• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Literature

ጀግና ውለጅ እባክሽ !

August 12, 2016 04:16 am by Editor Leave a Comment

ጀግና ውለጅ እባክሽ !

የምሁር መሃይም - ተባይ አላዋቂ፤ የመሃይም ኩፍስ - አስመሳይ አዋቂ፤ የጅብ ባለ ጊዜ - ታፋ መራጭ ከሽንጥ፤ ያንበሳ ልክስክስ - ልፋጭ የሚያላምጥ የቁራ ዕርግብ መሳይ - ሠላምን አብሳሪ፤ የፈረስ አዝጋሚ - የግመል ሰጋሪ፤ ንጹህ ሰው ታሳሪ - በፈጠራ ወንጀል፤ ፍርደ ገምድል ዳኛ - ፈራጅ በቂም በቀል፤ የባዕድ ባለቤት - የነባር ባይተዋር፤ ሥልጡን ሥራ ፈቶ - ሞያ ቢስ ሲገብር፤ ልማድ ሆኖ ቀረ - አቀርቅሮ መኖር፤ በተወሇድንባት በጦብያ ምድር :: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ጀግና ውለጅ እባክሽ !

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!

August 11, 2016 04:01 am by Editor 1 Comment

ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!

ይድረስ ለእኛ-ከእኛ! - ከላይ ልጀምር ካ’ናቱ፣ በብረት ኃይል ተከቦ - ከተኮፈሰው በከንቱ፣ ይድረስልኝማ ለወያኔ - ለጊዜያዊው ባለጉልበቱ፤ … “ለሕዝባዊነት መጣሁ” ብሎ - ሕዝብን በጥይት መቁላት የለምና፣ አቆልቁለህ እየውማ - የምትሄድበትን ጎዳና! የጭካኔ መጠንህ ጫፍ ደረሰ - የውሸት ቋትህ ሞላ፣ የ’እውቀት‘ ገደብህ አበቃ - ከእንግዲህ ላይኖርህ የቀረ ‘መላ’፣ ከወደቁ ወዲያ መንፈራገጥ.. እንዳይሆን ለመላላጥ፣ ሳሩንም ላለመጋጥ.. መሬቱንም ላለመናጥ…፣ ከአውሬነት ባህል ተላቆ - ሰውነትን ይሻልና፣ ይድረስ! ይድረስ! እልሃለሁ፤ ይድረስ! እንደገና፤ ዛሬ እንኳን እንደማመጥ - ይቅርብህማ ወንድሜ፣ በግፍ ተሞልተህ ጉዞ - ላይሆንህ መልካም ዕድሜ፣ “አበቅቴ ውሉን ሳይስት” - የአመሻሽ ጀንበር ሳትጠልቅብህ፣ ቆም ብለህ ማሰብ ጀምር - እንደ “ጆቤ”ህ፣ እንደ … [Read more...] about ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

አባተ መኩሪያ “ተንቀሳቃሹ ቴአትር ቤት” (1932 – 2008)

August 4, 2016 05:48 pm by Editor Leave a Comment

አባተ መኩሪያ “ተንቀሳቃሹ ቴአትር ቤት” (1932 – 2008)

‹‹ጥበበኛ በጥበብ እግር ይመላለሳል›› (ጠቢብ የሐውር በእግር ጥበብ) እንዲሉ፣ አባተ መኩሪያ ከግማሽ ምታመት በዘለለ በኢትዮጵያ ቴአትር ሕዋ ውስጥ በጥበብ ለጥበብ ኖሯል፡፡ ለቴአትር እስትንፋሱ ነበርም ይሉታል፡፡ በርሱ ጥበብ ያለፉት ሁሉ፡፡ በጥበብ የባተው አዘጋጅ፣ የውዝዋዜ አሠልጣኝ (ኬሪዮግራፈር)፣ ጸሐፌ ተውኔት፣ የፊልም አዘጋጅ የነበረው አባተ መኩሪያ በአገሪቱ የቴአትር ታሪክ ውስጥ ስማቸው በግዘፍ ከሚነሱትና አሻራቸውን ካሳረፉ በኩሮች አንዱ ነበር፡፡ በተለይ በተውኔት አዘጋጅነት ስመ ጥር ለመሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ተውኔቶችን ወጥ እና ትርጉሞች በማዘጋጀቱ ይጠቀሳል፡፡ ከታዋቂ ሥራዎቹ መካከል ሀሁ በስድስት ወር (1966) አቡጊዳ ቀይሶ (1971)፣ መልእክተ ወዛደር (1971)፣ የመንታ እናት (1971)፣ መቅድም (1972)፣ ጋሞ (1973)፣ አሉላ አባነጋ (1979) ይጠቀሳሉ፡፡ … [Read more...] about አባተ መኩሪያ “ተንቀሳቃሹ ቴአትር ቤት” (1932 – 2008)

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

“ሰው አይደለም ! …” አለኝ

July 2, 2016 07:07 am by Editor Leave a Comment

“ሰው አይደለም ! …” አለኝ

ገና ቁጭ እንዳልኩኝ ቀጥሮኝ እንዳገኘኝ እከሌ ጨርሶ «ሰው አይደለም!»  አለኝ ምነው? ምን አ’ረገህ ? «ሰው አይደለም!» ስልህ እኮ! ምን አ’ረገህ? «ሰው አይደለም!» አልኩህ። ቢራችንን አዘን በዝምታ ቆየን እንደገና ደግሞ ሳሉን እየሳለ አንገቱን ነቅንቆ «ሰው አይደለም!» አለ። ሰው ይመስላል አልኩኝ ስሜቱን ልረዳ ፊቱን መረመርኩኝ ባ’ይኑ እየገረፈኝ አይምሰልህ! አለኝ ግንባሩ ታጠፈ ጥርሶቹን ነከሰ ጠረጴዛ መታ፣ ቢራችን ፈሰሰ ልጠራርግ መጥታ -  ልጅት እያየችኝ በፊቷ ምልክት ምን ሆኗል? አለችኝ መዳፌን አሳየሁ፣ ከንፈሬን አስረዘምኩ እኔም ልክ እንደሷው በምልክት መለስኩ እሱ ግን ቀጠለ «ሰው አይደለም» ማለት «ሰው አይደለም!» አልኩኝ እኔም ተመቸሁት በቢራ ተራጨን በውስኪ ታጠብን ስሙን እያነሳን «ሰው አይደለም!» አልን። ልጅትም … [Read more...] about “ሰው አይደለም ! …” አለኝ

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

አባቱን ነገረኝ

June 22, 2016 08:22 am by Editor Leave a Comment

አባቱን ነገረኝ

በአባቱ ወንበር ላይ ሳሎን ተቀምጦ በባዶ ግድግዳ ተግ ብሎ አፋጦ የፊቱን ሁኔታ እየለዋወጠ ትካዜ ተጭኖት ቃላት እያማጠ ዓይኑን አጨንቁሮ እየመረመረኝ እንደዚህ እያለ አባቱን ነገረኝ አባቴ... አባባ ኤጭ! አለ ፊቱን አጨማዶ ሁሉን ነገር ጠልቷል ውስጡ ሆኗል ባዶ በምሬት ኮምትሯል ... በጥላቻ በግኗል ... አስሬ ኤጭ! ይላል አባባ ኤጭ! አለ እንደገና ደግሞ በሳሎኑ መሀል ተገትሮ ቆሞ እንደገና ደግሞ ቁጭ አለ አንገት ደፋ ካፍጫው አወጣ እምቅ አየር ተፋ ኤጭ! አለ እንደገና ተነሳና ቆመ ሽቅብ አንጋጠጠ ጣሪያው ላይ ቆዘመ የአባባን ንዴት ይቺን አላውቃትም ከወትሮው ተለየች ብዙ አልወደድኳትም አባባ አሳዘነኝ አዝኜም ፈራሁት ምን ሆንክ? አይባልም በንዲህ ያለ ንዴት አባባ ዓይኑ ቀላ ስሩ ተገተረ በአንድ ጊዜ አረጀ ሀያ ዓመት ጨመረ እንደዛ … [Read more...] about አባቱን ነገረኝ

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

አማኒ ኢብራሂም — “ያልታወቀው” የጥበብ ሰው!

June 20, 2016 05:26 am by Editor 1 Comment

አማኒ ኢብራሂም — “ያልታወቀው” የጥበብ ሰው!

“... ሰው እያለ አጠገባችን፣ ቅንነቱን ማየት ሲያመን ከኛው አብሮ በህይወት ቆሞ፣ መልካም ስሙን መጥራት ሲያንቀን፣ “ሰው ካልሞተ ወይ ካልሄደ አይነሳም” እንላለን። እንዲህ እያልን፣ ስንቱን ጠቢብ እየሸኘን፤ አበባውን ቀጥፈን ጥለን፣ አበባ እናስቀምጣለን!!” መቼም ያለ-ግጥም ፍቅር መኖር የሚሆንልኝ አይመስለኝም። ዛሬ ግን ብዕሬን ያነሳሁት ግጥም ለመጻፍ ባለመሆኑ፣ እነሆ ! የነብይ መኮንን የሆነችውን ይህቺን ግጥም፣ ለተነሳሁለት የጽሁፍ ጭብጥ እንደ መግቢያ ሆና ታግዘኝ ዘንድ ተዋስኩ። ገጣሚ ነብይ መኮንን ይህቺን የቁጭት ስሜት አስተናጋጅ የሆነች ግጥም በመታሰቢያነት ያበረከተው፣ ለእውቁ ሰዓሊና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ ነው። ያ! ድንቅ ኢትዮጵያዊ ሰዓሊና ገጣሚ ደግሞ በመጨረሻው የህይወት ዘመኑ፣ በስደት ባክኖ፣ በሰቀቀን ተጀቡኖ ያለፈው በአሜሪካ—ኦክላሆማ ግዛት ውስጥ … [Read more...] about አማኒ ኢብራሂም — “ያልታወቀው” የጥበብ ሰው!

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

አስርቱ አምባገነናዊ ትዛዛት!

June 14, 2016 04:17 am by Editor 2 Comments

አስርቱ አምባገነናዊ ትዛዛት!

"እኔ ስላንተ በበረሐ ደሜን አፍስሻለሁና ከእኔና ከአጋሮቼ በቀር ሌላ የፖለቲካ ፖርቲ በቃልህ አትስበክ በልብህም አትመን"፤ "መንግስት የኛ ናትና ወደ መንግስት አትመልከት ስልጣኑንም አትመኝ"፤ "የባለስልጣናትን ጥፋት ... የዜግነት መብቱንም በሶሻል ሚዲያ የተቸ እሱ ወዮለት፤ የባለስልጣን ሚስትም ቅምጥም ሃብትም የማይነኩ፤ የማይደፈሩ "ቅዱስ" ናቸውና ትንፍሽ እንዳትል!! ...." "ከደርግ ጨካኝ አገዛዝ አውጥቼሃለሁና... በፍፁም ልብህ በፍፁም ሃሳብህ ለእኔ ብቻ ተገዛ"፤ "ብሰርቅም፤ ባስርም፤ ብገድልም እንዳለየ እለፍ ... መብራት ቢጠፋ፤ ውሃ ቢቋረጥ ... አርፈህ ተቀመጥ"፤ "እኔ ልማታዊ መንግስትህ በስራዬ ፍፁም የማልሳሳት ነኝና በማስተዳድራት አገር ለሚደርስ ጥፋት ሁሉ የኤርትራን መንግስት ርገም"፤ "ከእኔ አርማ በስተቀር በሰማይ ይሁን በምድር እንዲሁም … [Read more...] about አስርቱ አምባገነናዊ ትዛዛት!

