• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የገዱ አንዳርጋቸው ፈተና

December 22, 2017 03:27 pm by Editor Leave a Comment

በህወሓት ተመልምለውና ለሥልጣን በቅተው ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ “የለውጥ ኃይል” እየተባሉ ከሚወደሱት መካከል አንዱ የሆነው ገዱ አንዳርጋቸው ለምስክርነት መጥሪያ ተቆርጦለታል። ገዱና ሌሎች ህወሓት እንደ ጭቃ ጠፍጥፎ የሠራው ብአዴን አባላት የተጠሩት በነ ንግሥት ይርጋ ክስ በመከላከያ ምስክርነት ነው።

ህዝባዊ ዓመጹ የተነሳው “በመልካም አስተዳደር ችግር” ምክንያት እንደነበር እነ ገዱ በተደጋጋሚ በየሚዲያው ሲናገሩ ቆይተዋል። ዓቃቤሕግ ደግሞ ክሱን የመሠረተው ሕዝባዊ ዓመጹን ከ“ሽብር” ጋር በማገናኘት ነው። በ“ለውጥ ኃይልነት” ሲወደስ የነበረው ገዱ አንዳርጋቸው ታማኝነቱ ለማን እንደሆነ በይፋ የሚያሳይበት ፈታኝ ወቅት ላይ የሚገኝ ሲሆን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች “አንገቱ ላይ ያለውን ገመድ ለማጥበቅ በህወሓት የታቀደ ሤራ ነው” ብለውታል። በተለይ ሃይለማርያም ደሳለኝ እና ደመቀ መኮንን በመከላከያ ምስክርነት ተቶጥረው መጥሪያ ሳይቆረጥላቸው መቅረቱ ጉዳዩን ልዩ ትኩረት አሰጥቶታል።

ጌታቸው ሽፈራው በፌስቡክ ገጹ በዘገበው መሠረት፤ “ምስክሮቹ ለታህሳስ 12/2010 ዓም ቀርበው እንዲመሰክሩ ትዕዛዝ ተፅፎ የነበር ቢሆንም መጥሪያው ዘግይቶ በመውጣቱ አልደረሳቸውም። ታህሳስ 12/2010 ዓም ተከሳሾቹ ተነጣጥለን ወደ ችሎት አንገባም በማለታቸው ጉዳዩ ሳይታይ ቀርቷል።” ፈተናው ግን ሳይታይ የሚቀር አልሆነም።

የጌታቸው ሽፈራው በሙሉ ዘገባ እንዲህ ይነበባል፤

የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር አቶ ሙሉጌታ ወርቁ፣ የጎንደር ከንቲባ አቶ ተቀባ ተባባል እና ስለ ህዝባዊ አመፁ ማስረዳት ይችላሉ የተባሉ ባለስልጣናት እና የፖሊስ አዛዦች በእነ ንግስት ይርጋ ተፈራ ክስ መዝገብ ስር ለተከሰሱት 6 ግለሰቦች የመከላከያ ምስክር ሆነው (ታህሳስ 12፤ 2010) እንዲቀርቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት አዟል።

ባለስልጣናቱ ህዝባዊ አመፁ በመልካም አስተዳደር ችግር የተነሳ ግጭት እንደሆነ በተለያዩ ጊዜያት በሚዲያ ቀርበው ያስረዱ ሲሆን ዐቃቤ ሕግ ህዝባዊ አመፁን ከ”ሽብር” ወንጀል ጋር በማገናኘት ተከሳሾቹ ላይ የ”ሽብር” ክስ መስርቶባቸዋል።

በተጨማሪም ተከሳሾች ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንም በመከላከያ ምስክርነት የቆጠሩ ሲሆን የሁለቱ ባለስልጣናት መጥሪያ አልወጣም ተብሏል።

በእነ ንግስት ይርጋ የክስ መዝገብ ስር የተከሰሱት ንግስት ይርጋ ተፈራ፣ አለምነህ ዋሴ ገ/ማርያም፣ ቴዎድሮስ ተላይ ቁሜ፣ አወቀ አባተ ገበየሁ፣ በላይነህ አለምነህ አበጀ እና ያሬድ ግርማ ኃይሌ ናቸው።

ተከሳሾቹ በምርመራ ወቅት በህዝባዊ አመፁ እጃቸው እንዳለበት እና የ”ሽብር ወንጀል” ፈፅመናል ብለው በሀሰት እንዲያምኑ ለማድረግ የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደደረሰባቸው ሲገልፁ የቆዩ ሲሆን 1ኛ ተከሳሽ ንግስት ይርጋ ጥፍሮቿ እንደተነቀሉ በክስ መቃወሚያዋ ላይ ተገልፆአል። ሌሎች ተከሳሾችም ያልፈፀሙትን ፈፅማችሁታል ተብለው በደል እንደደረሰባቸው መግለፃቸው ይታወሳል።

ከባለስልጣናት ባሻገር የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም፣ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም እና ሌሎች ምሁራንም በተከሳሾቹ በመከላከያ ምስክርነት ተቆጥረዋል። ምስክሮቹ ለታህሳስ 12/2010 ዓም ቀርበው እንዲመሰክሩ ትዕዛዝ ተፅፎ የነበር ቢሆንም መጥሪያው ዘግይቶ በመውጣቱ አልደረሳቸውም። ታህሳስ 12/2010 ዓም ተከሳሾቹ ተነጣጥለን ወደ ችሎት አንገባም በማለታቸው ጉዳዩ ሳይታይ ቀርቷል።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, Politics Tagged With: andm, eprdf, Full Width Top, gedu, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule