በቅርቡ የህወሃት ኣርባኛ ዓመት ለየት ባለ መንገድ መከበሩ ገርሞኛል። በየዓመቱ እንደሚከበር ሁላችን እናውቃለን። ይሁን እንጂ የዓርባኛ ዓመቱ በዓል እንዲህ ለምን እንደተወራለት ለምን የሌላ ኣገር መሪ ሳይቀር እንደተጋበዘበት ኣልገባኝም። ብዙ ጊዜ እንዲህ ዓይነት ለየት ያለ ድግስ የሚደረገው የኢዮቤልዩ በዓል ሲከበር ነው። የሆነው ሆኖ የመነሻ ኣሳቤ ይሄ ኣይደለም። ህወሃት ኣርባኛ ዓመት በዓሉን ሲያከብር እኔ በህወሃት ተፈጥሮ ስደመም ነበር። በርግጥ ኢትዮጵያ ኣሁን ላለችበት የተመሰቃቀለ ህይወት ሲንከባለሉ የመጡ ኣንዳንድ ችግሮች ኣስተዋጾ ቢያደርጉም የችግሩ ከፍተኛ ኣስተዋጾ ኣድራጊ ግን ህወሃት ነው። በየክልሉ የህወሃት ተከታዮች ኣስተዋጾኣቸው እንዳለ ሆኖ የህወሃት ድርሻ ግን በጣም ገዝፎ ይታያል። ግን …ግን ለምንድነው በህወሃት መራሹ መንግስት ጊዜ ኢትዮጵያ እንዲህ ዓይነት ኣስከፊ … [Read more...] about ህወሃት ምንድን ነው?
“የህዝባዊ ማህበራት ሚናና የ2015 የኢትዮጵያ ምርጫ”
ለዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ ለምትገኙ የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በሙሉ ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል ስለ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምንነት ማህበረሰቡን ግንዛቤ ለማስጨበጥ በየዓመቱ የአለም አቀፍ የሴቶችን ወር ምክንያት በማድረግ በመጋቢት ወር ላይ ጉባኤ በማዘጋጀት ሴቶችን በሚመለከቱ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምሁራን ጥናታዊ ጽሑፎችን እንዲያቀርቡና፣ ለችግሮቹ መፍትሔ እንዲጠቁሙ በማድረግ ማህበረሰባችንን ግንዛቤ ለማስጨበጥ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ሴቶች በማህበራዊ፣ በኤኮኖሚና በፖለቲካ የሚደርስባቸውን ችግሮች በተለይም የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በአረብ አገራት ተሰደው ስላሉ ኢትዮጵያዊያን ሴቶች መብትን አስመልክቶ በየጉባኤዎቹ ሰፋ ያለ ትምህርታዊ ውይይቶች አካሂዷል። ዘንድሮም የኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል ለ፬ኛ ጊዜ የሚካሄድ ዓመታዊ ጉባኤ … [Read more...] about “የህዝባዊ ማህበራት ሚናና የ2015 የኢትዮጵያ ምርጫ”
“ጅብ በማይታወቅበት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ” ይላል
“ጅብ በማይታወቅበት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ይላል” የሚለው ጥሬ ንባብ፤ ስለ ጅብና ስለ ቁርበት መልእክት ለማስተላለፍ አይደለም። ጅቡ የሚወክለው አካል አለ። ቁርበቱ የሚወክለው ነገር አለ። በቁርበቱና በጅቡ መካከል ያለውን ግንኙነት ሳያውቁ ቁርበቱን ለጅቡ ያነጠፉለትም የሚወክሉት አለ። ይህ አገላለጽ በኢትዮጵያዊው ቅኔ ትምህርት፣ ቀመር፣ ስልት ሲመዘን፤ ጅቡ ሰም ነው። ቆርበቱም ሰም ነው። ሁሉም ሰም ነው። ወርቁ ከሰሙ ጋራ ጎን ለጎን ባለመቀመጡ፤ ወርቅ የጎደለው ‘ሰማ-ሰም’ ይባላል። ወደ ጠቅላላ ይዘቱ ስንገባ፤ በጅብና በቁርበት መካከል ያለው ግንኙነት፤ በተበይና በበይ መካከል ባለው ግንኙነት ብቻ ሳይወሰን፤ የተደራረበ ሰይጣናዊ የአጠቃቀምን ዘዴ ይጠቁማል። ጅብ ቁርበቷን እንደሚበላት በማይታወቅበት አገር ሄዶ ቁርበቷን ‘አንጥፉልኝ ’ እንደሚል፤ አንዳንድ ሰዎችም በሚታወቁበት … [Read more...] about “ጅብ በማይታወቅበት አገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ” ይላል
እውን ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚደነቅ የሚከበር ነገር አለውን?
በእስካሁኑ ግፍ ያልጠፋኸው ነገር ግን ለማይቀርልህ ወገኔ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! እንኳን ለአጥፊህ ለወያኔ ሐርነት ትግራይ 40ኛ ዓመት የልደት በዓል አደረሰህ! የዚህች ሀገር ነቀርሳ በውስጧ የበቀለበት 40ኛ ዓመት እነሆ ከነገ ወዲያ እሮብ የካቲት 11 2007ዓ.ም. ይከበራል፡፡ ግን ወያኔ ማን ነው? እውን የሚከበር የሚያኮራ ማንነት አለው? ነው ወይስ የሚረገምና የሚያሳፍር? ከዚህ ቡድን ውስጣዊ ታሪክ እንደምንረዳው ይህ ቡድን በርዕዮተ ዓለምና በአስተሳሰብ ልዩነት በግል ጥቅምና በሥልጣን ሽኩቻ አንዱ ሌላውን እየበላ አንዱ በሌላው እየተበላ እርስ በእርስ እንደ አውሬ እየተባላ እየተጠፋፋ በመጨረሻ በአውሬነቱ የበረታው የበረታው አስከፊው አስከፊው ቀርቶና ተቧድኖ ለዚህ የደረሰ እኩይ ሰይጣናዊ ቡድን ነው፡፡ የወያኔን የትግል ታሪክ ስናይ ከቀደምቶቹ የሕወሀት አባላት ጥለው ከወጡትም … [Read more...] about እውን ወያኔ ሐርነት ትግራይ የሚደነቅ የሚከበር ነገር አለውን?
ከለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ
ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላት፤ እንዲሁም በUK እና በመላው ዓለም ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች በሙሉ። በዚህ በለንደን የፍርድ ቤት ችሎት የቤተ ክርስቲያኗን የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ ጽ/ቤትን በሕገ ወጥ መንገድ በመያዝ ከስልጣናችን አንለቅም በሚል መንገታገት በቤተ ክርስቲያኗም ሆነ በአባላቱ ላይ ከፍተኛ ምስቅልቅልን ያመጡ ግለሰቦች በሚወክላቸው ጠበቃ አማካኝነት 1) የቤተ ክርስቲያኗ አባላት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ለመግዛትም ሆነ ቤተ ክርስቲያኗን በሃብትና በንብረት ለማደርጀት ያፈሰሱት ሃብትና ጉልበታቸው በስጦታ መልክ የተደረገ ስለሆነ ከልገሳ ባለፈ የቤተ ክርስቲያኗ ሃብትና ንብረት ተጋሪ (Beneficiaries) ስላልሆኑ የመወሰንም ሆነ ይህ ይደረግ የማለት መብት አይኖራቸውም፤ 2) የቤተ ክርስቲያኗ … [Read more...] about ከለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ
በሳውዲ የኢትዮጵያዊቷ የደመወዝ ጥያቄ ሽጉጥ አስመዘዘ
ሳውዲ አረቢያ ቢሻ እየተባለ የሚጠራ አነስተኛ ከተማ ውስጥ አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ በሳውዲያዊ አሰሪዋ ከተተኮሰባት ጥይት ከሞት መትረፏን ምንጮች አረጋገጡ። በዚህች ኢትዮጵያዊት ላይ ስለደረሰው የነፍስ ማጥፋት ጥቃት በኢህአዴግ ተመልምለው የተሰየሙት ዲፕሎማቶች ምንም ዓይነት መረጃ የላቸውም፡፡ አደጋው የደረሰባት ወጣት በ20ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ መሆኗን የሚናገሩ የዜናው አቀባዮች ወጣቷ እንደተራራ የገዘፈውን ህይወት በመጋፈጥ ቤተስቦቿን ከችግር ለመታደግ በወቅቱ ከነበሩ የኤጀንሲ ደላላዎች ጋር ተዋውላ ሳውዲ አረቢያ ለስራ መምጣቷን ይናገራሉ። በተጠቀሰው ውል መስረት ወጣቷ አሰሪዋ የወር ደሞዝዋን በየወቅቱ እንዲከፍላት ለማስረዳት ብትሞክረም ከኢትዮጵያ ከመጣች ጀምሮ ላለፉት ሁለት አመት ያለደሞዝ ለመቆየት መገደዷን ለመረዳት ተችሏል። ሰሞኑን ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ … [Read more...] about በሳውዲ የኢትዮጵያዊቷ የደመወዝ ጥያቄ ሽጉጥ አስመዘዘ
ዘጸአት ለኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ ምድር፥ ምኒልክን (ዮሴፍን) 'ማያውቅ፥ አዲስ ንጉሥ መ'ቶ፣ "ለነፃነት" ብሎ፥ የነፃነትን ጧፍ፥ ረጋግጦ አጥፍቶ፣ "ከኔ ወዲያ ላሳር!"፥ አለን አፉን ሞልቶ፣ ያ'ባቶችን ክብር፥ አፈር መሬት ከ'ቶ። ያገሬ ፈርዖን፥ ልቡ እጅግ ደንድኖ፣ የፈጣሪን ፈቃድ፥ እንዳይሰማ ሆኖ፣ "እንደ'ኔ ያለ ንጉሥ!"፥ እያለ ይጽናናል፣ የበትሩን ምሬት፥ በጠገበ ጉልበት፥ ከተማን ያጸናል። ስንት አሮን ተላከ? ስንት ሙሴ መጣ? "የሠራዊት ጌታ፥ 'ህዝቤን ልቀቅ' ይላል!"፥ የሚል ቃል ሊያወጣ፣ ስንት ምርጫ ሆነ፥ ስንት ምርጫ ሄደ፣ ደንዳናው ፈርዖን፥ በህዝብና ፍትህ፥ እንደተጓደደ። ምልክቶች ታዩ፥ ታምራትም መጡ፣ ፈተናው ጸና እንጂ፥ የእብሪተኞችን ልብ፥ ቅንጣት አ'ለወጡ። የባሰው መጣና፥ የ'እብራውያን' በኩር፥ እየተሰደደ፣ መልአከ ሞት ጥላ ፥ 'የፈርኦንን በኩር'፥ … [Read more...] about ዘጸአት ለኢትዮጵያ
ምን እየጠበቅን ነው?
የትግሬ ወያኔ በኃሣብ፣ በዕቅድ እና በተግባር ፀረ-ዐማራ፣ ፀረ-ኢትዮጵያ እና ፀረ-ኢትዮጵያዊ የሆነ ድርጅት መሆኑን ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ያረጋገጠው ሃቅ ነው። ሠሞኑንም ከመገናኛ ብዙሃን የሚደመጠው «የትግራይ ድንበር አል-ውሃ ድረስ ነው» የሚለው ወሬ የዚሁ የሚጠበቀው የትግሬ-ወያኔ ተከታይ እርምጃ እንደሆነ አያጠያይቅም። ኢትዮጵያን የማፈራረሱ የንድፈ-ኃሣብ መሠረት የተጣለው በተለያዩ የውጭ ኃይሎች እንደሆነ ይታወቃል። ከእነዚህ መካከል ሮማን ፕሮቻዝካ የተባለው የኦስትርያ-ሐንጋሪ መሥፍን (Baron Roman Prochazka) ወጥነት ባለው መንገድ አዘጋጅቶ ያሠራጨው መጽሐፍ ዋና ተጠቃሽ ነው። የሮማን ፕሮቻዝካ መጽሐፍ ኢትዮጵያ በፋሽስት ጣሊያን በተወረረችበት በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. (1935 G.C.) በጀርመንኛ ቋንቋ «Abessinien: die schwarze Gefahr» በሚል ርዕስ፣ … [Read more...] about ምን እየጠበቅን ነው?
የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ 60ኛ አመት የልደት በአል በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ
ፌብርዋሪ 14, 2015 በኖርዌይ የሚኖሩ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ መተዳደሪያ ደንቡ በሚያዘው መሰረት የአባላት ጠቅላላ 3ኛ እና 4ኛ ሩብ ዓመት መደበኛ ስብሰባ የሥራ ክንውን ሪፖርት የቀረበበት የተሳካ አጠቃላይ ስብሰባ አድርገዋል። በስብሰባው ላይ በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎና በተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች የሚኖሩ የድርጅቱ አባላቶች የተገኙ ሲሆን የአባላት ስብሰባው አስቀድሞ በተያዘለት ፕሮግራም መሰረት በኖርዌጂያን የሠዓት አቆጣጠር ከቀኑ 13፡30 ተጀምሮዋል። ስብሰባውን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አቢ አማረ በ 24 ዓመት የወያኔ አረመኒያዊ አገዛዝ በግፍ ለተገደሉት እና በየእስር ቤቱ በግፍ ለሚስቃዮ ንጹሀን ዜጐች የአንድ ደቂቃ የህሊና ጹሎት በማድረግ ስብሰባውን ያስጀመሩ ሲሆን በመቀጠልም … [Read more...] about የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ 60ኛ አመት የልደት በአል በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ
ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት
እጅግ ለተከበሩ ለብፁዕ አቡነ ብርሃነ-ኢየሱስ ደምረው ሱራፌል የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት፤ የኢትዮጵያ ጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዚዳንትና የምሥራቅ አፍሪካ የካቶሊክ ቤ/ክ ማሕበር ሊቀ መንበር፤ አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ። በመጀመሪያ፤ ለብፁዕነትዎ የሚገባ እጅግ ከፍ ያለ የአክብሮት ሰላምታ አቀርባለሁ። በተጨማሪም፤ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በደህና፤ በክብርና በሞገስ አደረሰዎ በማለት መልካም ምኞቴን በትሕትና እገልጻለሁ። በመቀጠልም፤ ሰሞኑን የ1.228 ቢሊዮን የካቶሊክ እምነት ተከታዮች ባላት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን፤ እጅግ የተከበሩ ብፁዕ ሊቀ ጳጳሳት (ካርዲናል) ሆነው በመሾምዎ፤ እንኳን ደስ አለዎ በማለት፤ ለዓለም ሰላምና ለክርስቲያን አንድነት የሚያደርጉት ጥረት በቸሩ አምላክ ተራዳኢነት እንዲሳካልዎ ልባዊ ጸሎታችንን በትሕትና እናቀርባለን። የብፁዕነትዎ … [Read more...] about ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት