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

ስለቴክኖሎጂ ሊያነጋግር የከጀለ መጽሀፍ

June 1, 2016 02:34 am by Editor Leave a Comment

ስለቴክኖሎጂ ሊያነጋግር የከጀለ መጽሀፍ

የዛሬዋ ዓለማችን በደረሰችበት የእድገት ደረጃ ስልጣኔን ወይም ብልጽግናን ከቴክኖሎጂ ለይቶ ማየት ያስቸግራል። የሰለጠነ ህብረተሰብ ማለት ቴክኖሎጂን ያዳበረ ህብረተሰብ ማለት ነው። ባንጻሩም ቴክኖሎጂን ያላዳበረ ህብረተሰብ ማለት ደግሞ ያልበለጸገ ህብረተሰብ ነው። የሰለጠነ ህብረተሰብ ስንል ደግሞ ድኅነት የተረታበት፤ በሽታ የመነመንበት፤ ትምህርት የተስፋፋበት (እውቀት የለመለመበት)፤ ዲሞክራሲ የሰፈነበት፤ የመገናኛና ቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት በስፋት የተንሰራፋበትና ህግ የበላይ የሆነበት ህብረተሰብ ማለታችን ነው። ቴክኖሎጂ እላይ ለተጠቀሱት ለሰው ልጆች አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ አዎንታዊ የሆነ ቀጥተኛ አስተዋጽኦ አለው። ይሄን ሲይደርግ ግን ቴክኖሎጂ ከህብረተሰብ ውጪ ሆኖ በታዓምር ወይም ትእዛዝ በመስጠት ሳይሆን በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች የሚተገብሩት፤ ሌሎች የህብረተሰብ … [Read more...] about ስለቴክኖሎጂ ሊያነጋግር የከጀለ መጽሀፍ

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

ልዩ ጥበብ ገንባ

May 25, 2016 12:53 am by Editor Leave a Comment

ልዩ ጥበብ ገንባ

ፍቅር ታሞ ከርሞ አልጋ ላይ እንደሰው ብዙ ዘመን ሆነ ሞቶ ከቀበርነው ይሄ ሆኖ እያለ ሞቱን እያወቅን ለአያሌ ዓመታት ዘፋኞች በዘፈን አሁንም እንዳለ ህይወት እስትንፋሱ ጨርሶ እንዳልሞተ እንዳልወጣች ነፍሱ አድርገው ሲዘፍኑ ሲያቀብሉን ውሸት ነገሩን ዋጥ አድርገን አብረን ጨፈርንበት ከሁሉ ‘ሚገርመው የሚደንቀው ነገር አለ የሚባለው የአሁን ዘመን ፍቅር ገንዘብን ውሃልክ አ’ርጎ ተመስርቶ በዓይናችን እያየን መካካዱ ከፍቶ ዘፋኙ ተነስቶ ሲለን ፍቅር ፍቅር በሆታ በስክስታ የኛ አብሮ ማጫፈር ከ «እማትበላ ወፍ»«እዘበናኝ» ድረስ ሆዴ አንጀቴ እያለ ተሸክሞ እንደ ውርስ ወጣቱም ያንኑ ሲያማስል ሲያቁላላ ስለከረመበት ሳይቀይር በሌላ ያወጣው ሙዚቃ ሳይሰማ ጣፍጦ ዘፈኑ ይሞታል ዘፋኙ ተቀምጦ ይህ ሁሉ ሲሰራ ይህ ሁሉ ሲፈጠር እስከዛሬ ቆየን ምንም … [Read more...] about ልዩ ጥበብ ገንባ

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

እግርና ጫማ

May 17, 2016 05:53 am by Editor Leave a Comment

እግርና ጫማ

እግርና ጫማ ተጣብቀው አንድ ላይ በክር ተሳስረው አብረው ውለው ስታይ እውነት አይምሰልህ ያ ሁሉ ፍቅራቸው ሲመሽ ወደማታ ሄደህ ብታያቸው በአንሶላ መካከል እግር ተዘርግቶ ጫማ በራፉ ላይ ወድቋል አፉን ከፍቶ! … [Read more...] about እግርና ጫማ

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

  • « Previous Page
  • Page 1
  • …
  • Page 6
  • Page 7
  • Page 8
  • Page 9
  • Page 10
  • …
  • Page 27
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule