• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Editor

”ዛሬም ታለቅሳለች!”

October 30, 2013 08:19 am by Editor Leave a Comment

”ዛሬም ታለቅሳለች!”

''ዛሬም ታለቅሳለች!'' ትላ’ትናም - ዛሬም ቁማም - ተቀምጣም በውኗም - በህልሟም፤ እምባ እያዘነበች ደም እያፈሰሰች፤ ሁሉንም እያየች ዛሬም ታለቅሳለች።……. ‘’ረስታ - ተረስታ በራሷ ላይ ዘግታ፤ ከጥዋት እስከማታ እንቅልፏን ተኝታ’’። ተብሎ ተወርቶባት ለብዙ ዘመናት ታሪክ ተጽፎባት፤……. እሷ ግን፣ እሷ ናት ዓለም የሚያያት፤ እምባ እያዘነበች እህህ…… ትላለች ትንሰቀሰቃለች፤ ሁሉንም እያየች ዛሬም ታለቅሳለች።……… ተማፅኖ ተማሎ ተገዝቶ ምሎ ገ’ሎና አስገድሎ ፤ ‘’ለ’ርሀብ - ‘ርዛትሽ ለልመና - ፅናትሽ ለፍትህ - እጦትሽ ለሰላም - ለፍቅርሽ፤ መድሀኒት አውቃለሁ እኔ እሻልሻለሁ’’፤ ብሎ የሚገባው እምባዋን ሊጠርገው መፍሰሱን ሊያቆመው፤...... ጭራሽ አብሶባት ሀዘን ደራርቦባት፤ ማቁን አስለብሶ አመድ … [Read more...] about ”ዛሬም ታለቅሳለች!”

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

ኢህአዴግ የዘራውን አጨደ፣ ተጠያቂው ማን ነው?

October 28, 2013 07:12 am by Editor 1 Comment

ኢህአዴግ የዘራውን አጨደ፣ ተጠያቂው ማን ነው?

በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ተቃውሞ ቢያቀርቡም የኢህአዴግን ጆሮ ማግኘት ያልቻሉ ተበዳዮች ርምጃ ወሰዱ። ሕዝብ ወዶና ፈቅዶ ያልተቀበለው ኢንቨስትመንት ከዘረፋ ተለይቶ እንደማይታይ የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቀዋል። ውድመት የደረሰበት የህንድ ኩባንያ በልማት ባንክ ላይ ኪሳራ ሊያስከትል እንደሚችል ስጋት አለ። ለደረሰው ጉዳት "ተጠያቂው ማን ነው?” የሚል ጥያቄ ተነስቷል። በጥርጣሬ የሚታሰሩ መበራከታቸው በክልሉ ባሉ ተመሳሳይ የእርሻ ኢንቨስትመንት ባለቤቶችን ስጋት ላይ ጥሏል። ሻይ ቅጠል ለማልማት የተፈጥሮ ጥብቅ ደን እንዲያወድም የተፈቀደለት ቬርዳንታ ሀርቨስት የተባለ ኩባንያ በከፍተኛ ወጪ ያለማውና ለመለቀም በደረሰ ምርት ላይ ማንነታቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች እሳት ለቀውበታል። ጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓም ደረሰ በተባለው ቃጠሎ ኩባንያው የደረሰበት ሊሳራ እስከ 80 ሚሊዮን ዶላር … [Read more...] about ኢህአዴግ የዘራውን አጨደ፣ ተጠያቂው ማን ነው?

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

ከእሁድ እስከ እሁድ

October 27, 2013 10:59 pm by Editor 1 Comment

ከእሁድ እስከ እሁድ

“መጽሐፈ ቅዳሴ” ወደ ኦሮምኛ ተተረጎመ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን “መጽሐፈ ቅዳሴ” ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ ተተረጎመ፡፡ ለብዙ ዘመናት “መጽሐፈ ቅዳሴ”ን በግእዝ እና በአማርኛ ስትጠቀምበት የቆየችው ቤተክርስትያኗ፤ መፅሃፉን በኦሮምኛ ማስተርጎም የጀመረችው በ1999 ዓ.ም እንደሆነ ታውቋል፡፡ የመጽሐፉ መተርጎም በኦሮሚያ ክልል ላሉ አብያተ ክርስትያናት በኦሮምኛ ለመቀደስ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡ የቤተክርስትያኒቱ ቅዱስ ሲኖዶስ እያካሄደ ባለው የጥቅምት ምልዐተ ጉባዔው ትኩረት ከሰጣቸው ዋና አጀንዳዎቹ አንዱ ስብከተ ወንጌልን ማዳረስ እንደሆነ የገለፁት ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፤ የመጽሐፉ ሕትመት እንዲቀላጠፍ ትዕዛዝ እንዳስተላለፉም ለማወቅ ተችሏል፡፡ “መጫፈ ቂዳሴ” በሚል ርዕስ የተተረጎመው የኦሮምኛ መጽሐፉ፤ በቅርቡ ዝግጅቱን የተቀላቀሉትን ብፁዕ አቡነ ዮሴፍን … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ

Filed Under: News

ፈስ አጣርቶ የሚያስቀር ውስጥሱሪ በአሜሪካ እጅግ ተፈላጊ ሆኗል

October 27, 2013 05:08 pm by Editor 2 Comments

ፈስ አጣርቶ የሚያስቀር ውስጥሱሪ በአሜሪካ እጅግ ተፈላጊ ሆኗል

በእንግሊዝ የተፈበረከው ፈስ የሚያጣራ ውስጥሱሪ በአሜሪካውያን ዘንድ በከፍተኛ ሁኔታ ተፈላጊነቱ እየመጣ መምጣቱ ተሰምቷል፡፡ የአምራች ኩባንያ አፈቀላጤ የሆኑት ሲናገሩ “ከአጠቃላይ ሽያጫችን ውስጥ በአሜሪካውያን የሚገዛው እጅግ ከፍተኛውን ቁጥር የያዘ ነው” ብለዋል፡፡ ታዋቂው የውስጥሱሪ አምራች ሽሬዲስ በቅርቡ ፈስ አጣርቶ በማስቀረት እንዳይሸት የሚያደርግ ውስጥሱሪ ለወንዶችና ለሴቶች ለገበያ ማቅረቡ ከተሰማ በኋላ ሽያጩ በ400% አድጓል፡፡ ኩባንያው እንደሚለው በውስጥሱሪው የውስጠኛ ክፍል ከካርቦን የተሰራ ዞርፍሌክስ የሚባል ጨርቅ የተሰፋ ሲሆን ይህም አማካይ የሽታ መጠን ያላቸውን የፈስ ዓይነቶችን 200 ጊዜ ያህል እንዳይሸቱ የማድረግ ችሎታ እንዳለው አፈቀላጤዋ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ይህ የውስጥሱሪ ለሁሉም የሚያስፈልግ ነው፤ ምክንያቱም ሁሉም ሰው ይፈሳል” በማለት … [Read more...] about ፈስ አጣርቶ የሚያስቀር ውስጥሱሪ በአሜሪካ እጅግ ተፈላጊ ሆኗል

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

“በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ

October 27, 2013 09:11 am by Editor Leave a Comment

“በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ

ካዛንቺስ አካባቢ በልመና የሚተዳደሩ አንድ አይነሥውር ሽማግሌ አሉ፡፡ የሚለምኑት ከካዛንቺስ ስድስት ኪሎና ፒያሳ ለመሄድ ታክሲ ከሚጠብቁ ተሳፋሪዎች ነው፡፡ አንድ ቀን በእለቱ የለመኑትን ገንዘብ ታክሲ እየጠበቅሁ ባለሁበት ቁጠርልኝ አሉኝ፡፡ እስከ ቀኑ 11 ሰዓት አርባ ብር ለምነዋል፡፡ በሌላ ቀን ተመልሼ ጠየቅኋቸው። በልመና ከሚያገኙት ገንዘብ ልጃቸውን ኮሌጅ አስተምረዋል፡፡ ልጃቸው ሥራ ከያዘ ከዓመታት በኋላም ግን ልመና አላቆሙም፡፡ አሁንም እዚያው ካዛንቺስ እየለመኑ ነው፡፡ “ለምን ልመና አያቆሙም?” አልኳቸው፡፡ “ምን ላድርግ ቁጭ ልበል እንዴ?” በማለት እኔኑ መልሰው ጠየቁኝ፡፡ እዚያው ካዛንቺስ የሚለምኑ ሌላ አረጋዊ ከፍተኛ የእይታ ችግር አለባቸው፡፡ በምፅዋት የሚያገኙትን ሳንቲም ይዳብሱና አምስት ሳንቲም ከሆነ መልሰው ይወረውሩታል፡፡ በአንፃሩ የእይታም የአቅምም ችግር … [Read more...] about “በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

