• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢህአዴግ የመጨረሻ ጉባኤ…

September 30, 2018 06:26 pm by Editor Leave a Comment

ኢህአዴግ መሽቶበታል። አቅሙ ክዶታል። ባልሞት ባይ ተጋዳይነት አለሁ ቢልም ዘላለማዊ ዕንቅልፉ ግን የሚቀርለት አይመስልም።

የሜክሲኮውን ፒ አር አይ ፓርቲ አርአያው አድርጎ ሰባ አመታትን እጓዛለሁ ብሎ የተነሳው ድርጅት ግማሽ መንገድ እንኳን ሳይጓዝ ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል። ገዥው ፓርቲ ውስጥ ያለው የርዕዮተዓለም ልዩነት በማይታረቅ መንገድ የአደባባይ ሙግት ጀምሯል።

ኦዲፒ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ መማል ካቆመ ቆይቷል። ሊቀመንበሩ ዓብይ አህምድም (ዶ/ር) ከትናንት ጋር የተኳረፉት ለዚህ ይመስላል። ብአዴን የምመራበትን ርዕዮተ ዓለም ዳግም አጤነዋለሁ ብሎ ዛሬ መወያየቱን ጀምሯል (ይህ ዘገባ ከተጻፈ በኋላ ብአዴን አዴፓ በሚል ህወሓት የሰጠውን ቀይሮታል)። ከዚህ በአንጻሩ ህወሓት አብዮታዊ ዲሞክራሲን ብረሳ ቀኜ ትርሳኝ ብሎ ሙጥኝ ማለትን ወዷል። ደኢህዴን ሁለት ጎራ ይዞ የለየለት ፍልሚውን ቀጥሏል።

የኢህአዴግ እህት ድርጅቶችን የተካረረ አቋም ለተመለከተ ሰው ኢህአዴግ በመፍረስ ጫፍ ላይ መሆኑን በውሉ ይረዳል። የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር አንድ የፖለቲካ ፕሮግራም ያስተሳሰረው ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። ይህ ፕሮግራም ሁሉንም እህት ድርጅቶች ለአንድ ዓላማ ያሰለፈ የህልውና መገለጫ ተደርጎ የሚቆጠር ነው።

አብዮታዊ ዲሞክራሲ የሚል የዳቦ ስም ያለው ይህ የግንባሩ መሰሶ ከተናጋ ቤቱ መናዱ እንደማይቀር ዕሙን ነው። ለዚህ ደግሞ የድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ ትልቅ ምስክር ነው።

ኢህአዴግ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ “ኢህአዴግ የሚመራባቸው አጠቃላይ የአደረጃጀት መርሆዎች” በሚል ንዑስ ርዕስ ስር “ኢህአዴግ ለአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አላማ ተግባራዊነት የሚንቀሳቀስ ድርጅት ስለሆነ በአባልነት ሊቀበልና ሊያሰባስብ የሚችለው አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አላማን በግልፅ በፕሮግራማቸው ላይ የቀረፁ ድርጅቶችን ብቻ ነው”ይላል። የገዥው ፓርቲ የአባልነት መሰፈርት የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፕሮግራምን ዓላማ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በውሉ ለተግባራዊነቱ መረባረብን ይጠይቃል። ይህ የፓርቲው ምሰሶ ዛሬ እንደ ደመራ በአንድ አቅጣጫ ዘሟል። የሚጠበቀውም መቼና በየት በኩል ይወድቃል የሚለው ብቻ ነው።

በየት በኩል ይወድቃል?

ኢህአዴግ በወረቅት ላይ ለጋስ ፓርቲ ከሚባሉት ተርታ የሚሰለፍ ነው። በዚህ ምክንያትም ማንም እህት ድርጅት ከኢህአዴግ አባልነት በፈለገው ጊዜ መውጣት እንደሚችል በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ አስፍሯል። በድርጅቱ ህግ አንቀጽ 13/2 ሀ. “ማንኛውም የግንባሩ አባል የሆነ ድርጅት ለግንባሩ ምክር ቤት አሳውቆ በፈለገው ጊዜ ድርጅቱን መልቀቅ ይችላል” ይላል። ዛሬ ኢህአዴግ ቤት ያለው መፈራራት ማን ቀድሞ እንዲህ ያለውን ኃላፊነት ይወስዳል የሚለው ነው። ነገርየው ደመራው በየት በኩል ይወድቃል የሚልን ጉጉት ያጭራል።  ከዚህ ከፍ ሲልም ከኢህአዴግ ቤት የወጣ ድርጅት ከማን ጋር ተጣምሮ መንግስት ሊመሰርትስ ይችላል የሚል ጥያቄም ያስከትላል።

ብዙዎች ኢህአዴግ ከወደቀ የሚወደቀው በኦዴፓ አልያም በብአዴን (በአሁኑ አዴፓ) በኩል ነው የሚል ሀሳብ ይሰነዝራሉ። ኢህአዴግ ከፈረሰ በኋላም በጥምረት መንግስት የመመስረት ያላቸው ክልል ተሻጋሪ አጀንዳ ያላቸው ፓርቲዎች እነሱ ናቸው ይላሉ። ይህ ግን ከፖለቲካ ካፒታል ጽንሰ ሀሳብ አንጻር ከተመለከትነው ትልቅ ስህተት የሚሆን ይመስለኛል። ሁለቱ ድርጅቶች የየአካባቢያቸውን ህዝብ ድጋፍ ለማግኘት የሚሄዱበት መንገድ ለየቅል ነው። የሁለቱ ክልል ፖለቲካ ልሂቃን የብሄርተኝነት አረዳዳም በሁለት ጫፍ ላይ የቆመ ነው።

ሊበራሊዝም ርዕዮተ ዓለም ጥላ ሁኖ ያስተሳስራቸዋል የሚለው ግምትም ከብሄር ወደ መደብ ላልተሸጋገረ ህዝብ ፖለቲከኛ የሚያዋጣ አይደለም። ከዚህ አንጻር ሁለቱ ፓርቲዎች ከኢህአዴግ ቤት ከመውጣት በላይ አንድ ሊያደርጋቸው የሚችል የፖለቲካ ርዕዮትን የመንደፍ ከባድ የቤት ስራ ይጠብቃቸዋል።

በእኔ ግምት የኢህአዴግን የዘንድሮውን ጉባዔ ለየት የሚያደርገው በዚህ አጣብቂኝ መኃል መገኘቱ ነው። ዛሬ ላይ ቢያንስ አንድ ነገርን በእርግጠኝነት መናገር የሚቻል ይመስለኛል። ኢህአዴግ በ2013 ዓ.ም የሚያደርገው ጉባዔ እንደቀደመው ጊዜው አራት እህት ድርጅቶቹን ይዞ የሚካሄድ አይሆንም።

ይህ ከዛሬ ነባራዊ ሁኔታ በመነሳት የሚደረግ የፖለቲካ እንድምታ ነው። ይህ የእንድምታ ፍካሬ ግን ብቸኛ አይደለም። የገዥው ፓርቲ አፈለኛ አመራር ከርዕዮተ-ዓለም በላይ የስልጣን ጥቅም ያስተሳሰረው ከሆነ ኢህአዴግ የጣር ድምጽ እያስማም ቢሆን ሊጓዝ ይችላል። እንዲህ ያለው መንገድ ግን የኢትዮጵያን ፖለቲካ በተቃዋሚዎች ብቻ ሳይሆን በኢህአዴግ ውስጥ ባለ አለመግባባትም ወደለየለት ምስቅልቅል ይወስደዋል። የሀገር ህልፈትንም ሊያስከትል ይችላል። (ማዕረግ ጌታቸው በድሬቲዩብ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule