ከሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ የትግሬ ወያኔ በጎንደር ዐማራ ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለው በዘር ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ፣ ከባለፉት 40 ዓመታት ጀምሮ ሲያደርገው የነበረው ጭፍጨፋና ዐማራን ከምድረገጽ የማጥፋት ዓላማው ተከታይ እንደሆነ ወያኔ የተጓዘበት ጉዞና የቆመለት ዓላማ በግልጽ ያሳያል። የጭፍጨፋው አጀማመርና ሂደት እንዲህ ነው፥ ከሃያ የሚበልጡ የወያኔ ልዩ ኃይል ፖሊሶች፣ ሐምሌ መጀመሪያ 2008 ዓም ላይ የትግሬው ገዥና የወያኔ ሊቀመንበር በሆነው ዐባይ ወልዱ ልዩ ትዕዛዝ ጎንደር ከተማ ገብተው የተለያዩ የስለላ ሥራዎችን ሢሠሩ እንዲቆዩ ተደረገ። የአፋኝ ቡድኑ አባሎች ወደ ጎንደር ከተማ እንዲገቡ የተደገበት ስበብ፣ የዐሥራ ሁለተኛ ክፍል የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን ለመቆጣጠር በሚል ምክንያት እንደሆነና እነርሱም ከሕዝቡ ጋር ባደሩት ግንኙነት ይኸንኑ የ«በሬ ወለደ» ወሬ ሲያዛምቱ … [Read more...] about በጎንደር ሕዝባዊ አመጽ ለመቀስቀሱ መሠረታዊው ምክንያት ወያኔ በሕዝቡ ላይ ለ25 ዓመታት የፈጸመው ግፍ ነው!
Opinions
የኔ ሃሳብ
ያዲሳባው ሽምቅ ውጊያ!
እንዴት ናችሁ!? ‹‹በዛሬዋ መሐል አዲስ አበባ መኪና ማቆምያ ማግኘት መኪና ከመግዛት ያልተናነሰ መታደልን ይጠይቃል›› በሚል ጦማሬን ልጀምር አስቤ ተውኩት፡፡ ለምን ተውኩት? ጠዋትና ማታ እንደ ፓስታ በተዝለገለገ የታክሲ ሰልፍ እግሩ ሸምበቆ እያከለ ለመጣ አዲስ አበቤ ዐረፍተ ነገሬ ቁጣን ይቀሰቅሳል ብዬ፡፡ የዛሬ አነሳሴ በአዲስ አበባ እየከፋ ስለመጣው የመኪና ማቆምያ ችግር ለመጻፍ ነበር፡፡ ሁለተኛ አንቀጽ ላይ ስደርስ የግዜርን ቁጣና የአንባቢን ተግሳጽ ፈርቼ ተውኩት፡፡ ነገሩ ለተራበ ሕዝብ ‹‹ኬክ የመጋገሪያ ስልቶች›› የሚል አጭር ስልጠና እንደመስጠት ሆኖብኝ ተውኩት፡፡ .እንዳዲሳባ ሕዝብ አንጀት የሚበላ አለ እንዴ? ከተማ ለመኖር በመፈለጉ ብቻ ፀሐይና ብርድ የሚፈራረቅበት አዲሳቤን የመሰለ ምስኪን ሕዝብ አለ? ካለ ንገሩኝ፡፡ ኡዝቤኪስታንም- ታጃኪስታንም ቢኬድ እንዳዲሳባ … [Read more...] about ያዲሳባው ሽምቅ ውጊያ!
የኢትዮጵያ ጉዳይ መጽሔት
መጽሔቱን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። … [Read more...] about የኢትዮጵያ ጉዳይ መጽሔት
የአሁኑ የተለየ ነው
በጎንደር እየተካሄደ ያለውን ሀቅ፤ ሁላችንም በተለያየ መልክ እየተከታተልን ነው። በኢትዮጵያ ያለው መንግሥት የማንና ምን አንደሆነ በግልጽ ታይቷል። ሕዝቡም የደረሰበትን የ”በቃኝ!” ደረጃ እያየን ነው። አሁን በፓልቶክና በደረገጽ፤ በሬዲዮና በቲቪ መወሰናችን ያበቃበት ሰዓት ነው። ይህ ትግል እስከዛሬ ከተደረጉት ማናቸውም ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች የተለየ ነው። በአኝዋክ ዘመዶቻችን አልቀዋል። በኦጋዴን ዘመዶቻችን ረግፈዋል። በኦሮሚያ ዘመዶቻችን ተገድለዋል። በተለያየ መልክ ሕዝቡ ምሬቱን ገልጿል። ከፍተኛ መስዋዕትነት ክፍሏል። ይህ ሁሉ ተደማምሮ አሁን የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ወልዶታል። አሁን፤ የእስከዛሬው ጥርቅም ብሶት ውጤት ነው ከኢትዮጵያ ሕዝብ ፊት የተደቀነው። የአሁኑ የተለየ ነው። በጎንደር የወልቃይትን ማንነት ይዞ የተነሳው ወገናችን ጥያቄ፤ የማንነት ብቻ ሳይሆን፤ የወራሪውን … [Read more...] about የአሁኑ የተለየ ነው
የክብር ዶክትሬት ክብሩን እያጣ ነው ተባለ
በሀገሪቱ ያሉ ዩኒቨርስቲዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየዓመቱ ለሁለትና ሶስት ሰዎች የክብር ዶክትሬት መስጠትን እንደ ልማድ መያዛቸው ከክብር ዶክትሬት መሰረታዊ አላማዎች ጋር የሚፃረርና ክብሩን የሚያራክስ ነው ሲሉ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለፁ፡፡ የክብር ዶክትሬት የሚሰጥባቸው መስፈርቶች በመርፌ ቀዳዳ ግመል እንደ ማሽሎክ ያህል ናቸው ያሉት ምሁራኑ፤ በአሁን ወቅት አዳዲስ ዩኒቨርሲቲዎች ጭምር ፉክክር በሚመስል መልኩ ዶክትሬቱን የሚሰጡበት አካሄድ በአስቸኳይ ሊታረም እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ የክብር ዶክትሬቱ የተሰጠባቸው ግለሰቦችም ለስም መጠሪያነት መጠቀማቸው ተገቢ አይደለም ያሉት ምሁራኑ፤ መገናኛ ብዙኃን የክብር ዶክትሬት የተሰጠውን ግለሰብ፤ “የክብር ዶክተር” እያሉ መጥራታቸውም አግባብ ባለመሆኑ ማረም ይኖርባቸል ብለዋል፡፡ የቋንቋና ስነ ፅሁፍ ምሁሩ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፤ ከሀገሪቱ … [Read more...] about የክብር ዶክትሬት ክብሩን እያጣ ነው ተባለ
የሕዝብ መብት የማያከብር መንግሥት በሕዝብ አመፅ ይወገዳል
ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ሥልጣኑን በጉልበት ወስዶ፣ የሕዝቡን መብት ገፎ፣ ያገሪቱን ሃብትና ንብረት የሚዘርፈው ቡድን ሥልጣኑና አድራጎቱ ዝንተ-ዓለማዊ እንደማይሆን ከወደቁትና ከተወገዱት ተመሳሳይ መንግሥታት ታሪክ ገና አልተማረም። ከፋፍዬ እኖራለሁ የሚለው ስልቱ እየተጋለጠ በየአቅጣጫው በሕዝብ ተቃውሞ እየተዋከበ ይገኛል። ወደ ታሪክ መቃብር የሚገባበት ቀን እያጠረ መጥቷል። አሁን በጎንደር ቀደም ሲል በሸዋ በተለያዩ ያኦሮሚያ ክልል አካባቢወች በጋምቤላና በሌሎቹም ያገሪቱ ክፍሎች የተነሳው ሕዝባዊ አመፅ ይህን የሚያመላክቱና ውድቀቱን የሚያፋጥኑ ተቃውሞዎች ናቸው።... ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ … [Read more...] about የሕዝብ መብት የማያከብር መንግሥት በሕዝብ አመፅ ይወገዳል
Perspectives on the Trilateral Agreement on the Grand Ethiopian Renaissance Dam:
This commentary is our fourth installment on the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD). It is sparked by the news item which was posted on the pro Tigrean People’s Liberation Front (TPLF) website, on July 9, 2016. Citing Sudan Tribune as its source, Aigaforum indicated what the Egyptian Minister of Water Resources and Irrigation, Mohamed Abdel Ati, is reportedly had said. The statement is related to the arrangement about the legal affairs of GERD. The news item states that “…a U.K. based law … [Read more...] about Perspectives on the Trilateral Agreement on the Grand Ethiopian Renaissance Dam:
የበጎው ሰው፣ የጎልማሳው ህልፈት…!
በያዝነው ሳምንት ... በአብዛኛው የሀበሻ መገናኛ መንደር፣ በማህበራዊ ድህረ ገጽ ዋንኛ መድረክ በ Facebook መስኮት አንድ መሪር መርዶ ተሰምቷል! የትሁት ፣ አስተዋይና አርቆ አስተዋዩ በጎ ሰው ፣ የጎልማሳው የአቡኬ አሌክስ ህልፈት!!! የአቡኬ አሌክስ በድንገት መለየት ጥልቅ ሀዘናን ሁላችንም አንገብግቦናል! "ከሞቱ አሟሟቱ " እንዲሉ አቡኬ ባንድ ጀንበር ታይቶ በርቶ ፣ ባንዱ ጀንበር ሳይታሰብ ጠፍቶብናል! እናም በቅርብ ከሚያውቁት ፣ ቤተሰብ ዘመድ አዝማድ ጓደኞች እኩል በስራው በዝና የምናውቀው በሀዘኑ አዝነን ከፍቶናል! የጎልማሳው በጎ ሰው አቡኬ አሌክስ መረጃዎች የቅርብ ተከታታይ የሆነችው ባለቤቴ በህልፈቱ ጥልቅ ሀዘን የተሰማቸው መካከል አንዷ ናት ፣ ስለአቡኬ ስትገልጽ እንዲህ ብላኛለች " አቡኬ ብሩህ አዕምሮ የነበረው ፣ ኢትዮጵያውያንን በዘር በሐይማኖታዊ ሳይለየን … [Read more...] about የበጎው ሰው፣ የጎልማሳው ህልፈት…!
የሀገሬ ዲሞክራሲያዊ የበቀል ፖለቲካ!
* የሰሜኑ ኮከብ አብርሃ ደስታ እንኳንም ተፈታህ! የሰሜኑ ኮከብ ወንድም አብርሃም ደስታ ከእስር እንደሚፈታ ቢገመትም ዘንድሮ ሲሆን እንጅ ሲባል ለማመን ተቸግሬያለሁና ዛሬን መቆየት ነበረብኝ ። እናማ የሰሜኑ ኮከብ ደፋሩና ለእውነት ግንባሩን የማያጥፈው የመቀሌው አብርሃም ደስታ " እውነት ተፈታ " ሲባል ሰማሁ ፣ ደስ አለኝ ! አብርሽ እንኳንም ከቤተሰብ ፣ ከዘመድ አዝማድና ወዳጅ አፍቃሪ ወገንህ ጋር ተቀላቀልክ እልሃለሁ ፣ አብርሽ! ከሁሉ አስቀድሞ አብርሃም ሃብታሙ ከተኛበት ሲጎበኘው የሚያሳየውን ምስል ስመለከት በደስታ ኩራት ስሜቴን መቆጣጠር አቅቶኝ ማንባቴ አልቀረም ... ሁለቱ ወንድሞች ገርድሰው የጣሉት ልዩነትና ህብረታቸው ሳውቀው ዛሬ እንደ ብርቅ ነገር አስደሰተኝ ! በዚህ ዛቢያ ስማስን የዘር ፖለቲካው ክፋት አንደርድሮ ወደ ሌላ አቅጣጫ ወረወረኝ ... ከምንም … [Read more...] about የሀገሬ ዲሞክራሲያዊ የበቀል ፖለቲካ!
THE UGLY FACE OF DOUBLE STANDARD
It is frequently heard that campaigners saying democracy has no colour. Oh yes it has! We have seen what had happened to our compatriot Andargachew Tsige, haven’t we? It is also being heard shouting slogans like, “Injustice anywhere is injustice everywhere!” Not true!!! Habtamu Ayalew is dying in hospital bed denied of going abroad to get treatment to save his life. In reality, nobody cares, until such a crime against humanity knocks at the doors of the interest of those whose voices matter. … [Read more...] about THE UGLY FACE OF DOUBLE STANDARD










