• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አባቱን ነገረኝ

June 22, 2016 08:22 am by Editor Leave a Comment

በአባቱ ወንበር ላይ ሳሎን ተቀምጦ
በባዶ ግድግዳ ተግ ብሎ አፋጦ
የፊቱን ሁኔታ እየለዋወጠ
ትካዜ ተጭኖት ቃላት እያማጠ
ዓይኑን አጨንቁሮ እየመረመረኝ
እንደዚህ እያለ አባቱን ነገረኝ

አባቴ…
አባባ ኤጭ! አለ ፊቱን አጨማዶ
ሁሉን ነገር ጠልቷል ውስጡ ሆኗል ባዶ
በምሬት ኮምትሯል …
በጥላቻ በግኗል …
አስሬ ኤጭ! ይላል
አባባ ኤጭ! አለ እንደገና ደግሞ
በሳሎኑ መሀል ተገትሮ ቆሞ
እንደገና ደግሞ ቁጭ አለ አንገት ደፋ
ካፍጫው አወጣ እምቅ አየር ተፋ
ኤጭ! አለ እንደገና ተነሳና ቆመ
ሽቅብ አንጋጠጠ ጣሪያው ላይ ቆዘመ

የአባባን ንዴት ይቺን አላውቃትም
ከወትሮው ተለየች ብዙ አልወደድኳትም
አባባ አሳዘነኝ አዝኜም ፈራሁት
ምን ሆንክ? አይባልም በንዲህ ያለ ንዴት

አባባ ዓይኑ ቀላ ስሩ ተገተረ
በአንድ ጊዜ አረጀ ሀያ ዓመት ጨመረ
እንደዛ ሆነብኝ
አባባ አሳዘነኝ
አዝኜ ዝም አልኩት
ከድሮው ጨምሬ ደርቤ ፈራሁት
አባባ ምን ነካው …?
እንዴት ልጠይቀው ?
ዓይን ዓይኑን እያየሁ
ብዙ ተቀመጥኩኝ በዝምታ ቆየሁ

ሲመሽ ወደ ማታ ልሄድ ተነሳሁኝ
ዝምታዬን ላፈርጥ ከቤቱ ወጣሁኝ
ዝምታን አፈረጥኩ …
አባባን ረሳሁ መልካም ቀኔን አደስኩ
ቢራን የፈጠረ – ይመቸው ተባለ
ተበላ ተጠጣ ጨዋታ ቀጠለ
በጨዋታ ፈካሁ
በቢራው ወረዛሁ
እስከ ፍጥርጥሩ ሁሉንም ረሳሁ
ቢራው አበቃና አልኮል ተጀመረ
አገር ቀውጢ ሆነች ለጉድ ተጨፈረ
እኩለ ለሊት ላይ መጠጥ እያገሳሁ
ዝምታን ደፍጥጨ ሁሉን እንደረሳሁ
ስካሬን አዝዬ እቤቴ ስመለስ
ከሳሎን ገብቼ መብራቱን ስለኩስ

አባባ ጉድ ሰራኝ ኤጭ! እንዳለ ሄዷል
የጠላትን ሕይወት ጥሏት ተሰናብቷል
አባቴን ጠየኩት
ምነው? አባባ አልኩት
በሕይወት ፈርቼ በሞቱ ደፈርኩት
እያለ አወራልኝ
አባቱን ነገረኝ

ሀዘኑ በረታ ጓደኛዬ ከፋው
አይኖቹ ወረዙ እንባ ፊቱን ሞላው
ምነው ባልወጣሁኝ ባልሄድኩኝ  እያለ
አባቱን አስታውሶ በቁጭት ከሰለ
እንዴት አይዞህ ልበል ፍራት ፍራት አለኝ
መልኩ ተለወጠ አባቱን መሰለኝ
ኤጭ! አለ እንደ አባቱ  ኤጭታውን ጠላሁ
አሳዘነኝ ጓዴ አዝኔ አይዞህ ፈራሁ
እንደገና ቆመ አጨማዶ ፊቱን
ይንጎራደድ ጀመር ዙርያውን የቤቱን
ልክ እንደነገረኝ
ልክ እንዳወራልኝ
በሁሉም ነገሩ አባቱን ቢመስለኝ
ትቼው መሄድ ፈራሁ – ማደሩም ቀፈፈኝ።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule