Should Ethiopians Boycott the Upcoming Fake Election in Ethiopia? More Crackdowns Lock Out Opposition Groups from Political Participation “If we do not have a proper multiparty democracy, this country is going to end up like Somalia. This is imperative” he said. “It is up to the people to decide on how many seats should be given to the opposition and how many to the ruling party.” (Prime Minister Hailemariam Desalegn)[i] PRESS RELEASE. December 16, 2015. Washington, DC, The Solidarity … [Read more...] about Should Ethiopians Boycott the Upcoming Fake Election in Ethiopia?
Opinions
የኔ ሃሳብ
እውነትን ፈልጓት፤ ታገኟታላችሁም!!
በክፍል አንድ ጽሑፍ ውስጥ ለመግለጽ እንደተሞከረው ሁሉ እነዚህ ከእውነት ይልቅ ሃሰትን፤ ክቅንነት ይልቅ ተንኮልና ጭካኔን የመረጡ ጥቂት ካህናት ሕዝበ ክርስቲያኑን ለመከፋፈልና አንዱን ከሌላው ጋር በአስተሳሰብ አለያይቶ ለማጋጨት የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። ከዚህም ውስጥ በዚሁ በቅርቡ በፌስ ቡክ ላይ በለቀቁት ጽሑፋቸው በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የደረሰው ችግር “ሰዎች ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ጠንቅቆ ባለመረዳትና የራሳቸው ትርጉም በመስጠት.....” የሚል ጠቅሰዋል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) እውነትን ፈልጓት፤ ታገኟታላችሁም!! ክፍል አንድን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ ጸሃፊውን በዚህ አድራሻ ማግኘት ይቻላል: MaAyal@aol.com … [Read more...] about እውነትን ፈልጓት፤ ታገኟታላችሁም!!
ያለነፃነት የኢኮኖሚ ዕድገት አይኖርም!
የሰው ልጅ፣ ከሌሎች ፍጡራን በተለየ ከታደለው ፀጋ ውስጥ አንዱ ስልጣኔ ናፋቂ መሆኑ ነው፡፡ የሰው ልጅ የዝግመተ-እድገት ታሪክ የሚነግረን፣ አለም አሁን ለደረሰችበት የሀያ አንደኛው ክፍለ-ዘመን ስልጣኔ፣ መንስኤው ስልጣኔ ናፋቂ የሆነው የሰው ልጅ በየዘመኑ ያከናወናቸው እንቅስቃሴዎች ድምር ውጤት መሆኑን ነው፡፡ የሰው ልጅ፣ ከሌሎች የፈጣሪ ፍጡራን በተለየ ስልጣኔ ናፋቂ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ከሌሎች ፍጡራን በተለየ ፈጣሪ የማሰብ ፀጋ ስለቸረው ነው፡፡ “ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙላት” እንዲል ቃሉ፤ የሰው ልጅ ዘር መብዛቱን ተከትሎ፤ እንደ ህዝብ በቡድን መኖር ከመጀመሩ ጋር በተያያዘ የጋራ የሆነ ሀብትን ለመጠቀምም ሆነ እንደ ግለሰብ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ ፍትሀዊነት ህግ እና ደንብን ማእከል ያደረገ መንግስታዊ ስርአትን ተግባራዊ ማድረግ ከጀመረ እነሆ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ ይህም ለስልጣኔ … [Read more...] about ያለነፃነት የኢኮኖሚ ዕድገት አይኖርም!
ምርጫ ቦርድ፣ ማጭበርበሩን ያቁም!
በሕወሓት አመራርና አጃቢዎች የተፈበረከው ምርጫ ቦርድ ባለፉት 20 አመታት ለ4 ጊዜ ከፌደራል እስከ ቀበሌ ምርጫ አካሂዷል። ሁሉም ምርጫዎች ግን የዴሞክራሲ መስፈርትን የሚያሟሉ እንዳልነበሩ ዓለም-አቀፍ ታዛቢዎች ጭምር አረጋግጠዋል። በ2007 ዓ.ም የምርጫ ውድድርም ሕወሓቶች፣ በዚሁ አመት ሃቀኛ ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ጭራሹን ላለማሳተፍ፣ ለአመታት ያህል የቤት ስራ እየሰሩ ቆይተዋል፡፡ ለዚሁ አላማ ግቡን ለመምታት አስቀድመው እጅግ ብዙ ብቁ ምሁራንን እና ወጣት የፖለቲካ አመራሮችን “ለስልጣናችን አስጊ ናቸው” በማላት በሀሰት ወንጅለው አስረው በማሰቃየት ላይ ይገኛሉ። ብዙ የተቀናቃኝ ፓርቲዎች አባላት ላይም ስጋት ፈጥረዋል፤ ከትምህርትና ከስራም አፈናቅለዋል። ፓርቲዎችን ለመበታተን ብዙ ሰርጎ-ገቦችን በማስረፅ አለመተማመን በመፍጠር፣ እንዲከፋፈሉ ለማድረግ ብዙ ገንዘብ ረጭተዋል። ተቃናቃኝ … [Read more...] about ምርጫ ቦርድ፣ ማጭበርበሩን ያቁም!
የአምባገነኖች ፀሐይ ጠልቃለች!
በእኛ በኢትዮጵያ ህዝቦች ዘንድ ለ23 ዓመታት ተመዝኖ ቀሎብናል - ይህ የጥቂት ሽፍታዎች ቡድን! የመንግስትነት ስም ሊመጥነው የማይችል የውንብድናና የማፍያ ተግባር በ’መንግስትነት’ ሽፋን ሲራመድም ቆይቷል - ላለፉት ሁለት አስርታት፡፡ ዛሬ፡- ይህን በገሃድ የሚታይ ጥሬ-ሀቅ ያልተገነዘበ አንድም ኢትዮጵያዊ አይገኝ፡፡ ይህንን የጥቂቶች "የምዝበራ ፖለቲካል-ኢኮኖሚ" ለመሸፈን እና የተለየ ልባስ/ጭንብል ለማልበስ፤ እነዚህ መዝባሪዎች አያሌ ፎቆቻቸውን ከህዝብ በመዘበሩት የህዝብ አንጡራ-ሃብት አማካይነት ህዝብን ባፈናቀሉበትና ከቀዬው-በነቀሉበት በዚያው ስፍራ ላይ ለማቆም ችለዋል፡፡ ፎቆቻቸውን ያነፁት የእነርሱ-ዝርፊያ የሃገር-‘ልማት’ እንዲባልና በዚህም ሰፊው-ህዝብ ተደናግሮ ይህንን በአገር ላይ የሚሠራ "ጥፋት" በበጐ ጐኑ እንዲመለከተው ለማድረግ ነው፡፡ ‘ልማት’ እና የዘር-ልዩነት ላይ … [Read more...] about የአምባገነኖች ፀሐይ ጠልቃለች!
ቅዱስ ገብርኤል ሥነ ባህርይን (ሞራልን) አከበረ!
ታህሳስ 19 ቀን በቅዱስ ገብርኤል ስም የሚታሰበው በዓል፤ እግዚአብሔር ሥነ ባህርይን (ሞራልን) እንዲያከብር ቅዱስ ገብርኤልን የላከበት ቀን ነው። ማሳሰቢያ፦ በቅዱስ ገብርኤል ስም በየስርቻው ቤተ ክርስቲያን ከፍተው ህዝብን በመዝረፍ ላይ የሚገኙት ብዙዎቹ “ቅዱስ ገብርኤል ተከበረ እንጅ አከበረ ” የሚለውን ሰምተውት ስለማያውቁ፤ “ቅዱስ ገብርኤል አይከበር አለ ” እያሉ፤ አንብበው ከእውነቱ መድረስ የማይችሉትን አንዳንድ የዋሆችን ውዥንብር ውስጥ መክተታቸው አይቀርም። እኔ ኢትዮጵያን በመምራት ያሉ ፖለቲከኞችና በየስርቻው ቤተ ክርስቲያን የሚከፍቱትን የአስመሳይ ነጋዴዎች ባህርይ፤ አባቶች ስለበዓሉ አላማና ምክንያት ካስተማሩኝ ጋራ ሳንጻጽረው፤ ቅዱስ ገብርኤል ካከበረበት ምክንያትና ዓላማ ጋራ ምንም ግንኙነት እንደሌለው ገለጽኩ እንጅ ቅዱስ ገብርኤልማ ክብር ይገባዋል … [Read more...] about ቅዱስ ገብርኤል ሥነ ባህርይን (ሞራልን) አከበረ!
ኢትዮጵያና የካቲት 11 ቀን 1967 ዓ. ም.