ምሁር (intellectual)

October 27, 2013 07:14 am by Editor Leave a Comment

ምሁር (intellectual)

ከሰው ወይ ከአምላክ ፤ ተምሮ የረቀቀ ቀለም ብዙ የጠጣ ፤ ከባሕር እየጠለቀ ተለይቶ የወጣ ፤ በርቶለት የራቀ አንጥሮ አብጠርጥሮ ፤ መርምሮ የላቀ በአዎንታዊ እሴቶች ፤ ጌጦ ያሸበረቀ ደግነትን ከሸር ፤ ልማትን ከጥፋት ፤ ለይቶ የጠበቀ የሚያሰነካክለውን ፤ የት እንዴት እንደሆን ፤ ነቅቶ የጠነቀቀ ነበር ምሁር ማለት ፤ መሻል መብለጣቸውን ፤ አጣጥሞ ያወቀ አዬ ድንቄም አያ ii ፤ ምሁሩ ሊቅ ዐዋቂ የሀገር አደራ ጠባቂ በአረጋዊያን ተመራቂ በታናናሾቹ ተደናቂ ትውልድን አናጭ አምጣቂ አብእናን ቀራጭ አላቂ በዕውቀት በጥበብ አርቃቂ ለችግር መፍትሔን አፍላቂ የሥልጣኔን ብርሃን ፈንጣቂ ለሀገር ለወገን መከታ ለትውልድ ተስፋ አለኝታ መመኪያ ደጀን ስጦታ አይደለም ? ትርጉሙ ሲፈታ ? አዪ … እ !! ድንቄም ዐዋቂ የመጠቀ የእንስቷን ተስፋ የደመቀ በወላጅ … [Read more...] about ምሁር (intellectual)

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

ስብሃት ህወሃት ጠቦ ታሪኩን እንደሚቋጭ አረጋገጡ

October 26, 2013 12:53 am by Editor Leave a Comment

ስብሃት ህወሃት ጠቦ ታሪኩን እንደሚቋጭ አረጋገጡ

ስብሃት ነጋ የኢህአዴግ አባትና ፈጣሪ የሆነው ህወሃት የመጨረሻው ታሪኩ ጠቦ እንደሚቋጭ ይፋ አደረጉ። ችግር የህወሃት ልዩ በረከትና ስጦታ እንደሆነ በማመልከት ህወሃት ውስጥ ልዩነትና መፈርከስ አደጋ ተከስቶ እንደማያውቅ ሸመጠጡ። አቶ ስብሃት ጠቦ የሚጠናቀቀውን የህወሃት ስውር አጀንዳ የገለጹት ከጋዜጠኛ ደረጃ ደስታ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስ በሰጡበት ወቅት ነበር። በኢህአዴግ የመከላከያ መዋቅር ውስጥ ከፍተኛ መከፋፈልና የኩዴታ አደጋ ሊያስከትል የሚችል አደጋ እንደተረጋገጠ ተጠቅሶ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ስብሃት "አዲስ አበባ መንግስት ገልብጠው የክልሎችን ድጋፍ ቢጠይቁ ማን እሺ ይላል" በማለት ነበር የመለሱት። አንዴ በመከላከያ ውስጥ የመከፋፈልና የመበታተን አደጋ ሊያጋጥም የሚችልበት አግባብ እንደሌለ፣ ጠያቂው እንዳለው የመፈንቅለ መንግስት አደጋ ቢያጋጥም እንኳ የህወሃት ስጋት … [Read more...] about ስብሃት ህወሃት ጠቦ ታሪኩን እንደሚቋጭ አረጋገጡ

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

የጎሳ ፌዴራሊዝም

October 25, 2013 09:12 am by Editor 1 Comment

የጎሳ ፌዴራሊዝም

ክፍል አንድ የወያኔ ትግሬዎችና ስለ አማራ ህዝብ ያላቸው ግንዛቤና የቆየ ጥላቻ ምን ይመስላል? የወያኔ ሃርነት ትግራይ መሪዎችም ሆኑ ተከታዮቻቸው የትጥቅ ትግላቸውን ሲጀምሩ ለትግራይ ህዝብ ችግርና ኋላ ቀርነት ተጠያቂዎቹ ከዳግማዊ ዐጼ ምንሊክ ጀምሮ እስከ ደርግ መውደቅ ድረስ በስልጣን ላይ የነበሩት ወያኔ አማራ ብሎ የሚጠራቸው መንግስታት እንደ ነበሩ በፖለቲካ ፕሮግራም ደረጃ ቀርጸው የትግራይን ህዝብ እንዳስተማሩ ቀድሞ የወያኔ ድርጅት አባል የነበረውና ዛሬ በስደት በሚኖርበት አስውስትራሊያ ሆኖ የወያኔን እኩይ ዓላማ በቆራጥነትና በሃቅ እያጋለጠ ያለው አቶ ገብረ መድህን ዓርዓያ በቅርቡ “እነማን ነበሩ” በሚል ርእስ በመረጃ አስደግፎ አሳውቆናአል። የወያኔ ድርጅት የአማራው ህዝብ በእነዚህ የአማራ መንግስታት ብሎ በሚጠራቸው ከዐጼ ምንሊክ እስከ ደርግ መውደቅ ድረስ በነበሩት መንግስታት … [Read more...] about የጎሳ ፌዴራሊዝም

Filed Under: Opinions

በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉት 24 ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ

October 25, 2013 08:47 am by Editor Leave a Comment

በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉት 24 ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ

የፌዴራሉ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤ ህግ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣናት እና ግብረ አበር ባለሀብቶች ላይ የመሰረተውን ክስ በፍርድ ቤት ማሰማት ጀምሯል። የኮሚሽኑ ዐቃቤ ህግ በተለይም በአንደኛው ተከሳሽ በአቶ መላኩ ፈንታ ላይ መዝገብ ቁጥር 14356 ስር ባለው 11ኛ ክስ ውስጥ ተከሳሹ በትዳር ያለችን ሴት አስኮብልለዋል የሚል ክስ መስርቶባቸዋል። ትናንት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ክሱ ሲነበብ፤ 1ኛው ተከሳሽ አቶ መላኩ ፈንታ የስራ ኃላፊነታቸውን በመጠቀም ለስራ ጉዳይ የመጣችን ሴት፤ ትዳሯን ፈታና በትዳር ውስጥ ያፈራቻቸውን ሦስት ልጆች በትና አብራቸው እንድትሆን አድርገዋል ሲል ስልጣንን ያለአግባብ የመጠቀም የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ሲል ከሷቸዋል። ወ/ሮ መቅደስ ለማ የተባሉት እኚሁ ሴት የቀድሞ ባለቤታቸውን ንብረት … [Read more...] about በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉት 24 ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ

Filed Under: Law Tagged With: Left Column

አህያው ማን ነው? የሚመለከተውስ ብሔር አለን?

October 25, 2013 07:34 am by Editor 4 Comments

አህያው ማን ነው? የሚመለከተውስ ብሔር አለን?

ይህንን ጽሑፍ ከጻፍኩት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በወቅቱ ጽሑፎቸን  ያስተናግድ የነበረ አንድ ዝነኛ የሬዲዬ (የነጋሪት-ወግ) ዝግጅት የጽሑፉን ይዘት ነግሬው እንዲያቀርበው ስጠይቀው አይ ስላለ የሚስተናገድበትን የነጋሪተ-ወግ መድረክ በማጣት በኋላም ተዘንግቶ ቆይቶ አንድ ሰነድ ፈልጌ ካርቶን ሳገላብጥ አገኘሁትና አሀ……. ለምን ታዲያ አሁን ቢያንስ በጋዜጣና በመካነ-ድሮች በኩል ለአንባቢያን አላደርሰውም በሚል አምጥቸዋለሁ የተጻፈው እንዳልኳቹህ ከ4 እና 5 ዓመታት በፊት ነው እንካቹህ፡- ሰሞኑን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ምርዓየ-ኩነት) ራሱ ጣቢያው ያዘጋጀውን አንድ ውይይት ተመለከትኩ የመወያያ ርእሳቸው የነበረው አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ የሀብታም ልጆች በሚማሩባቸው የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች በከፊሎቹ ልክ ተማክረው ያደረጉት በሚመስል መልኩ ማሰብ ከሚችሉ ዜጎች ፈጽሞ የማይጠበቁና የድፍረት … [Read more...] about አህያው ማን ነው? የሚመለከተውስ ብሔር አለን?

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

  • « Previous Page
  • Page 1
  • …
  • Page 228
  • Page 229
  • Page 230
  • Page 231
  • Page 232
  • …
  • Page 294
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule