• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንግሥትና ኦዲፒ የጃዋርን የድጎማ በጀት ጥያቄ ውድቅ አደረጉ

October 17, 2019 06:39 am by Editor Leave a Comment

የኦሮሞ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ሥራ አስኪያጅና ባለቤት ጃዋር መሃመድ ለድርጅቱ በጀት እንዲመደብና በቋሚነት እንዲረዳ ለመንግሥት ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ መደረጉ ታወቀ። የጎልጉል የኦዲፒ የመረጃ ምንጮች እንዳሉት የድጎማ ጥያቄው ውድቅ መደረጉ ጃዋር በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይና በኦዲፒ ላይ የጥላቻ ሪፖርት ተጠናክሮ እንደሚሠራ መናገራቸውን አመልክተዋል። በተያያዘ ጃዋር የሚመራው ኦ.ኤም.ኤን. ለሸዋ ተወላጅ ኦሮሞዎች መድረክ እንደማይሰጥና ኦነግ በንጹሃን ላይ እየፈጸመ ያለውን ግድያም ሽፋን እንዲሰጥ እንደማይፈቅድ ተገልጿል።

እንደ መረጃ አቀባዮቹ ከሆነ ጃዋር ለሚመራው “የትግል ሚዲያ” ከፍተኛ በጀት የጠየቀው ሚዲያው ለተገኘው ለውጥ ትልቁን ሚና ተጫውቷል በሚል ነው። ኦ.ኤም.ኤን. በትግሉ ወቅት የአንበሳውን ድርሻ በመጫወቱ የኦሮሚያ ክልልም ሆነ መንግሥት ሊደጉመው እንደሚገባ በተደጋጋሚ ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ የተደረገው በሥራ አስፈጻሚ ውሳኔ ነው።

ጃዋር ድጎማው እንደማይሰጠው ከተገለጸለት በኋላ በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ በስፋት የአየር ሰዓት እንዲያገኝ ትዕዛዝ መስጠቱን ኦ.ኤም.ኤን. የሚሠሩ እንደነገሯቸው የመረጃው ክፍሎች ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ አስታውቀዋል።

በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዓለም ሰላም የኖቤል ተሸላሚ መሆናቸው ይፋ መሆኑንን ተከትሎ የዓለም ሚዲያ ሰፊ ሽፋን ቢሰጡትም ኦ.ኤም.ኤን. ግን ቀዳሚ ዜና እንኳን ያላደረገው በዚሁ ምክንያት እንደሆነ ታውቋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ታላቅ ሽልማት አስመልክቶ በተለያዩ የኦሮሚያና የክልል ከተሞች የተደረገውን የድጋፍና የደስታ መግለጫ ሰልፍ ኦ.ኤም.ኤን. በተመሳሳይ የሚገባውን ሽፋን እንዳልሰጠው መረጃ የሰጡት ክፍሎች ገልጸዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያም ጃዋር መሃመድ በስፋት ሲወገዝ ተሰምቷል።

ጃዋር በፌስቡክ ገጹ የእንኳን ደስ አለህ አጭር መልዕክት ከመለጠፉ በዘለለ የተገኘውን ዜና ሁሉ “ሰበር” ለማለት የማያቅማማው ኦ.ኤም.ኤን. ለዜናው ጆሮ ዳባ ማለቱ በተለያዩ የኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ ጉምጉምታ እንደፈጠረ ጎልጉል ያናገራቸው አስረድተዋል።

ኦ.ኤም.ኤን. አገር ውስጥ በአንድ ጎረምሣ ስም ተመዝግቦ የሚሠራ ተቋም ሲሆን የድርጅቱ ገንዘብም በዚሁ ወጣት ስም በተከፈተ አካውንት እንደሚንቀሳቀስ የሚዲያው ምንጮች ይናገራሉ። ጃዋር በዜግነት ኢትዮጵያዊ ባለመሆኑ አንድ በገንዘቡ ላይ እንደፈለገ እንዲናኝ የተፈቀደለት ወጣት መሰየሙን የገለጹት ምንጮች ኦ.ኤም.ኤን. ነጻነት የሌለበት፣ ገቢና ውጪው የፋይናንስ ደንብን በአግባቡ የማይከተል ድርጅት እንደሆነ ጠቁመዋል።

ከወራት በፊት ራሳቸውን በዩቲዩብ ይፋ ያደረጉ ይህንኑ የተዝረከረከና አንድ ሰው እንዳሻው ለፈለገው ተግባር የሚጠቀምበት ሚዲያ ወደ ህግ ለማቅረብ እንደሚሠሩ መናገራቸው የሚታወስ ነው።

በሚሊዮን ብሮች የሚገመቱ እጅግ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን የሚሸምተውና “ቱጃር” የሚባለው ጃዋር መሃመድ አቋሙን ግልጽ አድርጎ ወደ ፖለቲካ የማይገባው በዚሁ የሚዲያ ነጋዴነት ለመቀጠል ሲል የቀድሞ የቦርድ አባላትን ማሰናበቱን የሚገልጸው የኦ.ኤም.ኤን. ባልደረባ “ጃዋር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላይ አነጣጥረው ዘመቻ ለሚያካሂዱ የሚዲያ አውታሮችና የፌስቡክ አርበኞች ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ድጋፍ የማድረግ ዕቅድ መንደፉን አስቀድሜ አውቃለሁ” ሲል ተናግሯል። ይሁን እንጂ እነማን እንደሆኑ የሚዲያ አውታሮቹን በስም አልጠራም። ከዕቅዱ ሌላ አንዳንዶቹን በድብቅ ቀጥተኛ ድጋፍ እያደረገላቸው እንዳለ ይነገራል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኦነግ-ሸኔ ባለፈው ቅዳሜ በምስራቅ ጉጂ ዞን ስለገደላቸው ስድስት ንጹሃን ዜጎች ኦ.ኤም.ኤን. ዘገባ አላቀረበም። አባቱ የተገደሉበት ሀጻን “አባቴ ገጠር ካለው ቤቱ ለሥራ ሄዶ ቁርስ እየበላ ሳለ የኦነግ ታጣቂዎች ገብተው ገድለውት ሄዱ” ሲል ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ (ቪ.ኦ.ኤ.) ቢናገርም ለኦ.ኤም.ኤን. የዜና ፍጆታ ብቁ አለመሆኑ በኦሮሞዎችም ሆኑ በሰላም ወዳድ ዜጎች መነጋገሪያ መሆኑ ታውቋል።

የኦ.ኤም.ኤን. ባለቤት ጃዋር መሃመድ የቅማንት ዜና ላይ ሙጥኝ በማለት የህወሓት አጀንዳ አስፈጻሚ መሆኑና ዘንድ “እረኛውን ግደል፣ መንጋው ይበተናል” የሚለውን የዲጂታል ወያኔ ዓላማ መደገፉ፣ ዝምታን በመረጡት አብዛኛው የኦሮሞ ተወላጆና ነዋሪዎች ዘንድ እየተብሰለሰለ ያለ ጉዳይ እንደሆነ በርካቶች እየተናገሩ ነው።

ጃዋር የአሜሪካ ዜግነቱን እንደሚመልስ (ቀድጄ እጥለዋለሁ እስከማለት) በተደጋጋሚ ቢናገርም እስካሁን እርሱም ሆነ ቤተሰቡ የሚታወቁት በአሜሪካ ዜግነት ነው። በአሜሪካ አገር የተከፈተው ኦ.ኤም.ኤን. በሕግ የተመዘገበው በትርፍ አልባ ድርጅት ስም ሲሆን እኤአ ከ2014 እስከ 2017 አምኖ ለአሜሪካ መንግሥት ሪፖርት ያደረገው የድርጅቱ አጠቃላይ ገቢ ከ2.8 ሚሊየን ዶላር በላይ (በብር እስከ 100 ሚሊየን) ነው። ይህ የ2018 ዓም የድርጅቱን ገቢውን ሳይጨምር ነው።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የኦ.ኤም.ኤን. የቀድሞ የቦርድ አባልትም ሆኑ መረጃ ያላቸው ወገኖች አስተያየት መስጠት ከፈለጉ ለማስተናገድ ዝግጁ ነው። ጃዋርን በስልክ ለማግኘት የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ሙከራ ቢያደርግም ሊሳካለት አልቻለም።

በተያያዘ ዜና በምን ምክንያት እንደሆነ በውል ባይታወቅም ቀደም ሲል የኦነግ-ሸኔ ወታደሮችን ጫካ ድረስ እየሄዱ ሲያደራድሩና ሲያስማሙ የነበሩት እንዲሁም ወደ ካምፕ እንዲገቡ በማድረጉ ውስጥ ቀዳሚ የነበሩት በቀለ ገርባ በቅርቡ ኢትዮ ፎረም ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ “ሸኔ የሚባል ቡድን የለም” ሲሉ ተደምጠዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Ethiopia, Full Width Top, funds, jawar, Middle Column, omn

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule