• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እንደ ሻማ

February 13, 2013 07:06 am by Editor 3 Comments

አንደ ሻማ ነው ማንባት፣
ቀልጦ ጠብ እንደሚለው፤
የነፍሳችንን ስቃይ፣
ይሉኝታ ሳይጋርደው፤
ማስመሰል ሳያርቀው፡፡

እንደ ሻማ ነው መቅለጥ፣
በነበልባል ነዶ በግኖ፤
ሰብእናን በህይወት ጣር፣
ሰርቶ በማደር ፈትኖ፡፡

እንደ ሻማ ነው መብራት፣
ማለቅም እንደ ሻማ፤
ለሌላም ባይሆን ለነፍስ፣
አብርቶ የእውነትን ፋና፡፡

በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) ፣ /ፍካት ናፋቂዎች፤1999ዓ.ም/

ባለፈው ሁለት ግጥሞችን አቅርበን ነበር፡፡ “ቅኔ” እና “የማይጠፋ ፍቅር” በሚል ርዕሶች ለቀረቡት ግጥሞች ጨዋታውን በማድመቅ የተቀኛችሁትን እና ማብራሪያም የሰጣችሁትን ተሳታፊዎቻችንን በለው፤ YeKanadaw Kebede፤ አሥረዳው፤ እስከመቼ እና ዱባለ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡

ለዛሬው ደግሞ በግጥም ልተንፍሥ ከተባለ የፌስቡክ ገጽ ይህንን ግጥም አግኝተን ለጨዋታ አቅርበነዋል፡፡ “እንደ ሻማ”ን እነሆ! ተቀኙበት፤ ቅኔ ዝረፉበት፤ …

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    February 12, 2013 11:29 pm at 11:29 pm

    *************************
    አይ አንቺ ‘ሻማ’ እራስሽን መስዕዋት ያደረገሽ
    መብራት በጠፋ ቀን ሁሉ የሚያበሩሽ
    እነሱ ሲደሰቱ አንቺን እየለኮሱሽ
    ሀዘንም ሲገጥማቸው አንችው ተቃጥለሽ
    ከቶ ማነው አንቺ ቀልጠሽ! አንብተሽ!
    ለሌላውን ብርሃን ሁኚ ብሎ የፈረደብሽ ?
    ***ሻማ !
    ምን ነበር ታዲያ ከአንቺ የሰው ልጅ ቢማር
    ውጭ ሄዶ ከሚቀልጥ ከሚያነባ ከሚማረር
    እንዳይሆን የጋን መብራት እንዳይጠፋ ሳያስተምር
    እንደሻማ ተለኩሶ በርቶ እየታየ ለህዝብ ቢናገር
    ስንት የጨለመባቸው ፍንትው ብሎ በታያቸው ነበር !!።
    *****************
    ከምስጋና ጋር፣ ከሀገረ ካናዳ በለው!

    Reply
    • ቱሉ ፎርሳ (ከነምሳ) says

      February 14, 2013 01:38 am at 1:38 am

      “እንደ ሴቴ ሸረሪት ጽንስ
      ራሴን በራሴ መዋጤ”
      የገዛ ብርሃኔን አስኳል
      እኔው በእኔው መሰልቀጤ፡
      ፍቅር ቢፈልቅ ብዬ እኮ ነው
      ከአለት ልብህ አንዳች ጥጋት
      ጀንበር ቢቀድ ብዬ እኮ ነው
      በልቦናህ የጎህ ንጋት፡
      አንተም ታዲያ ሲደርስ ቀኑ
      ሻማ እንድትሆን ለጭቁኑ
      ለድምፅ አልባው ለምስኪኑ!
      ጧፍ እንድትሆን ልክ እንደኔ
      አፍ እንድትሆን ለወገኔ፡፡
      ( ለእስክንድር ነጋ)

      Reply
  2. ዱባለ says

    February 16, 2013 02:09 am at 2:09 am

    እንደ ሻማ ቀልጦ ብርሀን መስጠት
    ራስን ሰውቶ መሆን ትሩፋት
    ጀግና መሆን በጎ ለሁሉም በረከት
    የሰው ልጅ ምሳሌ መሆን በትጋት
    ለግለሰብ ኣቅም ይሰጣል ብርታት
    ለብዙሀኑ ግን ስንፍና ያወርሳል
    የግል ሀላፊነት እኋላ ይቀራል
    የራሱን እጅ ኣጥፎ የሌላውን ያያል
    ለዚህ የሚበጀን ችቦ መሆንን ነው
    እንጨትን ሰብስቦ በልጥ ማያያዝ ነው
    ሁሉም የየራሱን መሀል መቆለል ነው
    የራስን ለኩሶ ሌላ ማቀጣጠል
    ብርሀን ያበዛል
    ደስታውም ይደምቃል
    ዘላቂም ይሆናል
    ችግር ይቀረፋል
    ሸክምም ይቀላል::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule