የሚፈለገው ለውጥ ዋናው ዓላማ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚፈለገውን አስተዳዳሪዎቹንና የአስተዳደር ሥርዓትን በነፃነትና በዴሞክራሲ መንገድ ሊመርጥ የሚችልበትን ሥርዓት መመሥረት ነው። ህወሃት የዘረፋ ሥርዓቱን ለማቀላጠፍ እንዲመቸው ዘንድ ኢ-ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መመሪያ በማድረግ ፖለቲካውን የማጭበርበሪያ፣ ኢኮኖሚውን የመዝረፊያ፤ ዳኝነትን የመበቀያ፣ ደህነነትን የማሸበሪያና መከላከያን የማጥቂያ መዋቅሮች አድርጎ ለሃያ ሰባት አመት በኢትዮጵያ ሕዝብና በአገር ላይ ከባድ ግፍና መከራ እየፈፀመ ቆይቷል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የመጀመሪያ ዋና ጥያቄ ይህንን ሕዝቡንና አገሪቷን ከላይ እስከ ታች በኢ-አብዮታዊ ዴሞክራሲና በኢ-ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት በመጠፍነግ ለጥቂቶች ገነት ለአብዛኛው ሕዝብ ግን መከራና ስቃይ የሆነውን ሥርዓት በሰላማዊ መንገድ መለወጥ ነው። ዶ/ር አብይ ከሚናገሩትም ሆነ ከገዱ ቡድንና … [Read more...] about የጠ/ሚ/ር አብይን የለውጥ መንገድ ለመርዳት ምን ማድረግ ያስፈልጋል?
Right Column - Primary Sidebar
ከሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልጽ ውይይትና ድርድር ሊደረግ ይገባል!
ዶ/ር አብይ የኦህዴድ ጽ/ቤት አላፊ በነበሩበት ወቅት ኦህዴድ ሁሉንም ሰላም ወዳድ ዜጋን ያስደሰተ ጥሪ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ላሉ ተቃዋሚዎች አቅርቦ ነበር። ይህ ጥሪ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የቀረበ በመሆኑ አንዳንድ በኦሮሞ ስም የሚታገሉ በውጪም በውስጥም ያሉ ተቃዋሚዎች በደስታ የተቀበሉት ነበር። ነገር ግን ይህ የኦህዴድ ጥሪ ምንም ያህል ለሀገሪቱ ሰላም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ቢሆንም ያለ ኢህአዴግ አሺታ ሊሳካ እንደማይችል የገመቱ ነበሩ። ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን በመጡ የመጀመሪያዋ ቀን በፓርላማው ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ኦህዴድ ለተቃዋሚዎች ካቀረበው ጥሪ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን ሃሳብ ተናግረው ነበር። ጠቅላይ ሚንስተሩ በኢትዮጵያ ጉዳይ “በተለያየ መልኩ” ከሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ሀይሎች ጋር አብሮ ለመስራት እንደሚፈልጉ ጠቅሰው ነበር። የዲስፖራው ፖለቲካ ብዙውን … [Read more...] about ከሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች ጋር ግልጽ ውይይትና ድርድር ሊደረግ ይገባል!
ቋንቋን በቋንቋ
ስለ ቋንቋ የተለያዩ እይታዎች መኖራቸው አዲስ አይደለም። የሚገርመው ይልቅ፣ ብዙዎች እንደ ሹምና አቡን ትእዛዝ ሲሰጣጡ ማየት ነው። ትእዛዙን ማን፣ እንዴት ይፈጽም? እይታዎችን ማቀራረብና መተግበርስ ይቻላል? መቸ በምን ቅደም ተከተል? ወዘተ። ይህን ያሰቡበት ቢኖሩ ድምጻቸው አልተሰማም። የራስን አጉልቶ፣ የሌላኛውን ማድበስበስ የተለመደ በመሆኑ፣ የጽሑፌ ይዘት ለያንዳንዱ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፣ የተዘነጉ ጥቃቅን አሳቦችን ማነጋገር ይሆናል። ቋንቋ ቢያንስ ሀ/ ድንበር ተሻጋሪ መሆን ይኖርበታል፤ አማርኛ ተናጋሪ፣ እርስ በርሱ ብቻ ከሆነ፣ ከኬላው ውጭ በምን ይግባባል? ለ/ ድንበር ተሻግረን እንግሊዝኛ፣ አማርኛ፣ ወዘተ፣ የቆነጠርን ቢያንስ አኗኗራችንን ለማሻሻል እንደ ሆነ አንርሳ ሐ/ ቋንቋ ተሻጋሪ እንዲሆን፣ ድልድይ የሚሆን ቋንቋ ይሻል። አማርኛ ድልድይ ነው። እርግጥ፣ ሁሉን ቋንቋ ማወቅ … [Read more...] about ቋንቋን በቋንቋ
የአማራ ብሔረተኝነት ለስር ነቀል ለውጥ መሰረት፣ ለኢትዮጵያም መዳኛ መድሃኒት ነው
የአማራን ህዝብ በቃላት መሸንገል የማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል። የህዝቡ ንቃተ ህሊናው በስልጣን ላይ ከሚገኙት ከፓለቲከኞቹ ቀድሞ ሄዷል። ወጣቱ የነብር ጣቱ - እሳት ትውልድ ሆኗል። ገና ከመነሻው ወያኔ/ትህነግ በ1967 ዓ.ም ባፀደቀው በማኒፌስቶው ላይ አማራ ጠላቴ ነው በማለት የአማራ ህዝብ መቃብር ላይ የትግራይን ሪፕብሊክ እመሰርታለሁ፣ የአማራን ህዝብ ማህበራዊ ሰላም አሳጠዋለሁ ብሎ ሸፈተ። በርሃ ሳለ በአማራው ተወላጅ ላይ ከፍተኛ በደልና ወንጀል ሲፈጽም ከቅምየ በኋላ በተለት የአለም አቀፍና የሃገር ውስጥ ሁኔታዎች በደርግ መንግስት ላይ በፈጠሩት ጫና በለስ ቀንቶት የመንግስት ስልጣን ከተቆጣጠረበት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በጥናትና በእቅድ በተጠናከረ ሁኔታ በአማራ ህዝብ ላይ የሙፈጽመውን በደልና ቀጠለበት። ጫካ እያለ ያፀደቀውን ፀረ አማራ ፕሮግራሙን ለማታለያነት ከካናዳና ከሌሎች … [Read more...] about የአማራ ብሔረተኝነት ለስር ነቀል ለውጥ መሰረት፣ ለኢትዮጵያም መዳኛ መድሃኒት ነው
የዶ/ር አብይ አህመድ አዋላጅነት ጉዳይ
ቃሉ የሕዝብ ነው። ቃሉንም በተግባር የሚተረጉመው ሕዝብ ነው። የወንዝ ውሃ ሽቅብ እንደማይፈስ ሁሉ፥ ይህም ቃል ወደ ተግባር ሳይቀየር ይቀለበሳል ብሎ መጠበቅ ተገቢ አይደለም። ይልቁንስ ይህን ቃል ለመተግበር የዶ/ር አብይ ድርሻ ምንድነው ብሎ አውቆ በዚያው ሚዛን ብቻ እርሳቸውን መመዘን ያስፈልገናል። ለሕዝብ ታማኝ ባይሆኑ፥ እሳቸው ከታሪካዊነት ይጎድላሉ እንጂ የሕዝብ ቃል ዕውን መሆኑ አይቀሬ ነው። ዶ/ር አብይ አህመድ የሚናገሩት ቃል እርሳቸው የፈለሰፉት ስለሆነ አይደለም የተወደደው። ቃሉ የሕዝብ ቃል ስለሆነ ነው እንጂ። ይህ ሰሚ ያጣ ሕዝብ በትግሉ የራሱን ቃል የሚያስተጋባ ጠ/ሚ ሊያመጣ ቻለ። ታዲያ ይህን ቃል የዶ/ር አብይ የግል ንብረት ተደርጎ፥ ቃል ዋጋ የለውም ብሎ ቃሉን ማጣጣል ለኢትዮጵያ አይጠቅምም። የውልጃ አብሳሪ የሆነ ቃል በውልደት ቀን ዋዜማ ሲሰማ፥ በተስፋና በትጋት ይህን … [Read more...] about የዶ/ር አብይ አህመድ አዋላጅነት ጉዳይ
የጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ
እንደ መግቢያ ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ስለዶ/ር አብይ ያለኝ የጠለቀ እውቀት ወይም ከነበሩበትና ከተነሱበት ፓርቲና ፓርቲው ከሚያራምደው የፖለቲካ አመለካከት ጋር ያለኝ ጠብ ወይም ዝምድና አይደለም። ይልቁንም እንደ አንድሀገር-ወዳድ ኢትዮጵያዊ ባለው የህወሃት የበላይነትን የተከተለ ፍጹም ዘረኛ ጉዞ ሄደን ሄደን የደረስንበት ደረጃ በጣም አሳሳቢ መሆኑን በመመልከት ነው። በዘረኛው የወያኔ ከሩብ ምእተ አመት የዘለለ የጥፋት ጉዞ ውስጥ ከተጓዙና ከጉያቸው የበቀሉ ዘረኛው ስርአት ከሚያራምደው የተለየና የተሻለ ራእይ ያለው ጉዞን የመረጠ የኦሮሞ፣ የአማራ እንዲሁም የመላው ኢትዮጵያ ወጣቶች በደምና በህይወት ጭምር ዋጋ የከፈሉበትን ትግል ባዳመጠ መልኩ የተቃኘ ‘ቲም ለማ’ ከተባለ የለውጥ አራማጆች ውስጥ የበቀሉት የዶ/ር አብይ ራእይ ምን ቢሆን ለሐገር የሚበጅ መድህን ይሆናል የሚለውን … [Read more...] about የጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ
HR 128 መጽደቅ ለመሰረታዊ የመብት ትግላችን ታላቅ ድጋፍ ነው
ሸንጎ ህጉን ይደግፋል፤ ለተፈጻሚነቱም ተግቶ ይፋለማል HR 128 ተብሎ የሚታወቀው ባሜሪካ ኮንግረስ (ፓርላማ) ውስጥ ለውሳኔ ቀርቦ የነበረው በኢትዮጵያ መንግስት የመብት አያያዝ ላይ ያተኮረ የህግረቂቅ እነሆ ትናንት መጽደቁ ተነገረ። በውጭ አገር ያሉ የሰብዓዊ መበት ተከራካሪዎችና የተደራጁ ኢትዮጵያውያን ይህ የህግ ረቂቅ እንዲጸድቅና በስራ ላይ እንዲውል ለረጅም ጊዜ ከፍተኛ ተጋድሎ ሲያድርጉ ቆይተዋል። ሸንጎ ለዚህ ስኬት ታጥቀው ለታገሉ ሃይሎች በሙሉ ያለውን አድናቆትና ክብር እያስታወቀ፤ የረቂቁ ህግ ሆኖ መጽደቅ ለኢትዮጵያ ህዝበና ለመላው የዴሞክራሲ ሃይሎች ታላቅ ድል መሆኑን ይገልጻል። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ … [Read more...] about HR 128 መጽደቅ ለመሰረታዊ የመብት ትግላችን ታላቅ ድጋፍ ነው
አምቦ ትናንትና ዛሬ!
አምቦ ስሟ ሲጠራ የብዙዎቻችን ልብ በሃሴት እንደሚሞላ ሁሉ ወያኔዎችና አሽቃባጮቻቸው አጥንታቸው ድረስ የሚዘልቅ ብርድ እንደሚሰማቸው ግልፅ ነው። ያች ምድር የብዙ ጀግኖች መፈጠርያ ናት። ጣልያንን ብርክ ያስያዙ ጀግኖቿን ታሪክ ሲያስታውሳቸው ቢኖርም ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው የአባቶቻቸውን ጋሻ አንስተው የሃገር ጠላት የሆነን ስርዓት በመፋለም ለሌላውም አንቂና አበረታች ሆነው እነሆ እነሱም ታሪክ ሠሩ። አምቦዎች ወያኔን መፋለም የጀመሩት ገና ከመጀመርያው ነው። ከሁሉም በላይ ባለፈው ሶስት ዓመት የአምቦና የአካባቢ ጀግኖች፣ ቄሮዎች የለኮሱት አመፅ መላ አገሪቷን ከዳር ዳር አዳርሶ እነሆ ዲያስፖራንም አነቃንቆ HR 128 በማስወሰን በወያኔ አንገት ገመድ አጥልቆለታል። አምቦና ወያኔ ዐይንና ናጫ ናቸው። ወያኔ በጎንደር፣ በጎጃምና በወለጋ አቆራርጦ ሲገሰግስ ሊሞት አንድ ሃሙስ የቀረው ደርግ … [Read more...] about አምቦ ትናንትና ዛሬ!
