ከ17ሺህ በላይ ሰዎች ያሳተፈው የሰባት ወር ጥናት ይፋ ሆኗል የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ በደቡብ ክልል የሚነሱ የአደረጃጀት ጥያቄዎችን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ ምላሽ ለመስጠት ያስጠናው ጥናት ውጤት ዛሬ ይፋ ሆነ። በጥናቱ የተሳተፉት ክልል የመሆንን ጥያቄ በዕርጋታ እንዲታይ ተናግረዋል። ላለፉት ሰባት ወራት በምሁራን የተካሄደው የደቡብ ክልል አዲስ አከላለልን የተመለከተው ጥናት ውጤትን በተመለከተ ጥናቱን ያካሄዱት ባለሙያዎች ረቡዕ ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የደቡብ ክልል የብዝሃነት ምልክት አብሮ የመኖር አርአያ መሆኑን አንስተዋል። በአሁኑ ወቅት ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎች የክልል ምስረታ ጥያቄ በክልሉ በስፋት ቀርቧልም ብለዋል። የጥናት ቡድኑ ከተለያዩ የትምህርት ዘርፎች የተውጣጡ ምሁራንን የያዘ ሲሆን፥ ምሁራኑ … [Read more...] about በደቡብ ክልል የመሆን ጥያቄ ይቆይ፤ በዕርጋታ ይታይ – የክልሉ ነዋሪዎች አስተያየት
ሀዋሳ የጦርነት አውድማ አልሆነችም
በተነሳው ተቃውሞና ግጭት ጉዳት የደረሰባቸው አሉ የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ ለዛሬ ለማወጅ መቀጠሩን ተከትሎ በሐዋሳ እና አካባቢዋ ግጭት ተቃውሞ መከሰቱ ተገለፀ ። ከዚህ ጋር ተያይዞ ከተማዋ የጦርነት አውድማ እንደሆነች ተደርጎ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚወራው ሐሰት መሆኑ ተነገረ ። የጥያቄ አራማጆች ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ እንደገለፁት የሲዳማ ሽማግሌዎች እና ወጣት የጉዳዩ አቀንቃኞች ዛሬ ጠዋት ሊያካሂዱት ያቀዱት ስብሰባ አካባቢውን በዘጉት በፀጥታ ኃይሎች ተደናቅፏል። ባለሥልጣናት ወደዚያ ባለመምጣታቸው፤ እና ወደ መሰብሰቢያው ስፍራም እንዳያልፉ ያገዷቸው የፀጥታ ኃይሎች ላይ ወጣቶቹ ድንጋይ መወርወራቸውንም ዘገባው አመልክቷል። ሐዋሳ ከተማ ላይ በቁጣ ወደ ጎዳና የወጡት ዜጎች ጎማ በማቃጠል ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በተፈጠረው ግጭትም ቢያንስ የአንድ ሰው ሕይወት መጥፋቱን … [Read more...] about ሀዋሳ የጦርነት አውድማ አልሆነችም
በአብዲ ኢሌ መዝገብ ተከስሰው ያልተገኙ ስድስት ተከሳሾች ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ታዘዘ
በቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሃመድ መዝገብ በጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው ያልተገኙ ስድስት ተከሳሾች ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ የፌደራሉ ከፈተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት ትዕዛዝ ሰጠ። በተጨማሪም በአድራሻቸው ተፈልገው ያልተገኙ ሌሎች አምስት ተከሳሾች የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው አቃቤህግ ጠይቋል። መጥሪያ ላልደረሳቸው 23 ተከሳሾች መጥሪያ ለማድረስ የሚያስችል በቂ ጊዜ እንዲሰጠው አመልክቷል። ችሎቱ በአቃቤህግ ማመልከቻ ላይ ተገቢ ነው የሚለውን ትዕዛዝ ለመስጠት ለሀምሌ 17/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ሐሙስ ዕለት መቃወሚያ ባስገቡ ተከሳሾች ጉዳይ ብይን ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም የችሎቱ አንድ ዳኛ በእክል ምክንያት በስራ ገበታቸው ላይ ባለመገኘታቸው ብይኑን ለመስጠት ለሀምሌ 17/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ … [Read more...] about በአብዲ ኢሌ መዝገብ ተከስሰው ያልተገኙ ስድስት ተከሳሾች ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ታዘዘ
ኤች.አይ.ቪ./ኤድስ በአዲስ አበባ ወረርሽኝ ደረጃ ላይ ደርሷል
በአዲስ አበባ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭት 3 ነጥብ 4 በመቶ ደረሰ። በአዲስ አበባ ያለው የኤች አይ ቪ የስርጭት መጠን 3 ነጥብ 4 በመቶ መድረሱ ተገለፀ። የአዲስ አበባ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ፅ/ቤት ከአስሩም ክፍለ ከተማ እና ወረዳ ከተውጣጡ የጽህፈት ቤቱ ሰራተኞች ጋር የ2011 እቅድ አፈፃፀምን እየገመገመ ይገኛል። በግምገማው ላይም በከተማዋ ያለው የኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን እና አሁን ላይም 3 ነጥብ 4 በመቶ መድረሱ ተመልክቷል። ለዚህም በከተማዋ ያሉ አጋላጭ ቦታዎች መስፋፋት እና የስነ ምግባር ክፍተት ምክንያት መሆኑ ተነግሯል። በአለም ጤና ድርጅት መስፈርት መሰረት የኤች አይ ቪ ስርጭት ከ1 በመቶ በላይ ከሆነ ያ ሀገር በበሽታው ወረርሽኝ ውስጥ ነው። ይህም በከተማዋ ያለው የኤች አይ ቪ ስርጭት መጠን በጣም … [Read more...] about ኤች.አይ.ቪ./ኤድስ በአዲስ አበባ ወረርሽኝ ደረጃ ላይ ደርሷል
“የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ መታወጅ አለበት” የሐዋሳ ነዋሪ
ኤጄቶ ሁከት የሚያስነሳው ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት ነው አንድ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ አሁን በስልክ የነገረኝን ላካፍላችሁ። እሱ በሚኖርበት አከባቢ የተወሰኑ የሲዳማ ወጣቶች አንድ የቤትና ቢሮ ዕቃዎች መስሪያ ድርጅትን በእሳት ለማቃጠል ጥረት ያደርጋሉ። ነገር ግን የአከባቢው ማኅብረሰብ ተሯሩጦ ድርጊቱን ለመከላከል ይሞክራሉ። በዚህ መሃል የደቡብ ክልል ፖሊሶች በፓትሮል መኪና ከቦታው ይደርሳሉ። በድርጊቱ የተሳተፉ ወጣቶችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፈፅሞ አልሞከሩም። ከዚያ ይልቅ በዚህ የወንጀል ተግባር የተሰማሩትን ወጣቶች ከአከባቢው በቶሎ እንዲሸሹ በምልክት ይነግሯቸዋል። ወጣቶቹም መንገድ ለመዝጋት የደረደሩትን ድንጋይ እያነሱ ወደ ሌላ ቦታ ሄዱ። በኋላ ላይ የሌላ ምስኪን ነዋሪን ሃብትና ንብረት በእሳት ያወድማሉ። በአጠቃላይ ሐዋሳ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ የሚቀሰቀሰው ከክልሉ ፖሊሲ … [Read more...] about “የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ መታወጅ አለበት” የሐዋሳ ነዋሪ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ ክብረ ወሰን፤ በአንድ ቀን በ310 በረራ 29 ሺህ 528 መንገደኞችን አስተናገደ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በትላንትናው ዕለት ሐምሌ 10, 2011 ዓ.ም በአንድ ቀን ብቻ 310 በረራዎችን በማድረግ 29 ሺህ 528 መንገደኞችን በማጓጓዝ አዲስ ክብረ ወሰን ማሻሻሉን ገለጸ። አየር መንገዱ ለኢቢሲ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው አዳዲስ ዓለም አቀፍ ተሳፋሪዎች በአዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ በኩል መጓጓዝ ጀምረዋል። የቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ዳይሬክተር አቶ ጌታነህ አደራ የአየር ማረፊያውን አቅም ከሁለት እጥፍ በላይ የሚጨምረው አዲሱ ተርሚናል በከፊል መከፈቱን ገልፀዋል። በዚህ የክረምት ወቅት ብዛት ያላቸው ተሳፋሪዎችን ማጓጓዝ በመቻላችን በጣም ደስተኞች ነን ብለዋል። አየር መንገዱ በቅርቡ ባደረገው ማስፋፊያ በአመት 22 ሚሊዮን መንገደኞችን ለማስተናገድ የሚያስችል አቅም እንደፈጠረ ነው የተገለፀው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ … [Read more...] about የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ ክብረ ወሰን፤ በአንድ ቀን በ310 በረራ 29 ሺህ 528 መንገደኞችን አስተናገደ
አዴፓ ህወሓትን በልኩ በሚገባው ስም በመጥራት አዋርዶ ቀበረው
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት ሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ ብቸኛ ጠላት የሆነውን ህወሓት በሚገባው ስም መጠራት አለበት በማለት በተደጋጋሚ ሲወተውት ለመኖሩ ያለፉትን ጽሁፎች መመልከቱ በቂ ግንዛቤ ይሰጣል። በመሆኑም ህወሓት (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር) በሚለው የተገንጣይ ስሙ አገር በግፍ እየገዛ ያለ የወንበዴዎች ስብስብ ነው በማለት በዚሁ ስሙ እንዲጠራ ብዙ ብለናል። ይህ የአሸባሪዎችና በሞራል ዝቅጠት የመጨረሻው ደረጃ ላይ ባሉ ርካሾች የሚመራ የወሮበሎች ድርጅት በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን ያከለ ታላቅ አገር በንቀት እየገዛ ያለ ነው በማለት አትተናል። በመሆኑም ይህ በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች ቋት ውስጥ እስካሁን ድረስ ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መታደስ ሳይሆን መታገድና መክሰም ያለበት መሆኑንም አበክረን አሳስበናል። ይህ የእኛ ብቻ ሳይሆን የበርካቶች … [Read more...] about አዴፓ ህወሓትን በልኩ በሚገባው ስም በመጥራት አዋርዶ ቀበረው
የጄ/ል አበባው “ከፈለገ ይፈንዳ” ንግግር በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ ነው
ትግራይን የተቆጣጠሩ የቀድሞ አገዛዝ ርዝራዦች አሁንም ለዐቢይ ችግር ናቸው በባህርዳርና አዲስ አበባ በተቀናጀ መልኩ በተካሄደው የመፈንቅለ መስተዳድር/መንግሥት ህይወታቸውን ባጡት ጄ/ል ሰዓረ መኮንን አስከሬን ሽኝት ላይ በጄ/ል አበባው ታደሰ የተነገረው በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ መሆኑ ተሰማ። በአዲስ አበባ በቅድስት ሥላሴ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የጄ/ል ሰዓረ ቀብር ትግራይ መደረጉ ይህንኑ ተከትሎ ለተነሳው “እሣት” ማዳፈኛ ይሆን ዘንድ ለፖለቲካ ፍጆታ የዋለ መሆኑ ተገለፀ። በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊው ቲቦር ኒጌይ ትግራይ የመሸጉ የህወሓት ርዝራዦች አሁንም ለጠ/ሚ/ር ዐቢይ ችግር ፈጣሪዎች እንደሆኑ ተናገሩ። ህወሓትን በአደባባይ እንደሚያገለግል እየተናገረ መከላከያውን በኤታማዦር ሥልጣን ለረጅም ዓመታት ሲመራ የነበረው ሳሞራ የኑስን … [Read more...] about የጄ/ል አበባው “ከፈለገ ይፈንዳ” ንግግር በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ ነው
ህወሓት ወደ ስልጣን ለመመለስ የሎቢ ሥራውን ዳግም ጀምሯል
የተከበራችሁ የጎልጉል አንባቢያን፤ ለወራት ጠፍተን በመቆየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን። አንዱና ዋንኛው ምክንያት ድረገጻችን በማደስና የምናትማቸውን ጽሁፎች ባዲስ መልክ ለማድረስ እየሠራን ስለነበር ነው። ሥራው በፈቃደኝነት የሚሠራ በመሆኑ ካሰብነው ጊዜ በላይ ቢወስድብንም ባሁኑ ጊዜ በመጠናቀቅ ይገኛል። በቅርቡ አዲሱን ድረገጻችንን እናስተዋውቃለን። እስከዚያው ግን እዚሁ ላይ እንደተለመደው መረጃዎችን ማተማችንን እንቀጥላለን። በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁንና መልዕክቶች ለላካችሁልን ምስጋናችን የላቀ ነው። ከልብ እናመሰግናለን። ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ። በኢትዮጵያ ከፖለቲካው ቀውስ በማያንስ መጠን የኢኮኖሚው መላሸቅ፣ የሥራአጥነትና ድህነት የሚያስከትሉት አደጋ አሳሳቢና አደገኛ ሊሆን እንደሚችል ተጠቆመ። የለውጡ ኃይሎች ለውጡን በሚያደናቅፉ ላይ ፈጥነው እርምጃ አለመውሰዳቸው … [Read more...] about ህወሓት ወደ ስልጣን ለመመለስ የሎቢ ሥራውን ዳግም ጀምሯል
ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!
ህወሓት/ኢህአዴግ በግፍ ሲገዛት በነበረችው ኢትዮጵያ፣ አንድ ዓመት ያልሞላው የለውጥ ሒደት ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ባሉት ዘጠኝ ዓመታት (እኤአ 2003 – 2012) ባሉት ዓመታት ውስጥ 20ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ ከአገር ወጥቷል፤ ተዘርፏል። የሪፖርተሩ ብርሃኑ ፈቃደ ያቀናበረው እንዲህ ይነበባል፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ሥር የሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው የአፍሪካ የጤና ክብካቤና የኢኮኖሚ ዕድገት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ወደ ውጭ በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት አስታውቆ፣ ይህ ገንዘብ ለጤናው ዘርፍ የምታውለውን 87 በመቶ በጀት እንደሚሸፍን አመለከተ። ማክሰኞ የካቲት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ … [Read more...] about ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!










