የመኖሪያ ቤት የመመሥረት፣ መንጃ ፈቃድ የማውጣት፣ የመታወቂያና የውጪ ቪዛ (የጉዞ ሰነድ) የማግኘት፣ የባንክ ሂሳብ የመክፈትና ገንዘብ የማንቀሳቀስ፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ዜጎች ጋር ተዋህደው የመኖርና የኢትዮጵያን ዜግነት የመጠየቅ መብት ተሰጥቷቸዋል። አዋጁ ወደ ሥራ የመጣው Road map for the implementation of the Federal Democratic … [Read more...] about አወዛጋቢውና ባለጉዳዮች ያልመከሩበት የስደተኞች ሕግ ጉዳይ
“በማረፊያ ቤት ሰብዓዊ መብታች ተጥሷል”፤ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ በአግባቡና በሰዓቱ አይቀርብልንም – በረከትና ታደሰ
በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉት በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሣ “በማረፊያ ቤት ቆይታችን ሰብዓዊ መብታችንን እና ክብራችንን የሚነካ ድርጊት ተፈጽሞብናል” በማለት ለፍርድቤት ቅሬታ አቀረቡ። ጉዳያቸው በአዲስ አበባ እንዲታይ ለፍርድቤቱ ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ የአስራ አራት ቀን ቀጠሮ ሰጥቷል። በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ ጥር 17 ቀን 2011 ዓ.ም. በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ተጠርጣሪዎቹ ካለባቸው የጤና ችግር አንጻር በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ እንደሚመገቡ ገልጸው፤ ይሁንና በማረፊያ ቤቱ ምግብ በአግባቡ እና በሰዓቱ እንደማይቀርብላቸው ተናግረዋል። ለአብነትም ትናንት ምሳ በ10፡00 እንደቀረበላቸው ለችሎቱ አስረድተዋል። የኢኮኖሚ ችግር እንዳለባቸው እና ጡረታ በአግባቡ … [Read more...] about “በማረፊያ ቤት ሰብዓዊ መብታች ተጥሷል”፤ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ በአግባቡና በሰዓቱ አይቀርብልንም – በረከትና ታደሰ
“የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ
በኦሮሞ የባሕል ማዕከል ኦዴፓ ከኦነግ ጋር ስምምነት ባደረገበት ወቅት ዕርቀ ሰላሙን ከመሩት የአገር ሽማግሌዎች መካከል ኦቦ ኃይሌ ገብሬ እጅግ ጥልቅ ንግግር አድርገው ነበር። ይህ በአፋን ኦሮሞ እያለቀሱ የተናገሩት ልብ የሚነካ ንግግር ወደ አማርኛ ሲመለስ እንዲህ የሚል ነበር፤ “ዕርቀ-ሰላም በሚሆንበት ጊዜ እንዲሳካ ከብት ማረድ ካስፈለገ ገዝተን እናርዳለን፤ አይ ከብት አይደለም ሰው ይታረድልን የምትሉ ከሆነ ይኸው የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ”። ይህንን ዓይነት መስዋዕትነት የተከፈለበት ዕርቀ-ሰላም አንቀበልም የሚሉ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኃይሎች ለራሳቸው ሲሉ ከዚህ በኋላ ጥንቃቄ ቢያደርጉ መልካም ነው በማለት ስምምነቱን የተካፈሉ ይናገራሉ። የኦሮሞ ሕዝብ ከዚህ በኋላ ማንኛውንም ዓይነት ከፋፋይና ደም አፋሳሽ ተግባር መሸከም የሚችልበት ትከሻ የለውም። በኦሮሞ ስም … [Read more...] about “የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ
በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) በቁጥጥር ሥር ውለዋል
በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በተያያዘ በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ሥር የዋሉት። ዜናው በአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት የተዘገበ ሲሆን ከመኖሪያ ቤታቸው እንደተያዙ መረጃው ጨምሮ ገልጾዋል። ታደሰ ካሳ ጥረት ኮርፖሬትን በዋና ስራ አስፈፃሚነት ለበርካታ ዓመታት የመራ ሲሆን በረከት ስምኦን ደግሞ ከበርካታ የመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ቦታዎች ባሻገር የጥረት ኮርፖሬት የቦርድ ኃላፊ ሆኖ ሲመዘብር የነበረ ለመሆኑ ብዙዎች ይናገራሉ። ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) በቁጥጥር ሥር ውለዋል
አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ
ለጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ እና ግምቱ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ ከኅብረተሰብ በደረሰ ጥቆማ መያዙን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ “ትዕግስት ብሩክ ቶታል ማደያ” ውስጥ ጥር 12 ቀን 2011 ዓ/ም በ44 ጀሪካን 995 ሊትር ቤንዚን ከማደያው በመቅዳት ላይ እንዳሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል። የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተቀዳውን ከአስራአንድ ሺ ብር በላይ ዋጋ የሚያወጣ ቤንዚን እና ሌላ ሊቀዳበት የነበረ አርባ አራት ባዶ ጀሪካን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 አ/አ 29642 ከሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ሥር አውሏል። ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 5 ግለሰቦችም ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታውቋል። የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ … [Read more...] about አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ
በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው
በድርብ አኻዝ በከፍተኛ ፍጥነት ዕድገት ላይ ነች እየተባለ ሲደሰኮርባት በነበረችው አገር በቅርቡ ይፋ የተደረገ ጥናት እንደጠቆመው ሰላሣ ስድስት ሚሊየን የሚጠጉ ህፃናቶቿ ዘርፈብዙ በሆነ መልኩ ድሃ መሆናቸው ተነገረ። ይህም ማለት ህፃናቱ ለመኖር የሚያስፈልጓቸው መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንኳን ማግኘት ብርቅ ሆኖባቸዋል ነው ጥናቱ ያለው። በኢትዮጵያ ከ18 አመት በታች ከሆኑት ከ41 ሚሊየን ውስጥ 36 ሚሊዮኑ በድህነት ውስጥ እንዳሉ የስታቲስቲክ ኤጀንሲ እና ዩኒሴፍ ጥናት አስረድቷል። ጥናቱ በተለያዩ ዘጠኝ ክፍሎች ተለይቷል። ድህነቱ በዕድገት፣ በምግብ፣ በጤና፣ በውሃ፣ በንፅህና እና በመጠለያ ሲሆን ሌሎቹ የድህነት መለኪያ መስፈርቶች ደግሞ ትምህርት፣ ከጤና ጋር በተያያዘ በቂ ዕውቀት፣ መረጃና ተሳትፎን የሚጨምር ነው ተብሏል። በጥናቱ እንደተገለጸው 88 በመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው … [Read more...] about በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው
በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው
በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባባስ በሚያደርጉ ነዳጅ አቅራቢዎች እና አከፋፋዮች ላይ አስፈላጊውን ክትትል እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአገር አቀፍ ደረጃ በቂ ነዳጅ እያለ ነገር ግን በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባበስ በመደረጉ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያካተተ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ኢንጂነር ታከለ ኡማ የሚመራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ስራ መጀመሩ ይታወቃል። በከተማችን ነዳጅ ለማከፋፈል 120 ገደማ የሚሆኑ የነዳጅ ማደያዎች በሕግ አግባብ ፈቃድ መውሰዳቸው እየታወቀ 106ቱ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። ጥር 8 ቀን 2011 ዓ/ም በስራ ላይ ከሚገኙ 106 … [Read more...] about በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው










