• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦባማ የአፍሪካን ገዢዎች እያዋዛ ደቆሳቸው!

July 29, 2015 09:58 am by Editor 1 Comment

ኦባማ በአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ንግግር ብዙ ጥያቄዎችን መልሷል፤ የኦባማ ጉብኝት ያስከተለው ጫጫታ ሁሉ መልስ አገኘ፤ የሰው ልጆች በመሀከላቸው ምንም ዓይነት የአድልዎ ልዩነት ሳይደረግባቸው በሰውነታቸው ብቻ በተፈጥሮ ያገኙትን ክብራቸውንና ሞገሣቸውን አስከብረው መኖር እንዳለባቸው በአጽንኦት ተናገረ፤ ዛሬ የአሜሪካኑ ፕሬዚደንት ያደረገው ንግግር ከፕሬዚደንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ እስከ ፖሊሶች፣ መርማሪዎችና አዛዦቻቸው፣ እስከጦር ኃይሉና አዛዦቻቸው፣ አስከዓቃብያነ ሕግና ዳኞች፣ እስከወህኒ ቤት ጠባቂዎችና አዛዦች በየሥልጣን ተዋረዱ ላይ ሆነው የኢትዮጵያውያንን የሰውነትና የዜግነት እኩልነት አፈራርሰው በጎሣ መሠረት ላይ ሊበታትኑት የሚሞክሩትን በኃይለኛ ቃላት ከመሬት በታች ከቶአቸዋል፤ ማሰብና ማስተዋል የጎደለው፣ ከአፍንጫ የራቀ አመለካከት የሌለበት፣ አገርን የሚያጠፋ፣ ከሰውነት ጎዳና የሚያወጣ የድንቁርና መንገድ መሆኑን ገልጧል፡፡

ኦባማ የኢትዮጵያን ገዢዎች ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን ገዢዎች በሙሉ አላግጦባቸዋል፤ በሥልጣን ላይ ሙጭጭ በማለታቸው፣ በሙስናቸው፣ በአፈናቸው፣ ልክ ልካቸውን ሲነግራቸው እፍረታቸውን ውጠው ያጨበጭቡለት ነበር፤ የአፍሪካ ገዢዎች ሕጉን እንደፈለጉ የሚጠመዝዙትን መሳቂያ አድርጓቸዋል፤ በአዳራሹ ውስጥ የነበሩ ወጣቶች የኦባማን ንግግር በማድነቅ በጭብጨባና በጩኸት ይገልጹ ነበር፤ ለወግ ብቻ የሚደረግ ምርጫ የዴሞክራሲ መግለጫ አይሆንም አለ፤ ዴሞክራሲ ነጻና ትክክለኛ ምርጫን፣ ሀሳብን በነጻነት መግለጽን፣ በነጻነት መደራጀትንና መሰብሰብን ያካትታል፤ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድረጅቶችን ማገድና መገደብ ለዴሞክራሲ እንቅፋትና ለእድገት ጸር ነው፡፡

አገዛዞች ነጻነትን በማፈናቸው ሁለት ዋና ዋና የማኅበረሰብ ዓምዶችን ማለትም ደኅንነትንና ሰላምን ያጣሉ፤ ሰላምና ደኅንነት ሰጠፋ ማኅበረሰቡ የጉልበተኞች መጫወቻ ሆኖ ይደናበራል፤ ይህ አደገኛ ጉዞ ነው፤ መልካም አስተዳደር ከሰፈነ ሽብርተኛነት የሚበቅልበት መሬት አያገኝም፤ ሰዎች ሁሉ በሰውነታቸውና በዜግነታቸው እኩልነት ሰብአዊ መብቶቻቸው ሁሉ ከተከበሩላቸው ወደኃይል እርምጃ የሚወስደውን መንገድ የሚከተሉበት ምክንያት የለም፤ እድገት የነጻነትና የዴሞክራሲ ውጤት ነው፤ ነጻነት የሰው ልጆች ሁሉ ዓላማ ነው፡፡

ማንም ቢሆን ከሕግ በታችና ለሕግ ተገዢ መሆን አለበት፤ ሕገ መንግሥቱን ለእሱ እንደሚበጀው እያደረገ በመተርጎም በሥልጣን ላይ መቆየት አይቻልም፤ ሊፈቀድም አይገባም፤ በአጠቃላይ አባማ በአፍሪካ ኅብረት በአደረገው ንግግር የአፍሪካ ገዢዎችን ሁሉ ቁስላቸውን በአልኮል ሲያጥብላቸው እየለበለባቸው ተመልክተውታል፤ አዳምጠውታል፤ አንዳንዶቹም እያፈሩ አጨብጭበውለታል፡፡

የዚህ ንግግር የመጨረሻው ግብ ያልገባቸው የአፍሪካ ገዢዎች ክፉ ነገር ይጠብቃቸዋል፤ በሽብርተኛነት መነገድ መልኩን ሊለውጥ ነው፤ ካላወቁበት የማያውቁት ሽብር ቤታቸውን ይጠርግላቸዋል!

ሐምሌ/2007

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    July 29, 2015 11:23 pm at 11:23 pm

    >>> የአፍሪካ መሪዎች በአሜሪካው ጥቁሩ መሪ በነጩ ቤት ከተጋበዙ በኋላ የነበሩበትንም ያሉበትንም ዘንግተው ፎቶአቸውን አየለጠፉ ሲፈነድቁ ከርመዋል። ተራቸው ደርሶ ጥቁሩን መሪ በጥቁር ምድር ቻይና በሰራው ቤት ጋበዙት…”የሰው በልቶ አያድሩም ተኝቶ” ነዋ! ጠርታችሁ እየሳቃችሁና እያጨበጨባችሁ ስለተሰደባችሁ በጣም ደስ ብሎናል እንኳን ደስ አላችሁ። ወ/ሮ ዊንዲ ሸርማን በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ አለ.. ምርጫው ፍትሃዊና እንደቀድሞው ሁሉ የተሳካ ይሆናል ሲሉ የኢህአዴግ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር አቶ ቴዎድሮስ አደሃኖም በሳቅ ታፍነው ሽምቅቅ አሉ። ለምን? ከውሸታሙም በላይ ዋሾው ሲያሳምረው ደንግጠው…ከኦባማ ጉብኝት በኋላም ቴዎድሮስ አድሃኖም ሃፍረትና ድንጋጤያቸው ትክክል እንደነበር ተረድተው ስሐተቶችን አምነው መቀበል ጀምረዋል ሆድአደር ካላሰናከላቸው ይበርቱ። ወ/ሮ ሱሳን ራይዝ ደግሞ “ በቅርቡ ኢህአዴግ በመቶ ደምፅ የተመረጠ መንግስት ብለው… በመቶ ደምፅ መመረጥ ዲሞክራሲ ነውን? ሲባሉ አዎን! በመቶ ደምፅ ብለው በምርጫው ሳቁበት ”የዓለም ሕዝብም ሳቀ እኛም ተሳቀቅን…. ኦቦ ባራክ ሁሴን” የኢትዮጵያ መንግስት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የመጣ ነው” አሉት… ሁለት ውሸታም አማካሪዎቻቸውን ላለማሳፈር እሳቸውም በዲሞክራሲ ያልተመረጠ መንግስትን አልጎበኘሁም ለማለት ነበር። በእርግጥ ዲሞክራሲ ምርጫ ነው? በኢህአዴግ አባባል “ምርጫ ሂደቱ ብቻ በቂ ነው”ሲል ፮ሚሊየን አባላት አለኝ የሚለው ኢህአዴግ ፩ ለ ፭ ጥርነፋ የታፈኑ ሚሊየኖች አሉ። ምርጫው ከ፴፭ ሚሊየን አስከ ፴፰ነጥብ ፭ሚ ሕዝብ ተሳትፏል ይላሉ በእርግጥ ይህ ቁጥር እንዴት ተዘበራረቀ? ተመዝጋቢው ቀድሞ ከታወቀ የምርጫ ወረቀትስ እንዴት አነሰ? የትግራይ ልጆች በኤትርትራውያን ስደታኛ ሥም ከሀገር ሲሰደዱ ኤርትራውያን በትግራይ ልጆች ሥም ምርጫ ገብተውስ እንደሆነ? በመለስ ግዜ አመራር በቡድን ነበር በኀይለመለስ በኅብረት አደለምን!? ወጣም ወረደ ኦባማ ዋሽንግተን ነጩ ቤት ተቀምጦም ይሁን አዲስአባባ አፍሪካ ኅብረት ቻይና ሰራሽ አዳራሽ ቆመው ተናገሩ አልተናገሩ ገዢው፣ አውራ ፓርቲ፣ የኀያላን ሀገሮችን ትዕዛዝ እስካከበረና ጥቅማቸውን በድሃ ልጅ ደምና አጥንት እስካስከበረ ድረስ ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሃዊ፣ልማታዊ፣ እያሉ በፓርቲውና በሕገመንግስቱ ከለላ ጃፓን የደረሰችብት የዕድገት ደረጃ እስኪደርስ ሁሉም በአንድ የፖለቲካ ጥላ ሥር አጠቃሎ እንዲቀጥል ይደረጋል። ኀይሌ አሜሪካ ከእኛ የምትፈልገው አለ እኛም የምንጠይቃቸውን ያደርጉልናል ሲሉ ነበር። በመሠረቱ ሁሴን ኦባማ እንዳሉት አሜሪካም ሙስና አለ ካሉ ህወአት አባላትም እሥርና ግድያም አሜሪካንም አለ እንደሚሉን ማን በነገራቸው። የእያንዳንዱ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ፓርቲ አባል ክስ የሚመሰረትበት አሸባሪ ህግ አንቀፆችን አጠጋግቶ ከ፲ እስከ ዕድሜ ልክ የሚያስፈርጀውን የሚጽፉ የህግ ተማሪዎች (ዐቃቢ ሕግ) ባለሙያ ሳይሆኑ የፖለቲካል ሳይንስ ተማሪዎች እንደሆኑ አልተረዱልንም!። ሕግን ከአሜሪካ እና ከእንግሊዝ ኮርጀን በእስታሊን በሌኒን በቦልሸቪክና ሞኖቪክ ገሎ ማለፍ ሥርዓት የአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ሙስና መር ኢኮኖሚ ሲፈጠር ከታጋዩ ይልቅ ጥቅማጥቅመኛው አድርባዩ፣ አውርቶ አደሩ ሠላም፣ እኩልነት፣ አንድነት፣ እንዳይኖር እሳት ሲጭር ይኖራል…
    “አገዛዞች ነጻነትን በማፈናቸው ሁለት ዋና ዋና የማኅበረሰብ ዓምዶችን ማለትም ደኅንነትንና ሰላምን ያጣሉ፤ ሰላምና ደኅንነት ሲጠፋ ማኅበረሰቡ የጉልበተኞች መጫወቻ ሆኖ ይደናበራል፤ ይህ አደገኛ ጉዞ ነው፤ መልካም አስተዳደር ከሰፈነ ሽብርተኛነት የሚበቅልበት መሬት አያገኝም፤ ሰዎች ሁሉ በሰውነታቸውና በዜግነታቸው እኩልነት ሰብአዊ መብቶቻቸው ሁሉ ከተከበሩላቸው ወደኃይል እርምጃ የሚወስደውን መንገድ የሚከተሉበት ምክንያት የለም፤ ዕድገት የነጻነትና የዴሞክራሲ ውጤት ነው፤ ነጻነት የሰው ልጆች ሁሉ ዓላማ ነው፡፡ -ይህ ሳይሆን ሲቀር ነው ሰዶ ማሳደድ የሚጀምረው ። ኦቦ ሁሴን ባራክ በቤታችን መጥተው እያሳሳቁ ከሚተርቡን ከሚያፌዙብን ከሚሳቅብን ከምንሳቀቅ እዚያው ሆነው እርስ በእርሳችን በተደማመጥን በተራረምን መልካም ነበር። አሁንማ ሰድበው ለሰዳቢ ሰጡን መልካም የ፲፰ ወር ቆይታ በነጩ ቤት ይሁንላቸው እኛም ጥንቷዊቷ የምርጥ ዘርና የሰው ልጅ መገኛ የጥቁር ቤታችን ኢትዮጵያ በሠላም ለዘለዓለም በክብር ትኑር!! ሠላም ለሁሉም በቸር ይግጠመን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule