ያስገረሙኝና ፈገግ ያሰኙኝ የማህበራዊ ሚዲያ ‹‹ጥቅሶች›› 1. ‹‹የድሃ ልጅ ስሙ ሀብታሙ ነው›› 2. ‹‹ሰውና ድፎ በትዕዛዝ እንደፋለን›› 3. ‹‹ቁንጅና ይኑርሽ እንጂ ፀባይ በዱላ ይመጣል›› 4. ‹‹የሴት ልጅ ግርዛትና ሚስድኮል ይቁም›› 5. ‹‹ኡፍ በማለት ትንፋሽ እንጂ ብሶት አይወጣም›› 6. ‹‹ለህይወትህ ዋጋ፣ ለልጆችህ ዳቦ ስጥ!›› ሰፈር ውስጥ የሰማኋቸው አዲሶቹ የሸገር ልጆች ቃላት • ‹‹በጤ›› - በጣም ለማለት • ‹‹በኔ›› - በእናትህ ለማለት • ‹‹እሱ እኮ እምባ ነው›› - የቅርብ ተቆርቋሪ ነው ለማለት • ‹‹ጠበዘዝነው›› - በላነው ለማለት • ‹‹ዘጭ ብያለሁ›› - ጠግቤያለሁ ለማለት • ‹‹ኤም ጢ ›› - መስሚያዬ ጥጥ ነው/ አልሰማህም ለማለት ታክሲ ላይ ያነበብኳቸው፡ 1. ‹‹ሰው ብቻ ነው የምንጭነው፤ በስህተት የገባ ካለ … [Read more...] about የአፍታ እፍታዎች
አንዳርጋቸው ጽጌ፣ የስደተኛው “ሲኦል ምድር” የመን እና የእኛ ስጋት …
ሰሞነኛው የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በየመን መታገትና ወደ ኢትዮጵያ የመተላለፍ ዜና ብዙዎችን እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ሆኗል። በአረብ ሃገር የሚገኙን ጨምሮ ኢትዮጵያውያንን በመላ አለም ከአድማስ አድማስ በተቃውሞና በድጋፍ እያነቃነቀም ይገኛል። ምሽቱን በፊስ ቡክ በ Facebook ማህበራዊ ገጽ ከተንሸራሸሩት አስተያየቶችና ወቅታዊ መወያያ ርዕሶች መካከል የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ መታገት ሲሰማ የመን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፋ እንደምትሰጥ ምንጩን ሳይነግረን መረጃ ያቀበለን የአውራምባ ታይምስ አዘጋጅ ዳዊት ከበደ ያስተላለፈው የማወያያ መጠይቅ አስገርሞ አሳዝኖኛል። ዳዊት በዚህ መጠይቁ "...አቶ አንዳርጋቸው የኢትዮጵያ ፖስፖር ይዞ መቆየት የለበትም ትላላችሁ ?" በማለት ዳዊት ራሱ ለመረጃ ቅርብ እንደሆነ ባለሙያ በአለማችን ነባራዊ ሁኔታ የነጻነት ታጋዮችን ሁለንተናዊ … [Read more...] about አንዳርጋቸው ጽጌ፣ የስደተኛው “ሲኦል ምድር” የመን እና የእኛ ስጋት …
“ምሁራን” በፊደሎቻችን ላይ የሚያነሣሷቸው ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
የሀገር ውስጥ ምሁራን በፊደሎቻችን ላይ ብዙ ዓይነት ቅሬታዎችንና ጥያቄዎችን ሲያነሡ ቆይተዋል አሁንም በየ ብዙኃን መገናኛው ማለትም በየነጋሪተ ወጉ(Radio) በየ ምርአየኩነቱ (Television) እና በየ መጣጥፉ በማንሣት ላይ ይገኛሉ፡፡ ለውጦችንም ማድረግ ይፈልጋሉ፡፡ ለዚህም እንዲመቻቸው ይመስላል የፊደሎቻችን ባለቤት የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን መሆኑን ልቦናቸው እያወቀ እንደፈለጉ ያለከልካይ እና ጠያቂ ለውጥ ለማድረግ እንዲመቻቸው ከፊደላቱ ባለቤት ከኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ተቃውሞ እንዳይነሣባቸው የፊደላቱን ባለቤት ለባዕድ ይሰጡታል ወይም የደቡብ ዓረቢያ ነው ብለው ይሰብካሉ፡፡ ፻ ዓመት ከሚጠጋ ጊዜ ጀምሮ ምሁራኑ በፊደሎቻችን ላይ ጥያቄ ሲያነሡ ቆይተዋል፡፡ የቀድሞዎቹ በተለየ ያነሡት የነበረ ጥያቄ እንደዛሬው መቀምር (Computer) ባልነበረበት ሰዓት የአማርኛ መጻፊያ መሣሪያ … [Read more...] about “ምሁራን” በፊደሎቻችን ላይ የሚያነሣሷቸው ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
የአማራ ጉዳይ፤ አለ? ወይስ የለም?
ተናግሬ ነበር ማለት ዋጋ የሌለው የወሬ ማጌጫ ነው፤ እስቲ ፍቀዱልኝና ልጠቀምበት፤ ከወያኔ ዋና ምሁር፣ ከመለስ ጋር ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ ፊት-ለፊት በቴሌቪዥን በተገኛኘን ጊዜ ‹‹አማራ የሚባል ጎሣ የለም፡›› በማለቴ መለስ ዜናዊና ጭፍሮቹ ብቻ ሳይሆኑ ‹‹አማራ-ነን ባዮች›› በቃልም፣ በጽሑፍም፣ በቴሌፎንም ልክ-ልኬን እየነገሩኝ አንጀታቸውን ቅቤ አጠጥተው ነበር፤ ‹አንዲት ሴት ደውለው እብድና ዘበናይ የልቡን ይናገራል፤› ብለውኛል፤ አንድ ሰው የተናገረው ስሕተት ከሆነ ስሕተቱን በማስረጃ ማጋለጥና የራስን ሀሳብ በማስረጃ መትከል ነው፤ እውቀት የሚዳብረው፣ ሰዎች የሚማሩትና በእድገት ጎዳና የሚጓዙት በተጨባጭ ማስረጃ መነጋገር ሲችሉ ብቻ ነው፤ እኔ አማራ የለም፣ ዜሮ (0) ነው፤ አልሁ፤ አማራ አለ፣ አንድ አለ፤ (1) ነው ያለ ሰው የአንድን ዋጋ ማሳየት አለበት፤ አማራ የለም የሚል … [Read more...] about የአማራ ጉዳይ፤ አለ? ወይስ የለም?
የየመን ኩባንያ የትምባሆ ድርጅት ከፍተኛ የአክሲዮን ባለድርሻ ሆነ
የፕራይቬታይዜይሽንና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ውሳኔ መስጠት በተቸገረበት የብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት ሽያጭ ጉዳይ ላይ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ውሳኔ ሰጠ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የየመኑ ኩባንያ ሼባ ኢንቨስትመንት የብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት 60 በመቶ ባለቤት እንዲሆን ወስኗል፡፡ የ70 ዓመት ዕድሜ ባለቤት የሆነው ብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት 22 በመቶ የሚሆነው አክሲዮን ከ1991 ዓ.ም. ጀምሮ በየመኑ ሼባ ኢንቨስትመንት ሲያዝ፣ ቀሪው 78 በመቶ አክሲዮን ደግሞ በመንግሥት የተያዘ ነበር፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በወሰነው አዲስ ውሳኔ ሼባ ኢንቨስትመንት ተጨማሪ 38 በመቶ አክሲዮን ከመንግሥት ላይ እንዲገዛ የሚፈቅድ በመሆኑ፣ ሼባ ኢንቨስትመንት በብሔራዊ ትምባሆ ድርጅት አክሲዮን ላይ አንበሳውን ድርሻ 60 በመቶ ሲይዝ፣ … [Read more...] about የየመን ኩባንያ የትምባሆ ድርጅት ከፍተኛ የአክሲዮን ባለድርሻ ሆነ
ቅኝ ግዛት!
ምነው በቀደም ለት እንቢልታ ሲነፋ ከበሮ ሲደለቅ፣ ከዘመናት ግዞት ነፃ የወጣንበት፣ ብለህኝ አልነበር አፍሪካ ነፃ ናት? "'አፍሪካ . . . ሀገራችን አፍሪካ የኛ ናት አፍሪካ አፍሪካ. . ." ተብሎ ሲዘመር የጥቁሮች ነፃነት? ታዲያ ዛሬ ለሊት፣. . . የሰማሁት ዋይታ ያዳመጥኩት ጩህት፣ ሲያከብሩ እዳትለኝ የበአሉን ማግስት? ዋሽተህኛል እንዴ . . . ? ትርጉሙን አዛብተህ? . . . ሆኖ እንዳይሆን ብቻ፣ ነፃ መሆን ማለት ካልሆኑ አቻ ላቻ ፣ ለወሬ ማድመቂያ ዳንኪራ መርገጫ፣ ነፃነት ነፃነት እያሉ ማፋጫ፣ ድቤ መደለቂያ በባዶ መንጫጫ ? እኔን ነፃ ያርገኝ. . . በዚች መሬታችን በምንኖርባት፣ የጥቁር ደም አጥንት በግፍ ባለቀባት፣ ነፃነት አግኝቶ ደምቆ `ሚኖርባት ? የሰላምን አየር ተንፍሶ `ሚድርባት ነጭ ነው ወይ ጥቁር . . . … [Read more...] about ቅኝ ግዛት!
የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ታገቱ
ከግንቦት 7 የተሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት … [Read more...] about የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ታገቱ
“የድሮ ስርዓት ናፋቂ”?
ይህ ቃለመጠይቅ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ከአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ተስፋዬ ጋር (19 April, 2014) ካደረጉት ቃለምልልስ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው፡፡ አዲስ አድማስ፤ ባለፉት ተከታታይ ሳምንታት በሬዲዮ ፋና ላይ በነፃው ፕሬስ ዙሪያ ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል፡፡ እርስዎም በውይይቱ ላይ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ በውይይቱ ላይ “ዶ/ር ዳኛቸው ስሜታዊ ሆነው ነበር” የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡ “የድሮ ስርዓት ናፋቂ” የሚል ትችትም ተሰንዝሮቦታል፡፡ የእርስዎ ምላሽ ምንድን ነው? ዶ/ር ዳኛቸው፤ የስሜታዊነቱን ነገር ያመጡት እንኳን እነሱ ናቸው፡፡ ስድብና ዘለፋውን በመጀመር እነሱ ይቀድማሉ፡፡ “የድሮ ስርዓት ናፋቂ” ለሚለው በእውነቱ በናፍቆት ደረጃ ፍትህ ናፋቂ ነኝ፡፡ ዴሞክራሲና የህዝባችንን ነፃነት ናፋቂ ነኝ፡፡ የዱሮ ሥርዓት ናፋቂ የሚሉኝ “አሁን ያለንበት ወርቃማው ጊዜ ነው” የሚሉ ዜጎች … [Read more...] about “የድሮ ስርዓት ናፋቂ”?
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፭” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አምስት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ መልስ ለሀገር ለወገን - ውለታ የሰራ ስሙ ለዘለዓለም - ይኖራል ሲጠራ ነገር ግን ታሪኩን - ያረገውን በጎ አንባቢው አለበት - መረዳት ፈልጎ እኛ ለማስታወስ - ይሄንን አድርገን ለማቅረብ ችለናል - መላኩ በያንን እኚህ ስመ ጥሩ - ኢትዮጵያዊ ዶክቶር ሙሉ እድሜአቸውን - ደክመዋል ለሀገር። ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮
አቶ መላኩና አቶ ገብረዋህድ የቀረበባቸውን ክስ ክደው ተከራከሩ
"ልንመሰገንበት በሚገባ ሥራ ወንጀለኛ መባላችን ያሳዝናል" አቶ መላኩ ፈንታ በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ፣ የቀረበባቸውን ክስ ክደው በመከራከር ድርጊቱን አለመፈጸማቸውንና ጥፋተኛም እንዳልሆኑ ለፍርድ ቤት ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም. አስረዱ፡፡ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በሦስት የክስ መዝገቦች ክስ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ አንደኛውን የክስ መዝገብ እንዲያሻሽል የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ያዘዘው ቢሆንም፣ ዓቃቤ ሕግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት በትዕዛዝ ላይ ይግባኝ በማለቱና በማሳገዱ ተጠርጣሪዎቹ በሁለቱ የክስ መዝገቦች ላይ ብቻ የእምነት … [Read more...] about አቶ መላኩና አቶ ገብረዋህድ የቀረበባቸውን ክስ ክደው ተከራከሩ










