ከ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ዓመተ ምህረቱ የየካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት ጀምሮ፤ ለመብት፣ ለነፃነትና በሰላም ሠርቶ ለመኖር ያለው ትግል፤ ሳያርፍ በተከታታይ አሁንም እየተካሄደ ነው። በነዚህ ባለፉት ፵ ዓመታት፤ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፤ በትግሉ ከሕዝብ ጎን ተሰልፈው ሕይወታቸውን ሠጥተዋል። ቆራጥ የሕዝብ ጠበቃዎች ወጥተዋል፤ ሕይወታቸውን ላመኑበት ዓላማ በቆራጥነት በመሥጠት በጀግንነት ተቆጥረዋል። ትውልድ አልፎ ትውልድ ተተክቷል። በግለሰብ ደረጃ፤ አጥንት የሚሰብሩ፣ ደም የሚነውጡ፣ ልብ የሚነኩ፣ አንጀት የሚያንሰፈስፉ፣ ጀግንነት የተሞላባቸው ተግባራት ተከናውነዋል። ድርጅቶች ተነስተዋል፣ ወድቀዋል። በድርጅቶች ደረጃ፤ ሕዝባዊ ጉዳዮችን መልክ ባለው መንገድ አመቻችተው ባደባባይ አውጥተዋቸዋል። አባሎቻቸው ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍለውበታል። መሪዎቻቸው ከፍተኛ መሯሯጥን የኑሯቸው ማዕከል አድርገው … [Read more...] about መማር እንችላለን ወይ?
Opinions
የኔ ሃሳብ
በስዊድን የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር ራሱን አስተዋወቀ
የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር በስዊድን ተመስርቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በመግለጽ፤ የድጋፍ ማኅበሩ ቅዳሜ አፕሪል 4 ቀን 2015 ዓ.ም. (መጋቢት 26 ቀን 2007 ዓ.ም.) ራሱን አስተዋውቋል። በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ዓላማና ተግባርን ጥሪ ለተደረገላቸው ተሰብሳቢዎች ያስረዱት አቶ ሰለሞን ጌታነህ የድጋፍ ማኅበሩ ሰብሳቢ ናቸው። አቶ ሰለሞን በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በተደረገው የማስተዋወቁ ሥነሥርዓት ላይ ስለሰማያዊ ፓርቲ ሲያስረዱ፤ ሰማያዊ ፓርቲ በወጣት አባላት የተመሰረተና የሚመራ መሆኑን ገልጸው፤ ወጣቱ ደግሞ ከኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት ብልጫ ያለው እንደሆነና የወጣቱም ድጋፍ ሰማያዊ ፓርቲን እንዳልተለየው አሳውቀዋል። አያይዘውም ሰማያዊ ፓርቲ የዓላማ ጽናቱ የበረታ በመሆኑና በሀገር ውስጥ የሚያደርገውም እንቅስቃሴ እጅግ የጎላ ስለሆነ ፓርቲውን ሁላችንም መደገፍ ይገባናል … [Read more...] about በስዊድን የሰማያዊ ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር ራሱን አስተዋወቀ
Perspectives on the Declaration of Principles regarding the Grand Ethiopian Renaissance Dam
I. Introduction On March 23, 2015, Egypt, Ethiopia and the Sudan signed a declaration of principles on the Grand Ethiopian Renaissance Dam[2] (GERD). Since then, an intense debate has been going on regarding the modalities and core principles which were spelled out in the Declaration. Unfortunately, the principles contained in the Declaration have invited unhealthy rhetoric, particularly within Egypt, Ethiopia and among the Ethiopian diaspora. There are two fundamental reasons for the negative … [Read more...] about Perspectives on the Declaration of Principles regarding the Grand Ethiopian Renaissance Dam
ታሪክ ይፋረደናል!
እንደ እውነቱ ከሆነ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ገዥ ቡድን በእብሪት ተወጥሮ ሀገራችንን ሲጫወትባት፤ እኛ “የኔ ድርጅት! የለም የኔ ድርጅት!” “እኔ ልምራ እናንተ ተከተሉኝ! የለም እኔ ልምራ እናንተ ተከተሉኝ!” “እኔ እበልጣለሁ! የለም እኔ እበልጣለሁ!” እየተባባልን፤ በሌለ ሥልጣን ሽሚያ ልባችን አብጦ፤ ዛሬ ትናንት፤ ነገ ደግሞ ዛሬ እየሆነ ዓመታትን አስቆጠርን። ለምን? የሀገር ጉዳይ እያንዳንዳችንን የሀገሯ ተወላጆች እኩል አይሸነቅጠንም? ምን እስኪሆን ድረስ ነው የምንጠብቀው? በየድረገጹ የማነበው፣ በየፓልቶኩ ክፍል የማዳምጠው፣ በየሬዲዮኖች የሚተላለፈው፤ በአንድነት እስካልተነሳን ድረስ፤ ትግሉ አይሳካም! የነገውም ሂደት አያስተማምንም! ነው። ለምን በዚህ አውቶቡስ ሁላችን አንሳፈርም? ኧረ ተው! ታሪክ ይፋረደናል! አሜሪካ ፈልጌውና ጓጉቼለት የመጣሁበት ሀገር አይደለም። የዴሞክራሲ … [Read more...] about ታሪክ ይፋረደናል!
ስልጣን ላይ አድሮ ለመገኘት ሃገርን መሽጥ፤ ህዝብን መሸፈጥ ለምን? እስከመቼ?
የህወሃቱ መሪ መለስ ዜናዊ ሰሜን አፍሪቃ የተነሳሳው ህዝባዊ አመጽ በኢትዮጵያኖች ዘንድ መወያያ ርዕስ እንዳይሆንና አመጹም እንዳይዛመት "ዛሬን ስልጣን ላይ አድሮ መገኘት፤ ቀኑን እንዳመጣጡ ለማለፍ ስልት መቀየስ" በሚል እምነቱና ስልጣንን ከህዝብም ከሃገርም በላይ አምላኪነቱ የተነሳ: ለነገ ምን ችግር ያመጣል? ጉዳቱስ መጠኑና ስፋቱ ምን ያህል ይሆናል? ሃገር ሉዓላዊነትና ዘላቂ ብሄራዊ ጥቅም ላይ የሚኖረው አዎነታም ሆነ አሉታ ተጽዕኖ ሳያሳስበው ብልጭ ባለለት ማምለጫ መንገድ ብቻ የሚንቀሳቀሰው መለስ "አባይን እገድባለሁ" የሚል ቅዥት ይዞ ብቅ እንዳለ ሁላችንም እናስታውሳለን። ይህን ያልታሰበበት፤ ያልተጠና፤ ህዝብ ያላወቀውና መክሮ ያልተስማማበትን ቅዥት በየሙያው ዘርፉ አንቱ የተባሉና የሃገራቸው ጉዳይ የሚያሳስባቸው ተናገረውበታል፤ ጽፈውበታል አስጠንቅቀዋል፡ ህወሃት ግን የዕለት ስልጣንና … [Read more...] about ስልጣን ላይ አድሮ ለመገኘት ሃገርን መሽጥ፤ ህዝብን መሸፈጥ ለምን? እስከመቼ?
የት ሂዱ ነው?
ዓለም ሁሉ ጠላን፤ በየትም አገር እየሄድን "የሙጢኝ!" ከራሳችን መሬት በጉልበት እየተነቀልን፣ ከራሳችን ቤት እየተባረርን፤ ከተወለድንበትና ከአደግንበት አካባቢ እየተፈናቀልን፣ ጭራውን ቆልምሞ እንደሚሮጥ ባለቤቱ እንዳባረረው ውሻ በአገኘነው አቅጣጫ እየሮጥን፣ እጃችንን እያርገበገብን "የሙጢኝ!" እንላለን፤ የፈራነውን ሞት በየመንገዱ እናገኘዋለን፤ ሞትን ሸሽተን ሞት ያጋጥመናል፤ የሞቱ ልዩነት አይታየንም፤ በየመንገዱ የሚያጋጥመው ሞት የውርደት ሞት ነው፤ የብቸኛነት ሞት ነው፤ ዘመድ-ወዳጅ ለቀብር የማይገኝበት ሞት ነው፤ ሠለስት፣ አርባ፣ ሙታመት የማይወጣበት ሞት ነው፤ ባዕድ ምስጥ ያላሳደገውን አካል የሚበላበት ነው፤ የሞት ሞት ነው፡፡ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ከአገር አስወጥቶ ባዶ መሬት ብቻ ይፈልግ ይመስል የወያኔ ሎሌዎች በማስፈራራት ሁሉም አገሩን እየተወላቸው እንዲሄድ ያቀዱ ይመስላል፤ … [Read more...] about የት ሂዱ ነው?
የሮዶልፎ ግራዚያኒ የሚሊታሪ ሚዩዚየም በተመለከተ የተላለፈ ውሳኔ
የላዚዮ አውራጃ ኦፊሴያላዊ መግለጫ፤ (ቁ. 24/1) ዋና ዋና ነጥቦች (ዶ/ር ግርማ አበበ በኢጣልያንኛው ሰነድ መሠረት በእንግሊዝኛ ባቀረቡት መሠረት) ጉዳዩ፤ የአፊሌ ከተማ ማሕበራዊ ምክር ቤት ለማርሻል ሮዶልፎ ግራዚያኒ አፌሌ ስለ መረቀው ትንሽ የሚሊታሪ ሚዩዚየም፤ እ.አ.አ. ሐምሌ 21 ቀን 2012 ያስተላለፈውን ውሳኔ እንዲሰርዝ የቀረበ ጥሪ፤ በላዚዮ አውራጃ የተወሰደ እርምጃ እ.አ.አ. መጋቢት 13 ቀን 2015 እ.አ.አ. ሕዳር 11 ቀን 2004 የወጣውን የላዚዮን አውራጃ ሕግና ሌሎችንም ጉዳዮች በመመልከት፤ በተጨማሪም እ.አ.አ. በየካቲት 18 ቀን 2002 የወጣውን የክልሉን ሕግ በማስታወስ፤ የአፊሌ (ከተማ) ማሕበረሰብ ምክር ቤት እ.አ.አ. በሐምሌ 21 ቀን 2012 አንድ ትንሽ የሚሊታሪ ሚዩዚየም ለማርሻል ሮዶልፎ ግራዚያኒ እንዲመረቅ የወሰነ መሆኑን በማሰብ፤ ሮዶልፎ … [Read more...] about የሮዶልፎ ግራዚያኒ የሚሊታሪ ሚዩዚየም በተመለከተ የተላለፈ ውሳኔ
የቅማንት ክልል መመሥረትን በሶስት መንገዶች . . .
ጎንደር የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሳለሁ፤ ከጓደኞቼ መካከል ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ። አንድ ላይ የዘጠነኛ፣ የአስረኛና የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪዎች ነበርን። ግንብነህ አየለና አምባቸው አየለ ይባላሉ። በተለይ እሁድ እሁድ ማታ፤ ከዚያች በዚያ ወቅት ከነበረችው አንዲቷ ሲኒማ ቤት፤ ሲኒማ ጎንደር፤ የሚታዩትን ሲኒማዎች ለማየት፤ ከግማሽ ሰዓት በፊት ከአምባቸው አየለ ጋር ቆመን፤ (ሁለት ሜዟችንን -> አንድ ሽልንግ -> ሃምሳ ሳንቲም፤ በኪሳችን ቋጥረን) የሲኒማውን ማስታወቂያ ስዕሎችና ፎቶግራፎች እያየን፤ ከፎቁ ላይ የሚንቆረቆረውን የሬይ ቻርልስ “ኖ ሞር ኖ ሞር ጃክ” እየሰማን ስንጠብቅ ትዝ ይለኛል። ቀን ላይ፤ ሸጋዎቹ የዞብልና ባላጋራቸው የአፍሪቃ ቡድን እያለፉ ሌሎች ሲተኩ፤ እኒሁኑ ተተኪ ቡድኖች ሲጫወቱ ለማየት፤ ፋሲለደስ የእግር ኳስ ሜዳ ስለምንሄድ፤ የቀኑን ሲኒማ … [Read more...] about የቅማንት ክልል መመሥረትን በሶስት መንገዶች . . .
የርዕሰ አድናራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ
በእንግሊዝ ሃገር የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ገንዘብና ጉልበቱን አስተባብሮ በእግዚአብሔር ተራዳዒነት የገዛውን ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ለወያኔ ሹማምንት አሳልፈው በመስጠት ሥልጣንና ንዋይን የሚያጋብሱ የመሰላቸው የለንደኑ ዳያብሎስ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው፤ የቤተ ክርስቲያኑን አባላት መብት የሚነፍግ ተግባር ፈጽመው አባላቱ በቤተ ክርስቲያኗ ንብረት እኩል የመገልገል መብታቸው እንዲከበርላቸው ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት ወስደው በ13/02/2013 በዋለው የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ችሎት ተፈረደላቸው። ይህንን አስመልክቶ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ያስተላለፈውን ውሳኔና ያወጣውን ትዕዛዝ (interim relief order ) አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ተግባራዊ አናደርግም በማለታቸው የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ባለማክበረ (በContempt of Court) ተከሰው … [Read more...] about የርዕሰ አድናራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ
Yemen in our prayers
Poor Yemen is fast becoming the new playground of every wanabe strong Arab regime in the Middle East. Yemen is a safe location where they could test their acquired toys and pretend to act like a real army fighting real battles. Yemen never have it good. It was not blessed with oil, the only commodity that sustains the Arab monarchs’. Yemen came out from the womb staggering and never seem to have acquired this thing called stability, freedom and democracy. It is said long time ago the Axumite … [Read more...] about Yemen in our prayers