ኢትዮጵያና የካቲት 11 ቀን 1967 በሚል ርእስ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ማቅረብ ተገቢ ነው ብዬ ተነሳሁ። የማቀርበውም ባጭሩ የሚከተሉትን በተመለከተ ይሆናል፤ የየካቲት 11 ቀን 1967 ዓላማ፤ ፖሊሲው፣ ለማን እና ለምን እንደተፈጠረ። ቅድመ የካቲት 1967 ዋናው አስኳሉ የተፈጠረው፣ ማሕበር ገስገስቲ ብሄረ ትግራይ (ማገብት) በ1965 አካባቢ በቀ. ኃ. ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ነው። በትምህርት ላይ የነበሩ የትግራይና የኤርትራ ተማሪዎች ተሰብስበው ያቋቋሙት ማህበር ነው። ይህ ማህበር እንደተፈጠረ የወሰድው አቋምና የሚከተለው ፖሊሲ፣ በረቀቀ መንገና ጥናት ጸረ ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት፣ የኢትዮጵያን ህዝብ አንድነት፣ ፍቅርና ስላም ለማፍረስ የወጠነ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ኹከትና ብጥበጥ እንዲፈጠር የወሰነ በባእዳን የተፈጠረ ማህበር ነው። ማገብት ገና በረሃ ሳይወጣ ያዘጋጀው ፖሊሲው፣ ኤርትራና … [Read more...] about ኢትዮጵያና የካቲት 11 ቀን 1967 ዓ. ም.
Talking to each other than taking about each other
Diverse Ethiopians in Minnesota find new and promising relationship as they step out of ethnic, religious, gender, and political boxes to embrace each other as valued human beings first. What does it mean—in real life—to appreciate the common bond of humanity above ethnicity or any other distinctions? If you had attended the recent SMNE Forum in Minnesota on December 6, 2014 that brought diverse Ethiopians together to talk to each other rather than about each other you would have seen it in … [Read more...] about Talking to each other than taking about each other
ፍትሕ አያረጅም! የኢትዮጵያና የአርሚኒያ ትግል
መግቢያ፤ ኢትዮጵያንና አርሚኒያን ከሚያመሳስሏቸው ጉዳዮች አንደኛው የአንድ ዓይነት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የእምነት መሠረት (ዶግማ) ተከታዮች ያሉባቸው ሐገሮች መሆናቸው ነው። በዚህ ጽሑፍ የማተኩርበት ተመሳሳይነት ግን ሁለቱም ሐገሮች በከባድ የጦር ወንጀሎች ተጠቅተው እያንዳንዳቸው ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተጨፈጨፈባቸው መሆኑ ነው። ሌላም እጅግ አስጸያፊ ግፍ የተፈጸመባቸው ሐገሮች ናቸው። በተጨማሪም፤ ሁለቱን ሐገሮች ያቀራረባቸው ሌላው ጉዳይ በኦቶማን ዘመነ መንግሥት፤ ከቱርኮች ግፍ በመሸሽ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት 40 አርመኖች ኑሯቸውን በሐገራችን መቀጠላቸው ነው። እነዚህ አርመኖችና ተወላጆቻቸው በኢትዮጵያ ተመቻችተው የኖሩና ብዙዎቹም አማርኛውን ያቀላጥፉ እንደ ነበር የታወቀ ነው። በዚህ አጋጣሚ፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት … [Read more...] about ፍትሕ አያረጅም! የኢትዮጵያና የአርሚኒያ ትግል
ሥነ-ኪን (ጥበብ) ጥቅሟና ገጽታዋ በሀገራችንና በተቀረው አፍሪካ
ኪነት (ሥነ-ኪን) በሀገራችን ለሀገራችን ጠቅማ የነበረውን ያህል የማንንም ሀገር አልጠቀመችም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በፈር ቀዳጅነት ማለቴ ነው፡፡ እንዴት ቢባል 1. እናት አባቶቻችን ሊሉ የፈለጉትን ነገር በጊዜውና ያለጊዜው በቦታውና ያለቦታው በመግለጽ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዴት ባለ መንገድ ልናሻግረው እንችላለን የሚል የጋለና የታመቀ ስሜት መነሣሣት እና መንፈሳዊ ፍላጎት ከውስጣቸው አቀጣጥላ የራሳችንን ፊደል እና አኃዝ ወይም ቁጥር መፍጠር መቅረጽ እንዲችሉ አድርጋለች፡፡ 2. በዓይነቱ ልዩ የሆነ የሰማያዊ እና መንፈሳዊ ጥዑመ ዜማ ባለቤት አድርጋናለች፡፡ 3. በዚህም ቀደምት እና ኅብረ ዝማሬንም ለዓለም እንድናስተዋውቅ አድርጋናለች፡፡ 4. ዓለም በድጋሚ ሊያንፃቸው ወይም ሊቀርጻቸው የማይችላቸውን ከወጥ አለቶች የተፈለፈሉ ውብና ድንቅ ረቂቅ የኪነ-ሕንፃ ውጤት የሆኑ … [Read more...] about ሥነ-ኪን (ጥበብ) ጥቅሟና ገጽታዋ በሀገራችንና በተቀረው አፍሪካ









