• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሳውዲ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ቀጥሏል

November 27, 2013 08:58 am by Editor Leave a Comment

ሪያድ አሚራ ኑራ ዩኒቨርስቲ በሚገኝ ጊዜያዊ መጠለያ ሜዳ ላይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና በሳውዲ ፖሊሶች መሃከል በተነሳ ግጭት አንዲት ነፍሰጡር ኢትዮጵያዊት በአውቶብስ ተገጭታ ህይወቷ አለፈ።

ሪያድ መንፉሃ እየተባለ ከሚጠራ አካባቢ ሰሞኑንን በሳውዲ ፖሊሶች ታፍሰው ከከተማይቱ 120 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ወደ ምትገኝ፡ በተለምዶ ሚንዛህሚያ እየተባለ የሚጠራ እስርቤት ተወስደው ከነበሩ 10 ሺህ ኢትዮጵያውያን መሃከል ግማሽ ያህሉ በ17 አውቶብስ ተጭነው ማምሻውን ሪያድ ከተማ አሚራ ኑራ እየተባለ የሚጠራ ዩኒቨርስቲ ሜዳ ላይ መጣላቸውን ተከትሎ ከባድ ሁከት መቀስቀሱን ከሪያድ የሚደርሱ መረጃዎች ያመለክታሉ።

ይህን ተከትሎ በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ በኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች እና በሳውዲ ፖሊሶች መሃከል ከባድ ግጭት መከሰቱን የሚገልጹት እነዚህ ምንጮች አዲት ነፍሰጡር ሴት ከድንጋይ ውርወራው ለማምለጥ ከግቢው ለመውጣት ሲበሩ በነበሩ አውቶብሶች በአንዱ ተጭፍልቃ መሞቷን ገልጸዋል። ግጭቱ በጣም ዘግናኝ፡ አሰቃቂ እንደነበር የሚገልጹት የአይን ምስክሮች የሳውዲ ፖሊሶች ማንም ሰው ካሜራ እንዳይቀርጽ ለማገድ ከአካባቢው ኢትዮጵያውያኑንን በማራቅ አስከሬኑን ነጭ ነገር ሸፍነው በቅጽበት በአምቡላንስ ተጭኖ ወደ ሆስፒታል እንዲወሰድ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ዛሬ ረፋዱ ላይ በ17 አውቶብስ ተጭነው ሚንዛህሚያ እየተባለ ከሚጠራ አካባቢ እንደመጡ ከሚነገርላቸው ኢትዮጵያውያን መሃከል በአብዛኛዎቹ ሴቶች ህጻናት እና ነፍሰጡር እንደሆኑ የሚናገሩት ምንጮች አውቶብሶቹ የተጠቀሰው አካባቢ ሲደርሱ በውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያኖች ኤርፖርት እንወስዳችሃለን ብላችሁ እዚህ ባዶ ሜዳ ላይ አምጥታችሁ ለምን ትበትኑናላችሁ በማለት ከአውቶብሱ አንወርድም በሚል የኡ ኡ ታ ጩሀት በማሰማት ተቃውሞቸውን ሲገልጽ የሳውዲ ፖሊሶች የአካባቢውን ጸጥታ ያደፈርሰውን የህዝብ ኡ ኡታ ጩህት ለማርገብ ጥረት በሚያደርግበት ወቅት ድንጋይ ውርወራ መጀመሩን የሚገልጹ እማኞች በፖሊስ እና በህዝቡ መሃከል በተነሳው ግጭት አያሌ ህጻናት እና አረጋውያን መረጋገጣቸውን በመጥቀስ እስካሁን በወገኖቻችን ህይወት ላይ የደረሰው አደጋ በውል ባይታወቅም ብዛት ያላቸው አምቡላሶች ኢትዮጵያውያኑ ከተጠለሉበት ግቢ «ሳይረን» እያሰሙ ሲወጡ መታየታቸውን አክለው ገልጸዋል።

ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ሚንዛህሚያ እየተባለ ከሚጠራው መጠለያ በ17 አውቶብሶች ተጭነው የመጡት ወገኖቻችን ከአውቶብሶቻቸው እንዳልወረዱ እና በአሁኑ ሰአት ብጥብጡ ተባብሶ መቀጠሉ ተገልጾል። ቀደም ሲል ለፖሊስ አሻራ ትሰጣላችሁ ተብለው ከተለያየ አካባቢ ሪያድ ከተማ መለዝ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ የሚገኝ አንድ ትልቅ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ እስከ 7 ሺህ የሚጠጉ ወገኖቻችን ያለዳስ «ድንኳን» ሜዳ ላይ ተጠለው ፀሃይ ብርድ እና ዝናብ እይተፈራረቀባቸው መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሎል።

በዚህ ዙሪያ ጉዳዩ ወደ ሚመለከታቸው በሪያድ የኢትዮጵያ አምባሳደር መሃመድ ሃሰን ስልክ በመደወል ስለጉዳዩ ለማነጋገር ያደረኩት ጥረት እስካሁን አልተሳካም! የዲያስፖራው ሃላፊ ዲፕሎማት አቶ ተመስገን ኡመር ቴሌፎን ቁጥር ይህ ሁከት ከተቀሰቀስ ወዲህ መስመሩ ከአገልግሎት ውጭ ነው የሚል መለዕክት የሚያስተላልፍ በመሆኑ የኤምሲውን ተጠሪዎች እስካሁን ማግኘት አልተቻለም ።

Ethiopian Hagere በፌስቡክ ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከጅዳ በዋዲ የላኩት

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule