ሚዲያ ከስሜታዊነት፣ ከስጋና ደም ድምር፣ ከችኩል ውሳኔና ግብታዊነት ነጻ ለመሆን ሌት ተቀን መስራት እንዳለበት ባለሙያዎች አበክረው የሚናገሩት ዓቢይ ጉዳይ ነው። ሚዲያ ስንል ደግሞ ሁሉንም ነው - የኅትመት፣ የምስል፣ የድምጽ፣ የድረገጽ፣ የዲጂታል፣ የማኅበራዊ ድረገጽ፣ … ። ሁሉም ሚዲያዎች አሻግሮ በማየት ህዝብንና አገርን የመጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው። ጋዜጠኞች ወይም እንደ ጋዜጠኛ የሚሠሩ ሁሉ ከየትኛውም ሙያተኛ በላይ ሃላፊነት ሊሰማቸውም ግድ ነው። ለዚህም ነው በጋዜጠኝነት ሙያ "አመጣጥን፣ አሁንም አመጣጥን፣ አሁንም አመጣጥን … “ባላንስ” አድርግ" የሚባለው!! ከኢህአዴግ ዓይነ ያወጣ ውሸትና ዝግነት የተነሳ ሁሉንም መረጃዎች የማመጣጠኑ ሙያዊ ሃላፊነት ለመወጣት ፈተና ቢያጋጥምም በከፍተኛ ደረጃ ጥንቃቄ ልንወስድባቸው የሚገባን ጉዳዮች አሉ። ከነዚህ ጉዳዮች መካከል አንዱና ዋናው … [Read more...] about ኢህአዴግ ሌላ፤ ኢትዮጵያችን ሌላ!!
“ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
/ዜና ጎልጉል/ ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት "የአስተዋይነት" ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል። ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል። በኢህአዴግ ላይ የቀረበው ሪፖርት የመፍትሄ ሃሳብም ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት … [Read more...] about “ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
፪ኛው ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ
በኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል (ኢሴመማ) ፪ኛው ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ በዲያስፖራ የጉባኤው ቀዳሚ ቃል “የኢትዮጵያ ሴቶች በደል ማብቃት አለበት” ቅዳሜ መጋቢት ፲ ፮ ቀን ፳፻፭ዓም በዋሽንግተን ዲሲ 2nd ANNUAL INTERNATIONAL ETHIOPIAN WOMEN CONFERENCE IN THE DIASPORA Washington Marriott Hotel 1221 22nd Street, Washington, DC 20037 March 23, 2013 9 AM TO 5 PM … [Read more...] about ፪ኛው ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ሴቶች ጉባኤ
Immediate Press Release: Center for Rights of Ethiopian Women
February 14, 2013 The Center for the Rights of Ethiopian Women (CREW) appreciates Ethiopian Sport Federation of North America (ESFNA) for its decision to uphold the theme of “Celebrating Ethiopian Women” at its 30th year anniversary. Ethiopian women are known worldwide for their cultural diversity and beauty; but for far too long, their intelligence, tenacity, achievements as well as the tremendous hardships they face have not been part of the social dialogue adequately. Their heroic … [Read more...] about Immediate Press Release: Center for Rights of Ethiopian Women
ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ
እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ ሀገርንና ትውልድን የሚያጠፋ እኩይ አመለካከትና ምግባር ይዞ ተነስቶና ተሳክቶለትም የሚገዛ ከኢትዮጵያ ውጭ በአለም ላይ ያለ ሀገርም ሆነ የሚገዛ ህዝብ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግ የገዛ ወገኑንና ሀገሩን በጠላትነት ፈርጆ፣ ታጥቆና ተደራጅቶ የሚወጋና የሚያፈራርስ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ አገዛዝም ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊንን የማጥፋቱንና የመበታተኑን ምግባር እንዲያቆም እሽሩሩ የተባለና እየተለመነ ያለ የለም።..... በልመና ቢሆን..... ፍትህ - እኩልነት በልመና ቢሆን... ነጻነት - አንድነት በልመና ቢሆን.... ሰላምና ሕይወት፤ እመጣ ነበረ- አንች ካለሽበት ትመጭልኝ ነበር - እኔ ካለሁበት ዓለም ይሆን ነበር፣ የሁላችንም ቤት። እንደ ደርግ ያለ አምባገነን መንግስት ሀገሩን በክህደትና በጥላቻ ለተሞሉ፤ እንደ ሻአቢያዊንና እንደ … [Read more...] about ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ
በአልቃይዳ ሰበብ ቻይናን መቆጣጠር
የአገራቸውን አጠቃላይ ሁኔታ እና መጪው ጊዜ ምን እንደሚመስል፤ የአገራቸውን የወደፊት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ … ሁኔታ እንዲሁም አሜሪካ በቀጣይ ዓመታት የምትከተለውን የአጭርና የረጅም ጊዜ የውጪ ፖሊሲ ዕቅድ በተመለከተ ለሁለተኛ ጊዜ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ማክሰኞ ምሽት ለምክርቤቱ ንግግር ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኦባማ በርካታ ጉዳዮችን ዳስሰዋል፡፡ አፍሪካና ቻይናም የንግግራቸውን ሙሉ ቀልብ የሳቡ ነበሩ ባይባልም ሳይጠቀሱ አልታለፉም፡፡ በተለይ ስለአፍሪካ እንዲህ ብለዋል፤- ‹‹… የተለያዩ አፍቃሪ የአልቃይዳ ወኪሎችና አክራሪዎች ከአረብ ምድር እስከ አፍሪካ ብቅ እያሉ መጥተዋል፤ እነዚህ ቡድኖች ሊያመጡ የሚችሉት አደጋ እንደዚያው እያደገ መጥቷል፡፡ ይህንን አደጋ ለመቋቋምም በአስር ሺዎች የሚጠጉ ልጆቻችንን በመላክም ሆነ አገራትን መቆጣጠር አያስፈልገንም፡፡ ይልቁንም … [Read more...] about በአልቃይዳ ሰበብ ቻይናን መቆጣጠር
እንደ ሻማ
አንደ ሻማ ነው ማንባት፣ ቀልጦ ጠብ እንደሚለው፤ የነፍሳችንን ስቃይ፣ ይሉኝታ ሳይጋርደው፤ ማስመሰል ሳያርቀው፡፡ እንደ ሻማ ነው መቅለጥ፣ በነበልባል ነዶ በግኖ፤ ሰብእናን በህይወት ጣር፣ ሰርቶ በማደር ፈትኖ፡፡ እንደ ሻማ ነው መብራት፣ ማለቅም እንደ ሻማ፤ ለሌላም ባይሆን ለነፍስ፣ አብርቶ የእውነትን ፋና፡፡ በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) ፣ /ፍካት ናፋቂዎች፤1999ዓ.ም/ ባለፈው ሁለት ግጥሞችን አቅርበን ነበር፡፡ “ቅኔ” እና “የማይጠፋ ፍቅር” በሚል ርዕሶች ለቀረቡት ግጥሞች ጨዋታውን በማድመቅ የተቀኛችሁትን እና ማብራሪያም የሰጣችሁትን ተሳታፊዎቻችንን በለው፤ YeKanadaw Kebede፤ አሥረዳው፤ እስከመቼ እና ዱባለ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡ ለዛሬው ደግሞ በግጥም ልተንፍሥ ከተባለ የፌስቡክ ገጽ ይህንን ግጥም አግኝተን ለጨዋታ አቅርበነዋል፡፡ “እንደ … [Read more...] about እንደ ሻማ
ለቅሶ ሳቅ – ሳቅ ለቅሶ
አቅቶን መለወጥ ለቅሶን በደስታ፤ ሃዘን ጠል አልብሶን ሳቅ ደርቦ ኩታ፤ ያንዱን ቤት ገንብቶ የሌላውን ሲያፈርስ፤ አንዱን ሳቅ አጅቦት ሌላው ከፍቶት ሲያለቅስ፤ ለቅሶ ሳቅ - ሳቅ ለቅሶ - እየደባለቀ፤ ግማሽ ጎኑ ሲያለቅስ - ግማሽ ጎኑ ሳቀ:: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ለቅሶ ሳቅ – ሳቅ ለቅሶ
ከእሁድ እስከ እሁድ
“ኢትዮጵያን ቀስ ብለን ስሟን እንቀይራለን” Ethio Muslims Interfaith Dialogue for Justice በሚል ስያሜ በሚታወቀው የፓልቶክ ክፍል ውስጥ "አቡ ሃይደር" በሚል ቅጽል ስም የሚታወቁት ተናጋሪን በመጥቀስና ንግግራቸውን በቀጥታ በማሰማት የሙስሊሞች እንቅሰቃሴ የመጨረሻ ዓላማ ኢትዮጵያን የሙስሊም መንግስት ማድግ እንደሆነ በEthio Christians and Muslims discussion 4 solution የፓልቶክ ክፍል "ዘ ቤስት ሶሉሺን" በሚል የቅጽል መጠሪያ የሚታወቁት ተናጋሪ አስታወቁ። የአቡሃይደርን ንግግር በተደጋጋሚ በድምጽ ማስረጃነት ሲቀርብ ኢትዮጵያን የእስላማዊ መንግስት ከማድረግ ባሻገር አስፈላጊ ከሆነ መጠሪያ ስሟን እንደሚቀይሩ ሲናገሩ ተደምጧል። "አገሪቱ የእኛ ናት። ካፊሮች አገሪቱ የኛ ናት የሚል የታሪክ ምስክር ያላቸውም" ሲሉ የተናገሩትን … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
የ“ጃሃዳዊ ሐረካት” ዘጋቢ ፊልም መዘዝ!
"ጀሃዳዊ ሐረካት" ዘጋቢ ፊልም "በኢትዮጵያ እስላማዊ መንግስት ለመመስረት ከሃሳብ ያለፈ እቅድ አላቸው" የተባሉት ተጠርጣሪ አሸባሪዎችን ገመና አንጠርጥሮ ሊያሳየን መሆኑን ሞቀ ደመቅ ደመቅመቅ ያለው የኢቲቪ ማስታወቂያ ልባችን አንጠልጥሎት ከርሟል ። ሳምንት በደመጽና በምስል በለፈፉትና በናኙት ማስታወቂያ የሙሰሊማን የመፍትሄ አፈላላጊ ኰሚቴ አባላት "አሸባሪ" አካሄድ በተጨባጭ መረጃ እንደሚያሳዩን የነገሩን የመንግሰት መገናኛ ብዙሃንን የተለመደ ስራ የማውቀው ሳይቀር ነፈሴ በአንገቴ እሰክትወጣ ጉጉት አሳድሮብኛል። ይህ መሰሉ ስሜት ለጊዜው ምንጩ ከየት እንደሆነ ባውቀውም ስሜቴን ተቆጣጥሬ በሰአቱ ደረስኩ፡፡ ተመሳሳይ ስሜት አድሮባቸው እንደሁ በሚል እዚህ ሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውንን እየደወልኩ ስሜታቸውን መጠየቅ ያዝኩ! (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል):: ጸሐፊውን በዚህ አድራሻ ማግኘት … [Read more...] about የ“ጃሃዳዊ ሐረካት” ዘጋቢ ፊልም መዘዝ!









