• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አንተ ሌባ – አንቺ ሌባ” – የመቀሌው ሽኩቻና የህወሃት የውድቀት አፋፍ

November 16, 2017 11:30 pm by Editor Leave a Comment

መቀሌ ወሩን ሙሉ ውጥረት ውስጥ ከርማለች። ከተማዋ ላይ እየወረደ ያለው ዶፍ የሚያባራ አይመስልም። የህወሃቶቹ የዘንድሮ መሰባሰብ ለጤና እንዳልነበረ ግልጽ ነው። ሰዎቹ እንደወትሮው “በሃገር ጉዳይ ላይ” ለመዶለት ወደ መቀሌ አልተጓዙም። ቀደም ሲል ጠላታችን ድህነት ነው ሲሉን ነበር። አሁን ግን ለሁለት ተቧድነው አንዱ ሌላውን ጠላት ሲል ይሰማል።

በግል ጸብ ለሁለት መሰንጠቃቸው የአደባባይ ምስጢር ይሁን እንጂ፤ እርቅ እና ሰላም በአጀንዳቸው ውስጥ አልተካተተም። ሃገሪቱ የገባችበትን ችግር ወደጎን ትተው፣ “አንተ ሌባ – አንቺ ሌባ” ሲባባሉ እንደከረሙ ነው እየተሰማ ያለው። ይህንን የማይታረቅ ቅራኔ ይዘው አብረው ስለማይዘልቁ የአንዱ ቡድን ማሸነፍ ግድ ይላል።

በዚህ ‘ታሪካዊ’ ስብሰባ የሙስና እና የሌብነት ፋይሎች ተጠርዘው ቀርበዋል። ህወሃቶች አፍ አውጥተው “በስብሰናል”ም ብለዋል። እንደ አጀንዳ በቀረቡ በነዚህ የክስ ፋይሎች ላይ ድምጽ ተሰጥቶባቸዋል።

ስብሰባውን እየረገጡ የወጡት ወንጀል ሲዶለትባቸው የነበሩትና “ተሸናፊ” ህወሃቶች ናቸው። በሃብታቸው ብዛት “ቀዳማዊት እመቤት” የተባሉት አዜብ መስፍን የመጀመሪያው ስብሰባ ረጋጭ መሆናቸውን ሆርን አፌይርስ ከውስጥ ምንጭ ጠቅሶ ዘግቧል።

አዜብ ተከትለው ስብሰባውን እየረገጡ የወጡት የነ ስዬ አብርሃን ጽዋ ይቅመሱ አይቅመሱ ገና ባይታወቅም፣ ዛቻውና ጥርስ መናከሱ መቀጠሉን ግን የመቀሌ ምንጮች ገልጸዋል።

ወሩን ሙሉ መቀሌ ላይ ከትመው ሲጠዛጠዙ ውለው ሲጠዛጠዙ መሰንበታቸውን እነዚሁ ምንጮች ጠቁመዋል። ግምገማው ቀድሞ እንደሚያደርጉት አንዱ ባንዱ ላይ ጣት መሰባበቅን አልፎ፣ በተራ ስድብ እና ዘለፋ የታጀበ ነው። አጀንዳቸው ብሄራዊ ጉዳይ ቢሆን ባልከፋ ነበር። እጅግ የሚያሳፍረው ጸቡ እኔ እበልጥ፣ የግል መሆኑ ነው። ሌቦች የሚጋጩት ሲሰርቁ ሳይሆን ሲካፈሉ ነው ይባል የለ።

አቶ ሀብቶም ገ/እግዚያብሄር የህወሃቱ ድረገጽ በሆነው አይጋ ፎረም ላይ ኢህአዴግ ያለበት መንታ መንገድ እና የሀገራችን እጣ ፈንታ! በሚል የለቀቁት ያልተለመደ ጽሁፍ ከወዲያ እየነደደ ያለውን እሳት ይጠቁመናል። አይቴ ሃብቶም ስለዛሬው መግማማትና የሌቦች ፖለቲካን ክፉኛ ይኮንናሉ። ዛሬ ብቸኛው የመክበሪያ መንገድ ወይ የመንግስት ስልጣን መያዝ ወይ ከመንግስት ባለስልጣን መጠጋት እሳቤ መሆኑን እና ለዚህም ሙሉ ተጠያቂው ኢህአዴግ የሚመራው መንግስት ነው ይላሉ።

እርግጥ ነው። በህወሃት ውስጥ ሽኩቻ እና መጠላለፍ አዲስ አይደለም። የከዚህ ቀደሙን ተመክሮ እንዳየነውም፤ ስብሰባ ረግጦ መውጣት ለችግሮቹ መፍትሄ አልሆነም። ከ16 አመት በፊት እነ አቶ ገብሩ አስራት፣ አረጋሽ አዳነ፣ ስዬ አብርሃ፣ ፃድቃን ገ/ተንሳኤ የመለስን ሰነድ አንቀበልም ብለው ስብሰባ ረግጠው ነበር። እነ ስዬ በወቅቱ አብዛኛ ድምጽ ነበራቸው። ግና ማኬቬሊያዊው መለስ ቀደማቸውና እንደወጡ በዚያው ቀሩ።

አሁን መለስ የለም። ጸቡም የውስጥና የርስበርስ ብቻ አይደለም። ሽኩቻው ከሕዝብ ጋርም ነው። ከ90 ሚሊዮን ሕዝብ ጋር። የከረረው ክፍፍል ከህዝብ እንቢተኝነት ጋር ተደምማሮ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ታምራት ገለታን መጠየቅ አያስፈልግም።

ፋይዳ ላይኖረው፣ እንዲሁ ሲቀያየሩ መሰንበታቸው “ስልቻ ቀልቀሎ…” ይሁን እንጂ፣ የኑሮው ውድነት፣ ከጣና ኬኛ ፖለቲካ እና የሼኩ ያልጠጠበቀ መታሰር፣… ተደማምሮ ለውጥ ፈልጎ ለተነሳው ኃይል በር መክፈቱ ግልጽ ነው። (ፎቶው ከHorn Affairs የተወሰደ ነው – አባይ ወልዱና ደብረጽዮን የመቀሌውን የህወሃት ስብሰባ ሲመሩ)

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule