እስከመቼ እውነቱ ሳይወጣ ሊቀር ነው? ሆዱ እያረረ በብዙው ዘንድ መወለድ አቅቶት የሚጉላላው እውነት ምንድን ነው? አዎ! "እያንዳንዱን የዛሬውን የኢትየጵያ ሃገር ወዳድ ሊያሳስበው ብቻ ሳይሆን፣ ራሱን አስይዞ የሃሳብ ያለህ አሰኝቶ ሊያስጮኽው የሚገባው“፣ አፍጥጦ የመጣው አደጋ ምንድን ነው? እውነቱ ነገ ዛሬ ሳይባል ባደባባይ ተሰምቶ የእርቅ ዘመን ካልወረደ ፣ ከገባንበት ጭቃ ሳንወጣ ክፉዎች የደገሱልን ማጥ ውስጥ ሰጥመን እንቀራለን። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ለ ሃገር ሰው፣ የ“መድሃነ፥ኢትዮጵያ” ደወል፣ እውነቱም ይሰማ!
“የሰከነው ትግል” በጋንዲ ምድር ተዘራ
“መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው” የንግግሩ መግቢያ ነበር። “በጨለማ ውስጥ ነን። ከፍተኛ በደል እየተፈጸመብን ነው። ለመረጃ ሩቅ የሆኑ ሰዎች፣ የስልጣኔ ጮራ ያልበራላቸው ሰዎች፣ የመማር ዕድል ያላቸኙ ሰዎች፣ ግፍ እየተፈጸማባቸው ነው። መብታቸውና ሰብዓዊ ክብራቸው ተረግጧል። በጉልበት መሬታቸው እየተነጠቀ በልማት ስም እየተሸጠ ነው። ይህ ሁሉ የሚደረገው በህንድ ህዝብና መንግሥት ስም ነው። ይህ አሳዛኝ ተግባር በስማችሁ እየተከናወነ ነው። በናንተ ስም። ተቃወሙ። ታገሉ። አግዙን። ለዚህ ነው መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው የምለው” ይህ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ንግግርና የትግል ጥሪ የቀረበው ህንድ ታዋቂው በሆነው ጃዋሃርላል ኔህሩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፊትለፊት ነበር። “ትግል አርቆ ማሰብ ይጠይቃል፤ እቅድ ይፈልጋል። ትግል ህዝብን ማስተባበርና የረዥም ጊዜ … [Read more...] about “የሰከነው ትግል” በጋንዲ ምድር ተዘራ
እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ?
መለስ የሚሌኒየም ንግሥ እለት ተገኝተው ዘፈን ምረጡ ሲባሉ “የሱዳን ዘፈን ይሁንልኝ” ብለው ከባለቤታቸው ጋር የተምነሸነሹበት የሚሌኒየም አዳራሽ በአቶ አሊ አብዶ የከንቲባነት ዘመን ለመስጊድ ማሰሪያ ተጠይቆ እንደነበር ፣ አቶ አሊም ቦታውን ለተጠየቀው ዓላማ እንዲውል መፍቀዳቸውንና ውሳኔው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ኢህአዴግ ዘንድ መረጃው ደርሶ መታገዱን ውስጥ አዋቂዎች ያስታውሳሉ። ከምርጫ 97 በኋላ ደግሞ መላ ሰውነታቸውን የተሸፋፈኑ ሙስሊሞች እየበዙ በመሆኑ ጉዳዩ ሥር ሳይሰድ፣ ከጀርባው እነማን እንዳሉበት ክትትል እንዲደረግ በታዘዘው መስረት የብሔራዊ የመረጃና የደህንነት አገልግሎት አስገራሚ ሪፖርት አቅርቦ እንደነበር እነዚሁ ክፍሎች ይናገራሉ። በክትትሉ የተገኘው መረጃና የመጨረሻ ድምዳሜ ተሸፋፍነው የሚለብሱት እህቶች አብዛኞቹ ሴተኛ አዳሪዎችና የገንዘብ ችግር ያለባቸው የሌላ ሃይማኖት … [Read more...] about እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ?
Indian investors are forcing Ethiopians off their land
Ethiopia's leasing of 600,000 hectares (1.5 acres) of prime farmland to Indian companies has led to intimidation, repression, detentions, rapes, beatings, environmental destruction, and the imprisonment of journalists and political objectors, according to a new report. Research by the US-based Oakland Institute suggests many thousands of Ethiopians are in the process of being relocated or have fled to neighbouring countries after their traditional land has been handed to foreign investors … [Read more...] about Indian investors are forcing Ethiopians off their land
ልዩነት አያስፈራም
ባለፉት 21 ዓመታት በልዩነት ላይ የተመሰረተው፣ ኢትዮጵያ ውስጥ የተነዛው የዘረኝነት መርዝ ቀላል አይደለም። መላ ኢትዮጵያን ቀስ በቀስ እየወረረው መጥቶ ማሰብ ይችላል ተብሎ የሚጠበቅበትን፣ ጥቂት ያልሆነ "ምሁር" የሚባለውን ሁሉ ሳይቀር በነጻ ጭንቅላት እንዳያስብ እያደረገው ነው። ሰለሆነም ነው፣ ማሰብ የሚገባው እንደዚህ ካሰባ፣ የፖለቲካና የስለላ ማዕከሎች ጥናቶች፣ አልፈው ተርፈው ረዥም ታሪክ ያላትን ኢትዮጵያ ሃገራችንን ከእንግዲህ በሃያ ዓመታት ውስጥ ከሚወድቁት መንግስታት ተርታ ውስጥ ያስገቧት። ይህ መቼም፣ ሆነም አልሆነም፣ እራሱ መገመቱ እንኳን፣ እያንዳንዱን የዛሬውን የኢትየጵያ ሃገር ወዳድ ሊያሳስበው ብቻ ሳይሆን፣ ራሱን አስይዞ የሃሳብ ያለህ አሰኝቶ ሊያስጮኽው ይገባል። ደግሞም የመንግሥትንና የአባሪዋቹን ታሪካዊ አካሄድና ዛሬ የሚወስዱትን ኢትዮጵያን የማፈራረስ እርምጃዎች … [Read more...] about ልዩነት አያስፈራም
የጎልጉል ቅምሻ
ሐላል ምግብ ውስጥ የአሳማ፤ በርገር ሥጋ ውስጥ ደግሞ የፈረስ ዲኤንኤ ተገኘ በእንግሊዝ አገር ለእስረኞች ሐላል ምግቦችን የሚያቀርቡ ድርጅቶች (ቸርቻሪዎች) በሚያቀርቡት ሥጋም ሆነ የጣፋጭ ምግብ ውጤቶች ውስጥ የአሳማ ሥጋ (ዲኤንኤ) እንደሚገኝ ከታወቀ ወዲህ በርካታዎቹ ለእስርቤቶቹ ምግብ ማቅረባቸውን እንዲቋረጥ የፍትህ ሚ/ር አዝዟል፡፡ በበርካታ አገራት የፈጣን ምግብ አቅራቢ እንደሆነ የሚታወቅ በርገር ኪንግ በሚሸጠው የበርገር ሥጋ ውስጥ የፈረስ ዲኤንኤ እንደሚገኝ ባለፈው ሐሙስ አምኗል፡፡ የአሳማ ሥጋ መገኘቱ ከታወቀ ወዲህ በርካታ ሙስሊም እስረኞች ተቃውሟቸውን እየገለጹ ሲሆን የፍትህ ሚ/ር በአቅራቢዎቹ ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ቃል ሰጥቷል፡፡ በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ሐዘን የተሰማቸው ሙስሊም አስተያየት ሰጪዎች ጉዳዩ ሆን ተብሎ የተደረገ ጉዳይ በመሆኑ ሙስሊሙ ኅብረተሰብ በሙሉ በአንድ … [Read more...] about የጎልጉል ቅምሻ
The dilemma of adopting ethnic federal system in Africa: Ethiopian experience
This article aims to analyse the major challenges of adopting ethnic federal system in Africa with special focus on the context of Ethiopia’s ethnic federal system. It is argued that though the adoption of ethnic federal system in Ethiopia has created the opportunity for minority groups to exercise their cultural and linguistic rights, the ethnic federal experiment has faced enormous challenges. The challenges include problems of legitimacy, unprecedented emphasis on ethnicity and lack of … [Read more...] about The dilemma of adopting ethnic federal system in Africa: Ethiopian experience
ከእሁድ እስከ እሁድ
ማክሰኞ ኢቲቪ ድግስ አለበት “ክርስቲያኖችም ሙስሊሞችም ልባችሁን ጠብቁ” “እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ” የማስታወቂያው ፍንጣሪ ሃረግ ነው። በአብዛኛው የማህበራዊ ድረገጾች አስቀድመው የሚያስተላልፉት መልዕክት ደግሞ “ክርስቲያኑም ሙስሊሙም ልባችሁን ጠብቁ የሚል” ነው። ኢቲቪ ድግስ አለኝ ሲል ለማክሰኞ ቀጠሮ የያዘለት ዘጋቢ ፊልም አክራሪነት ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነ ቀደም ብሎ የተሰራጨው ማስታወቂያ ያስረዳል። ከኢህአዴግ አፈጣጠርና የፕሮፓጋንዳ ልምዱ በመነሳት ለማክሰኞ በቀጠሮ የተዘጋጀውን ዘጋቢ ፊልም “አኬልዳማ ቁጥር ሁለት” በሚል ብዙዎች ሰይመውታል። አንዳንዶች ደግሞ “አዳዲስ ሆዳሞችን እንተዋወቃለን” ሲሉ ፊልሙ በደህንነት ሃይሎች የተቀነባበረ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው ይገልጻሉ። “የውሸት አባት ኢህአዴግና ወዲ ስምዖን የቆመሩት ቁማር” ሲሉ የሚገልጹትም ጥቂት … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
የሚድሮክ ልዑክ ለአባዱላ ያቀረቡት ጥያቄ
የሚድሮክ ኢትዮጵያ የበላይ አመራሮች አባዱላ ገመዳን ለማነጋገር ቀጠሮ አስይዘው የተወሰኑ ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀው እንደነበር የጎልጉል ምንጮች አስታወቁ። በኦሮሚያ የሚገኙ የሼኽ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ንብረት የተባሉ ድርጅቶች ላይ የተደረጉ የሂሳብ ምርመራዎችና ግብር ታሪፍ የተሰራባቸው ሰነዶች ዝርፊያ ምርመራ ተድበስብሶ እንዲታፈን መደረጉ እስካሁን ምላሽ ያላገኘ ጉዳይ እንደሆነ ተጠቆመ። አባዱላ ገመዳ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ሚድሮክ የሰየማቸውና በዶ/ር አረጋ የሚመራ ልዑክ ቢሯቸው የተገኘው በወቅቱ የሼክ መሀመድ ድርጅቶች ላይ ክልሉ ግብር እንዲከፍሉ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነበር። የክልሉ ካቢኔ ግብር መክፈል የሚገባቸው ባለሃብቶች በሙሉ ሊከፍሉ የሚገባቸውን ውዝፍ እዳ ገቢ እንዲያደርጉ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ክልሉ ውስጥ … [Read more...] about የሚድሮክ ልዑክ ለአባዱላ ያቀረቡት ጥያቄ
በደመ ነፍስ የምትነዳ ሀገር
አንድ ምራቅ መዋጥ የጀመረ የ28 ዓመት ወጣት የኑሮ አጉራ ቢጠናው ጊዜ ወደ ጠንቋይ ቤተ ይሄዳል፡፡ ለአጋፋሪው ሣንቲም ቢቴ ቦጨቅ ያደርግና ወረፋውን አፋጥኖ በተሎ ይደርሰዋል፡፡ በሁሉም ቦታ መቼም ይቺ ሙስና ተንሰራፍታለችና በዚህ አይግረማችሁ፡፡ ሀገራችን በተለይ በዚህ አንደኛ ሳትሆን የምትቀር አይመስለኝም፡፡ ጠንቋይ፤ ምን ፈልገህ መጣህ? አውሊያው ምን እንዲያደርግልህ ትፈልጋለህ አንተ ብላቴና? አስጠንቋይ፤ የኑሮ ችር ነው ወደዚህ ያመጣኝ፡፡ ሕይወቴ ልፋት ብቻ ሆነ፤ ቀን ከሌት ብለፋ ድካም እንጂ ውጤት የለም፡፡ ጓደኞቼ የትና የት ሲደርሱ እኔ በድህነት እየማቀቅሁ ቀረሁ፡፡… ጠንቋይ፤ አይዞህ፤ ገና ወጣት እኮ ነህ፡፡ ተስፋ አትቁረጥ… አስጠንቋይ፤ እሺ! በርስዎው መጀን አባቴ፡፡ ያለርስዎ ማን አለኝ፡፡ እስካሁንም ወደርስዎ ያልመጣሁት … [Read more...] about በደመ ነፍስ የምትነዳ ሀገር