ልጄ ሆይ፤ ሰው ሁን!
እነሆ ሰንበት ነበረ። ምዕመኑ በሚኖርበት ከተማ በምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅድሰት ቤተ ክርስቲያን እንዳለፉት አያሌ ሰንበቶች ሁሉ ባለፈው ሰንበትም ተገኝቷል። ቃሉን ሊሰማ፤ ስለ ቃሉም ለመኖር ብርታትን ሊያገኝ፤ ስለራሱና ስለቤተሰቦቹ፤ ስለ ህዝቦቹና ስለ ሀገሩም ሊፀልይ፤ እጆቹንም ወደ ሰማይ አንስቶ ሊለምን። ማረን ለማለት። እግዚኦታም ለማቅረብ። ከትጉሁና ትሁቱ ካህንም ቃለ ህይወት ሊሰማ። ቃለ ህይወትንም ሊማር። እነሆም ካህኑ ቅዳሴውንና ፀሎቱን ይመራሉ። ድምፃቸውም በመንፈሳዊ ቅላፄ በመቅደሱ ይሞላል። ዲያቆናቱም ይቀበላሉ። ምዕመናኑም ይደግማሉ። ወይ ተንበርክከውና አንገታቸውን ከመሬት ደፍተው፤ ወይ ቀጥ ብለው በመቆም እጆቻቸውን ወደ ፈጣሪ ዘርግተው። የካህኑ ድምፅ በፀሎትና በቅዳሴ ዜማ እንዲህ ይላል - አምላካችን ክርስቶስ ሆይ፤ የተጨነቀችይቱን ነፍስ ሁሉ አሳርፍ፤ … [Read more...] about ልጄ ሆይ፤ ሰው ሁን!
የጠቅላይ ሚንስትሩ ተስፋ ሰጪ ንግግርና የኛ ሚና!
በትናንትናው ዕለት በሕይወቴ ለመጀመርያ ጊዜ በኢትዮጵያ የፖሊቲካ ታሪክ ውስጥ ሥልጣን ካንዱ ጠ/ሚንስትር ወደ ሌላው ሲሸጋገር በአደባባይ በማየቴ ለማመን እየተቸገርኩኝ ነው። በጠ/ሚንስትሩ ንግግር ውስጥም ላለፉት አርባ ዓመታት የለመድናቸው “ጠላት” “ጸረ ሰላም ኃይሎች” “እናሸንፋለን” የመሳሰሉ ካድሬያዊ አነጋገሮች ለመጀመርያ ጊዜ በመሪያችን አፍ አለመነገሩን፣ ተፎካካሪ እንጂ ተቃዋሚ እንደሌለ መስማት፣ የተለየ አስተሳሰብ ስላስተናገዱ ብቻ የተገደሉትን የፖሊቲካ መሪዎችና በጨቅላነታቸው የተቀጩትን አስታውሶ ይቅርታ መጠየቅ፣ ከልብ ይቅር ተባብሎ ያለፈውን ምዕራፍ ዘግቶ ወደ ፊት ለመራመድ መጋበዝ፣ ከኤርትራ ጋር በሰላም ለመኖር ከማሰብ አንጻር ንግግር ለመጀመር ዝግጁ መሆን፣ ከሁሉም በላይ ለዘመናት እንደ “ገበና” ተቆጥሮ የማይነገረውን የግልን ህይወት ለአደባባይ ፍጆታ ቀርበው ስናዳምጣቸው … [Read more...] about የጠቅላይ ሚንስትሩ ተስፋ ሰጪ ንግግርና የኛ ሚና!









