ስንኖር በዚህ አለም • • • ቆመን ለመራመድ፣ ጫናውን ለመቻል • • • ግፊያውን ለመልመድ፣ አቀበት ለመውጣ • • • ቁልቁለት ለመውረድ፣ ጠንክሮ መጓዝ ነው • • • የለም መንገዳገድ። እኛ ያምላክ ልጆች ~ ባምሳሉ የሰራን፣ እንደ ምድር አሸዋ ~ ምድርን የሞላን፣ ፈጣሪ ሲፈጥር ~ ከአፈር ሲሰራን፣ "ብዙ ተባዙ" እንጂ ~ መች ተጋፉ አለን? እንደ ቃሉም ሆነ = እልፍ አእላፍ ሆንን፣ ላይ በላይ ተዋለድን = እንደ አሸን ፈላን፣ ምድር ተጥለቀለቀ = አለምንም ሞላን፣ መሬት ተጣበበች = ቦታ አልበቃ አለን፣ አንዱ ባንዱ አሴረ = እርስ በርስ ተጋፋን፣ መንገድ ለማስለቀቅ = ጥሎ ማለፍ ጀመርን። ባምሳሉ የፈጠረን • • • እኛ ያምላክ ልጆች፣ ሰብእናው ጎሎን • • • ሆነን እንደ ጥጆች፣ ግጦሹን ለማግኘት • • • ሳሩን ለማሻመድ፣ ደካማውን ጥለን • • … [Read more...] about እኛ ያምላክ ጥጆች!!!
ለሃጅ ጸሎት መጥቶ ሳውዲ የቀረው ገበሬ እንግልት
ወንድም ራያ ጀማ የ5 ወንድ እና የ3 ሴት ልጆች ጎልማሳ አባት ነው። ወደ ሳውዲ የመጣው ድህነት፣ የኑሮ ውድነት፣ የፖለቲካው ሙቀት አለያም የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ገፍቶት አይደለም። ሳውዲ የመጣው፣ በእስልምና እምነቱ በሚያዘው መሰረት በህይወት ዘመኑ የሚጠበቅበትን ለማድረግ ከብቶቹን ሽጦ የሃጅ ጸሎት ለማድረግ ነበር . . . ዳሩ ግና የጅማው ገበሬ ራያ ጀማል እንደ ቀሩት ጓደኞቹ ጸሎቱን አድርጎ ለመመለስ አልቀናውም! ከሀጃጅ ጓደኞቹ ተለይቶ ከቤተሰብ እንደራቀ ፣ ላለፉት ሁለት አመት ከመንፈቅ ገደማ ሳውዲ በእንግልት ጊዜውን ሊገፋ ግድ ብሎታል። ምክንያቱም የሃጅ ጸሎቱን ከውኖ መካ ውስጥ መኪና አደጋ ደረሰበትና ነው! የራያ ጀማል ጉዳት. . . ራያ ጀማል በደረሰበት የመኪና ግጭት የተለያየ የአካሉ ክፍል በጠና ስለተጎዳ በከፍተኛ ህክምና መካ ውስጥ ለሁለት አመት ተኩል ገደማ በሳውዲ … [Read more...] about ለሃጅ ጸሎት መጥቶ ሳውዲ የቀረው ገበሬ እንግልት
አድዋ ለኔ!
እውነት አድዋ ለኔ ምኔ ነው? ላንተ፣ ላንቺ ለርስዎስ ትርጉም አለው? ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ አንዱ ዓለም ተፈራ እስከመቼ፤ ረቡዕ፤ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻፯ ዓመተ ምህረት ሳኒቬል፤ ካሊፎርኒያ ( Wednesday, 2/25/2015 ) … [Read more...] about አድዋ ለኔ!
ወያኔና ሽብርተኛነት
ወያኔነትና ሽብርተኛነት ትናንት ምን ዓይነት ግንኙነት ነበራቸው? ዛሬ ምን ዓይነት ግንኙነት አላቸው? ወደዚያ ከመሄዳችን በፊት የአሸባሪነት የተግባር መገለጫው ምንድን ነው? ብለን እንጠይቅ፤ አሸባሪነት፡- • ያለውን የሥልጣን ሥርዓት የማፍረስ ዓላማ ያለው ነው፤ • ዓላማውን ለማሳካት ጉልበቱን የሚያፈረጥመው ከሥርዓቱ ጠላቶች በሚያገኘው፡-- • የመሣሪያ እርዳታ፣ • የእውቀት ድጋፍና ገንዘብ • ዓላማውን ለማሳካት o ሰዎችን ገድላል o ያስራል፤ ያሰቃያል o ይዘርፋል፤ ይቀማል፤ • ዓላማውን ለማሳካት o ሃይማኖቶችንና ባህልን ያዳክማል፤ o የጥንት ታሪክ ማስታወሳዎችንና የቆዩ መጻሕፍትን ያጠፋሉ፤ o የፖሊቲካ እምነትን ያግዳል፤ o የመሰብሰብ ነጻነትን ይከለክላል፤ o የመደራጀት ነጻነትን ይከለክላል፤ o ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ይከለክላል፤ o ጉልበትን ወደሥልጣን … [Read more...] about ወያኔና ሽብርተኛነት
DCESON Press release
Press release DCESON has arranged a public meeting and fundraising event on April 18, 2015 from 15 pm to 22 pm, Come and contribute your share to the HULEGEB TIGEL for freedom and democracy. Let’s support ultimate struggle for building democratic system in Ethiopia. There was no reign or rule in the history of Ethiopia like the rule of Wayne under which Ethiopians humiliated, undignified, undermined and lost their identity. At present the fundamental trouble of Ethiopia and its citizen is not … [Read more...] about DCESON Press release
“ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ ሆን ተብሎ የተቀየሰ ስልት ነው”
• የሶዶ ፖሊስ 8 የሰማያዊ ዕጩዎችን በማሰር ቅስቀሳውን አስተጓጉሏል • የጅማ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ተዘርፏል ሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅስቀሳ እንዳያደርግ በፖሊሶች ክልከላና ወከባ እየደረሰበት እንደሚገኝ የሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ጉዳይ ኃላፊና ም/ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ዛሬ መጋቢት 5/2007 ዓ.ም ፓርቲው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅስቀሳ ያደረገ ሲሆን በባህርዳርና ወላይታ ዞን ፖሊስ የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር ቅስቀሰውን ማደናቀፉን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ቅስቀሳ በሚያደርግበት ወቅት የከተማው ፖሊስ "የምርጫ ቅስቀሳ አልተጀመረም" ብሎ ያዋከበ ሲሆን የፓርቲው አመራሮችና አባላት ቅስቀሳ መጀመሩን ገልጸው ስራቸውን እያከናወኑ በነበሩበት ወቅት "ህገ ወጥ ሰላማዊ ሰልፍ" … [Read more...] about “ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ህዝብ እንዳይደርስ ሆን ተብሎ የተቀየሰ ስልት ነው”
“ስሉሱ” ዞረ እንዴ?!
ከጥቂት ሳምንታት ወዲህ ባልተለመደ ሁኔታ ኢህአዴግ ላይ ታዋቂ የዓለማችን ጋዜጦች የጀመሩት ተከታታይ ትችት፣ ማሳሰቢያና መፍትሔ ጠቋሚ ዘገባዎች መነጋገሪያ አጀንዳ ሆነዋል፡፡ ሚዲያዎቹ በዘገባቸው ኢህአዴግን ከቻይና አምባገነናዊና አክራሪ አገዛዝ ጋር አመሳስለዋል፡፡ ኢህአዴግ እከተለዋለሁ የሚለውን የኢኮኖሚ መርህ ከቻይና የተኮረጀ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ውጤቱም ሆነ መድረሻው ግራ የሚያጋባና የማይታወቅ እንደሆነ ዘግበዋል፡፡ ጋዜጦቹ ኢህአዴግን በሚንከባከቡት መንግሥቶቻቸው እና በራሱ ኢህአዴግ ላይ የሰላ ሒስ መሰዘንዘር መጀመራቸው የፖሊሲ አውጭዎችን አስተሳሰብ የሚያስቀይር ከመሆን አልፎ ኢህአዴግ ላይ “ስሉሱ” ዞሯል የሚያስብል እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ “ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” በሚል ርዕስ የሰብዓዊ መብት ተመልካች የሆነው ድርጅት (ሂዩማን ራይትስ ዎች) ኢህአዴግ በሚያደርስባቸው ስልታዊ … [Read more...] about “ስሉሱ” ዞረ እንዴ?!
“አልሸጥም ማለትም ዕብሪት አይደለም”
ኢትዮጵያውያን በታሪካችን የታወቅነው በኩራታችንና ራሳችንን በማክበራችን ነበር፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት የስዊስ አምባሳደርን ወያኔ አስፈራራውና በኢሰመጉና በሱ መሀከል የነበረውን ልዩነት አደባባይ አወጣው፤ ስለኢሰመጉ የሆነ ያልሆነውን ለመናገር መብት ያገኘህ የመሰለህ አሥር ሺህ ዶላር ስለሰጠኸን ነው፤ ይህንን አሥር ሺህ ዶላር መኪናዬን ሸጬም ቢሆን እመልስልሃለሁ ብዬ በጋዜጣ አወጣሁ፤ ይህንን ያነበበ የትምህርት ቤት ጓደኛዬ እቤቴ ድረስ መጥቶ የአሥር ሺህ ዶላር ቼክ ሰጠኝና መከናህን አትሸጥም፤ ይኸውልህ አፍንጫው ላይ ወርውርለት ብሎኝ ሄደ፤ እኔም ለስዊስ አምባሳደር የአሥር ሺህ ዶላር ቼክ ላክሁለት፤ እሱም አልተቀበለኝም፤ በመቀስ ቆርጦ መለሰልኝ፤ ልናገር የፈለግሁት ዋናው ነገር ሁለት ነው፤ አንዱ ክብራችንን በገንዘብ የማንሸጥ እንደነበርን ለማስታወስ ሲሆን ሌላው ደግሞ ደጉን ጓደኛዬን … [Read more...] about “አልሸጥም ማለትም ዕብሪት አይደለም”
“ችሎት ደፍራችኋል” ተደፋሪው “ፍርድ ቤት”
"ችሎቱ ላይ ያጨበጨብነው በማፌዝ ሳይሆን በምሬት ነው" የሺዋስ አሰፋ "ችሎት ደፍራችኋል ካላችሁ ቅጣቱን ጨምሩብንና ሸኙን" ዳንኤል ሺበሽ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ቅጣት ተላለፈባቸው፣ ተጨማሪ ቅጣትም ይጠብቃቸዋል በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ከስምንት ወራት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ፣ የአንድነት እንዲሁም የዓረና ትግራይ ፓርቲዎች አመራሮች "ችሎት በመድፈር ወንጀል" ጥፋተኛ በመባላቸው መጋቢት 1/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት በሦስቱ አመራሮች ላይ እያንዳንዳቸው በሰባት ወራት እስራት እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል፡፡ የካቲት 26/2007 ዓ.ም ተከሳሾች በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸመባቸውና ንብረትም እንደተወሰደባቸው በመግለጽ አቅርበውት ለነበረው አቤቱታ ፍርድ ቤቱ የማረሚያ … [Read more...] about “ችሎት ደፍራችኋል” ተደፋሪው “ፍርድ ቤት”










