• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠ/ሚ/ሩ በአሜሪካ ከወሳኝ ኢትዮጵያውያን ጋር ሊነጋገሩ ነው

May 25, 2018 03:12 pm by Editor 1 Comment

በኢህአዴግ የተሰየሙት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ በሰኔ ወር መገባደጃ አካባቢ ወደ አሜሪካ ጉዞ እንደሚያደርጉ ታወቀ። በቆይታቸው ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ በተለይ በሰላማዊ መንገድ ትግል ከሚያደርጉ ኢትዮጵያውያን ጋር በግልና በቡድን በመገናኘት ሊነጋገሩ እንደሚችሉ ተነግሯል።

በህወሓት/ኢህአዴግ ስያሜ የጠቅላዩን መንበር የተቆናጠጡት ዓቢይ አህመድ ላለፉት በርካታ ሳምንታት በአገር ውስጥ እና በአጎራባች አገራት ጉብኝቶችን ሲደርጉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በቀጣይ የተያዘው መርሃግብር ወደ አውሮጳና አሜሪካ ጉዞ ማድረግ እንደሚሆን መረጃዎች ሲወጡ ነበር። ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ የጠቅላይ ሚ/ሩ የአሜሪካ ጉብኝት መረጃ ቀደም ብሎ የደረሰው ቢሆንም በወቅቱ የተባለው በሰኔ ወር መገባደጃ ወይም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ላይ ንግግር ለማድረግ በመስከረም አካባቢ ሲመጡ ሊሆን ይችላል የሚለው ነበር።

ዛጎል ታማኝ ምንጮቼ ያደረሱኝ መረጃ ነው በሚል በድረገጹ ላይ እንደገለጸው ጠ/ሚ/ሩ “ሰኔ 26 ወይም 27 ወደ አሜሪካ እንደሚያቀኑ” ተናግሯል። ሲቀጥልም የዓቢይ አህመድ ጉብኝት “በአሜሪካ በኩል ሙሉ ድጋፍ ያለውና አስፈላጊው ሁሉ ትብብር የሚደረግለት” መሆኑን አስታውቋል።

“በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ አዙሪት ያሳሰባት አሜሪካ በአገሪቱ የሰከነ የፖለቲካ ለውጥ እንዲኖር፣ ለዚሁም ተግባራዊነት ድጋፍ የምታደርግ፣ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ይህንን ለውጥ የማይቀበል ከሆነ ኮሮጆውን እስከማድረቅ የሚያደርስ እርምጃ እንደምትወስድ እያስጠነቀቀች መቆየቷ ይታወሳል። በሂደት ላይ ያሉ የህግ ጉዳዮችም አሉ። በዚሁ ቅኝት መሰረት የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የአሜሪካ ጉዞ በዲያስፖራውና በመንግሥት በኩል ያለውን ልዩነት ለማርገብ፣ የወደፊቱን የለውጥ ሂደት የማስረዳትና በዝርዝር የማሳየት እንዲሁም አፋኝ የሚባሉት ህጎችን አስመልክቶ የሚደረገውን ማሻሻል በይፋ የማሳወቅ ነው። ተያይዞም አገራቸው መግባት ለሚፈልጉ በይፋ ዋስትና የሚሰጥ ግብዣ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።”

ጊዜው ሲደርስ የሚታወቅ ቢሆንም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የጉብኝት ወቅት በዳስፖራው ፖለቲካ ላይ በጉልህ የሚታወቁ በተለይም በሰላማዊ (ነውጥ አልባ) መንገድ ትግላቸውን ለዓመታት ሲያካሂዱ ከነበሩ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር ይገናኛሉ ተብሏል። እነዚህም በድርጅት ተደራጅተውም ይሁን በግላቸው በአገራቸው ጉዳይ ላይ የሚወተውቱትን እንደሚካትት ታውቋል።

“በዚሁ መሰረት ውይይቱ ከመዘላለፍ፣ ከሁከትና ውጤት ከማያስገኝ እንከኖች የጸዳ ይሆን ዘንድ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንን” ዛጎል የመረጃ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል። ሲቀጥልም “(የዜናው አቀባዮች) ስለ አጠቃላዩ ዝግጅት ከመናገራቸው ውጪ ስለሚደረገው ዝግጅት በዝርዝር አላብራሩም፤ የአሜሪካ ሚና ምን እንደሚሆንም አላስታወቁም” ብሏል።

የጠቅላዩን ጉዞ በአዎንታዊ መልኩ የሚመለከቱ ወገኖች ጉብኝቱን እንደ መልካም ዕድል በመጠቀም ለበጎ ውጤት እንጠቀምበት በማለት ይመክራሉ። ጠቅላይ ሚ/ር ዓቢይ አህመድ የዳያስፖራውን ኃይል በሚገባ የተገነዘቡና ይህንንም በአደባባይ የተናገሩ መሆናቸውን የሚጠቅሱ ክፍሎች ዳያስፖራው ካለው ሙሉ የመናገር መብት አኳያ አገር ቤት ያለው ኢትዮጵያዊ በድፍረት ሊናገር የማይችለውን በማንሳት ለወገኑ ያለውን ተቆርቋሪነት ማሳየት ይገባል ይላሉ። ከዚህ በፊት የህወሓት ኃላፊዎች በድብቅ መጥተው በድብቅ መሄዳቸው አግባብነት የለውም በሚል ትልቅ ተቃውሞ ይደርስባቸው እንደነበር የሚያስታውሱ ወገኖች በገሃድ እንወያይ የሚል መሪ ሲመጣ በጭፍን ከመቃወም ይልቅ “እኛም የምንፈልገው ይህንን ነበር” በሚል በሰከነ መንፈስ የጉብኝቱ አካል መሆን ይገባቸዋል በማለት ሃሳብ ይሰጣሉ።

ጉብኝቱ ዋሽንግቶን ዲሲ በሚገኘው ኤምባሲ የበላይ ኃላፊነት የሚቀናበር ከመሆኑ አኳያ እዚያ ያሉት የህወሓት ሎሌዎች ውይይቱንም ሆነ ስብሰባውን በዳስፖራው ስም በደጋፊዎቻቸውና በአፍቃሪ ህወሓቶች ጠለፋ እንዳያካሂዱበት ካሁኑ ጠንቅቆ በመጠበቅ አስፈላጊውን የቤት ሥራ መሥራት እንደሚገባ ጎልጉል ያነጋገራቸው የዳያስፖራ አካል ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, diaspora, Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    May 26, 2018 10:35 pm at 10:35 pm

    በምን ነጥብ ላይ?? በህገ መንግሥቱ? በመሬት ሥሪት? በክልላዊ ኣስተዳደር?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule