በአዲስ አበባ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭት 3 ነጥብ 4 በመቶ ደረሰ። በአዲስ አበባ ያለው የኤች አይ ቪ የስርጭት መጠን 3 ነጥብ 4 በመቶ መድረሱ ተገለፀ። የአዲስ አበባ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ፅ/ቤት ከአስሩም ክፍለ ከተማ እና ወረዳ ከተውጣጡ የጽህፈት ቤቱ ሰራተኞች ጋር የ2011 እቅድ አፈፃፀምን እየገመገመ ይገኛል። በግምገማው ላይም በከተማዋ ያለው የኤች አይ ቪ/ኤድስ ስርጭ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን እና አሁን ላይም 3 ነጥብ 4 በመቶ መድረሱ ተመልክቷል። ለዚህም በከተማዋ ያሉ አጋላጭ ቦታዎች መስፋፋት እና የስነ ምግባር ክፍተት ምክንያት መሆኑ ተነግሯል። በአለም ጤና ድርጅት መስፈርት መሰረት የኤች አይ ቪ ስርጭት ከ1 በመቶ በላይ ከሆነ ያ ሀገር በበሽታው ወረርሽኝ ውስጥ ነው። ይህም በከተማዋ ያለው የኤች አይ ቪ ስርጭት መጠን በጣም … [Read more...] about ኤች.አይ.ቪ./ኤድስ በአዲስ አበባ ወረርሽኝ ደረጃ ላይ ደርሷል
News
ዜና
“የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ መታወጅ አለበት” የሐዋሳ ነዋሪ
ኤጄቶ ሁከት የሚያስነሳው ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት ነው አንድ የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ አሁን በስልክ የነገረኝን ላካፍላችሁ። እሱ በሚኖርበት አከባቢ የተወሰኑ የሲዳማ ወጣቶች አንድ የቤትና ቢሮ ዕቃዎች መስሪያ ድርጅትን በእሳት ለማቃጠል ጥረት ያደርጋሉ። ነገር ግን የአከባቢው ማኅብረሰብ ተሯሩጦ ድርጊቱን ለመከላከል ይሞክራሉ። በዚህ መሃል የደቡብ ክልል ፖሊሶች በፓትሮል መኪና ከቦታው ይደርሳሉ። በድርጊቱ የተሳተፉ ወጣቶችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፈፅሞ አልሞከሩም። ከዚያ ይልቅ በዚህ የወንጀል ተግባር የተሰማሩትን ወጣቶች ከአከባቢው በቶሎ እንዲሸሹ በምልክት ይነግሯቸዋል። ወጣቶቹም መንገድ ለመዝጋት የደረደሩትን ድንጋይ እያነሱ ወደ ሌላ ቦታ ሄዱ። በኋላ ላይ የሌላ ምስኪን ነዋሪን ሃብትና ንብረት በእሳት ያወድማሉ። በአጠቃላይ ሐዋሳ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ የሚቀሰቀሰው ከክልሉ ፖሊሲ … [Read more...] about “የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ መታወጅ አለበት” የሐዋሳ ነዋሪ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ ክብረ ወሰን፤ በአንድ ቀን በ310 በረራ 29 ሺህ 528 መንገደኞችን አስተናገደ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በትላንትናው ዕለት ሐምሌ 10, 2011 ዓ.ም በአንድ ቀን ብቻ 310 በረራዎችን በማድረግ 29 ሺህ 528 መንገደኞችን በማጓጓዝ አዲስ ክብረ ወሰን ማሻሻሉን ገለጸ። አየር መንገዱ ለኢቢሲ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው አዳዲስ ዓለም አቀፍ ተሳፋሪዎች በአዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ በኩል መጓጓዝ ጀምረዋል። የቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ዳይሬክተር አቶ ጌታነህ አደራ የአየር ማረፊያውን አቅም ከሁለት እጥፍ በላይ የሚጨምረው አዲሱ ተርሚናል በከፊል መከፈቱን ገልፀዋል። በዚህ የክረምት ወቅት ብዛት ያላቸው ተሳፋሪዎችን ማጓጓዝ በመቻላችን በጣም ደስተኞች ነን ብለዋል። አየር መንገዱ በቅርቡ ባደረገው ማስፋፊያ በአመት 22 ሚሊዮን መንገደኞችን ለማስተናገድ የሚያስችል አቅም እንደፈጠረ ነው የተገለፀው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ … [Read more...] about የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ ክብረ ወሰን፤ በአንድ ቀን በ310 በረራ 29 ሺህ 528 መንገደኞችን አስተናገደ
የጄ/ል አበባው “ከፈለገ ይፈንዳ” ንግግር በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ ነው
ትግራይን የተቆጣጠሩ የቀድሞ አገዛዝ ርዝራዦች አሁንም ለዐቢይ ችግር ናቸው በባህርዳርና አዲስ አበባ በተቀናጀ መልኩ በተካሄደው የመፈንቅለ መስተዳድር/መንግሥት ህይወታቸውን ባጡት ጄ/ል ሰዓረ መኮንን አስከሬን ሽኝት ላይ በጄ/ል አበባው ታደሰ የተነገረው በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ መሆኑ ተሰማ። በአዲስ አበባ በቅድስት ሥላሴ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የጄ/ል ሰዓረ ቀብር ትግራይ መደረጉ ይህንኑ ተከትሎ ለተነሳው “እሣት” ማዳፈኛ ይሆን ዘንድ ለፖለቲካ ፍጆታ የዋለ መሆኑ ተገለፀ። በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊው ቲቦር ኒጌይ ትግራይ የመሸጉ የህወሓት ርዝራዦች አሁንም ለጠ/ሚ/ር ዐቢይ ችግር ፈጣሪዎች እንደሆኑ ተናገሩ። ህወሓትን በአደባባይ እንደሚያገለግል እየተናገረ መከላከያውን በኤታማዦር ሥልጣን ለረጅም ዓመታት ሲመራ የነበረው ሳሞራ የኑስን … [Read more...] about የጄ/ል አበባው “ከፈለገ ይፈንዳ” ንግግር በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ ነው
ህወሓት ወደ ስልጣን ለመመለስ የሎቢ ሥራውን ዳግም ጀምሯል
የተከበራችሁ የጎልጉል አንባቢያን፤ ለወራት ጠፍተን በመቆየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን። አንዱና ዋንኛው ምክንያት ድረገጻችን በማደስና የምናትማቸውን ጽሁፎች ባዲስ መልክ ለማድረስ እየሠራን ስለነበር ነው። ሥራው በፈቃደኝነት የሚሠራ በመሆኑ ካሰብነው ጊዜ በላይ ቢወስድብንም ባሁኑ ጊዜ በመጠናቀቅ ይገኛል። በቅርቡ አዲሱን ድረገጻችንን እናስተዋውቃለን። እስከዚያው ግን እዚሁ ላይ እንደተለመደው መረጃዎችን ማተማችንን እንቀጥላለን። በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁንና መልዕክቶች ለላካችሁልን ምስጋናችን የላቀ ነው። ከልብ እናመሰግናለን። ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ። በኢትዮጵያ ከፖለቲካው ቀውስ በማያንስ መጠን የኢኮኖሚው መላሸቅ፣ የሥራአጥነትና ድህነት የሚያስከትሉት አደጋ አሳሳቢና አደገኛ ሊሆን እንደሚችል ተጠቆመ። የለውጡ ኃይሎች ለውጡን በሚያደናቅፉ ላይ ፈጥነው እርምጃ አለመውሰዳቸው … [Read more...] about ህወሓት ወደ ስልጣን ለመመለስ የሎቢ ሥራውን ዳግም ጀምሯል
ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!
ህወሓት/ኢህአዴግ በግፍ ሲገዛት በነበረችው ኢትዮጵያ፣ አንድ ዓመት ያልሞላው የለውጥ ሒደት ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ባሉት ዘጠኝ ዓመታት (እኤአ 2003 – 2012) ባሉት ዓመታት ውስጥ 20ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ ከአገር ወጥቷል፤ ተዘርፏል። የሪፖርተሩ ብርሃኑ ፈቃደ ያቀናበረው እንዲህ ይነበባል፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ሥር የሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው የአፍሪካ የጤና ክብካቤና የኢኮኖሚ ዕድገት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ወደ ውጭ በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት አስታውቆ፣ ይህ ገንዘብ ለጤናው ዘርፍ የምታውለውን 87 በመቶ በጀት እንደሚሸፍን አመለከተ። ማክሰኞ የካቲት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ … [Read more...] about ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!
በእስር ቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም፤ ኮምፒውተር እንፈልጋለን – በረከት ስምዖን
በሌብነት የተጠረጠሩት በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሣ አርብ በባህር ዳርና አካባቢዋ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። በዕለቱ ሁለቱም ግለሰቦች ያሉባቸውን ችግሮች ያስረዱ ሲሆን በተለይ በረከት ስምዖን በእስርቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም ሲል ማማረሩን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ኮምፒውተር ያስፈልገናልም ብለዋል። በዕለቱ የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ባለፈው በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ማስረጃዎችን ማየቱንና የምስክሮችን ቃል መቀበሉን አሳውቋል። ሆኖም ጉዳዩ ከባድ፣ ውስብስብና ድንበር ተሻጋሪ ከመሆኑም በላይ ምስክሮች እና ሰነዶች በሃገር ውስጥ እና ከሃገር ውጪ መገኘታቸውን አስታውሶ ምርመራውን ባለማጠናቀቁ ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል። በወቅቱ የቀረበውን ማራዘሚያ ቀን በረከት የተቃወመ ሲሆን ያቀረበው ምክንያትም የሕግ ሥልጣን በሌለው አካል መከሰሰሱን ነው። ይህ ሕጋዊነት … [Read more...] about በእስር ቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም፤ ኮምፒውተር እንፈልጋለን – በረከት ስምዖን
የአል አሙዲ ሃብት በ9.7 ቢሊዮን ዶላር ወደረ!
የኢትዮጵያን ሃብት ከህወሓት ጋር በጥቅም በመመሳጠር ሲበዘብዝ የነበረው መሐመድ አለ አሙዲ (አላሙዲ) እጅግ በርካታ ገንዘብ ከፍሎ በሌብነት ከታሰረበት ሳዑዲ አረቢያ መለቀቁ ተሰምቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ሲታሰር 10.9 ቢሊዮን ዶላር የነበረው ሃብቱ ሲፈታ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። በፎርብስ ደረጃ አሠጣጥ መሠረት ከእስር በኋላ የ159ኛ ደረጃ ሰጥቶታል። ሆኖም ፎርብስ የአላሙዲ ሃብት በእርግጥ የእርሱ መሆኑን ማረጋገጥ ስላልቻለ በ2018 ከዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ አውጥቶታል። በርካታዎች እየሞቱና መብታቸው ተገፍፎ በእስር እየማቀቁ በነበሩበት ወቅት የንብ ካኔተራ በመልበስ የህወሓት ደጋፊነቱን በገሃድ ያስመሰከረው አላሙዲንን ከህወሓት ለይቶ “የሕዝብ ሰው” አድርጎ ማቅረብ ለህወሓት ያለን “ጥላቻ” ከአላሙዲ “ትግሬ” አለመሆን ጋር የተገናኘ ይመስላል የሚሉ ጥቂቶች … [Read more...] about የአል አሙዲ ሃብት በ9.7 ቢሊዮን ዶላር ወደረ!
የሎሬት ፀጋዬ ማዕከል ሊቋቋም ነው
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ በሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን ስም የባህል ማዕከል እንደሚያቋቁም አስታውቋል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታደሰ ቀነዓ ለኢዜአ እንደገለጹት ማዕከሉ የሚቋቋመው የሎሬቱን ጨምሮ በኪነ ጥበብ ሥራዎች ላይ ጥናትና ምርምር ለማድረግና ተሰጥኦ ያላቸውን ጠቢባን ለማፍራት ነው። “ማዕከሉን ለሟቋቋም ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ ተገብቷል” ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ማዕከሉን ለማቋቋም ከአዲስ አበባ፣ ከባህር ዳርና ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ልምድ ቀስሟል ብለዋል። ከሎሬት ጸጋዬ ወጥ ሥራዎች መካከል የአቴቴ ሥርዓት፣ የገዳ ሥርዓት፣ ዝክረ መርካቶ፣ የኩሽ ሕዝቦች ሥልጣኔ፣ ዳግማዊ ቴዎድሮስ፣ ኦዳና አቡነ ጴጥሮስን የሚዘክሩት ተጠቃሽ ናቸው። ከትርጉም ሥራዎቻቸው መካከል የዊሊያም ሼክስፒር ድርሰቶች ሃምሌትና ኦቴሎ ዘመን ተሻጋሪ ሥራዎች ይገኙበታል። የአምቦ አካባቢ ተወላጅ የሆኑት ሎሬት … [Read more...] about የሎሬት ፀጋዬ ማዕከል ሊቋቋም ነው
ከአገር ሊሸሽ የነበረው ወርቅና ገንዘብ ወደ ብሔራዊ ባንክ ገብቷል
በቁጥጥር ስር የዋለው ወርቅና የ13 ሀገራት ገንዘብ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደረገ። በቶጎ ውጫሌ የመቆጣጠሪያ ጣቢያ ላይ ኮድ 3 ኦሮ የሰሌዳ ቁጥር 63100 አይሱዚ ጫት ጭኖ ወደ አርጌሳ እየተጓዘ በነበረበት ወቅት ጥር 28 ቀን 2011 ከሌሊቱ 9፡00 አካባቢ 7 ኪሎ ግራም የሚመዝን ወርቅ በቁጥጥር ስር መዋሉ ይታወሳል። በቁጥጥር ስር የዋለው ወርቅና የውጭ አገራት ገንዘብ በመከላከያ ሠራዊት አባላት ታጅቦ ትናንት ምሽት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የደረሰ ሲሆን በዛሬው ዕለት (ሐሙስ) ደግሞ ብሔራዊ ባንክ ትክክለኛነቱን አረጋግጦ ተረክቦታል። በተመሳሳይ የውጭ አገራት ገንዘብ ትክክለኛነታቸው ተረጋግጦና ተቆጥሮ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል። በአራት ዓይነት መጠን (Bar) የተዘጋጀው ወርቅ 21.7፣ 21.75፣ 22.5 እና 22.34 ካራት መሆናቸውን በብሔራዊ ባንክ የተረጋገጠ ሲሆን … [Read more...] about ከአገር ሊሸሽ የነበረው ወርቅና ገንዘብ ወደ ብሔራዊ ባንክ ገብቷል










