• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል!”

July 26, 2013 12:33 am by Editor Leave a Comment

2005 ዓ.ም ከ1998 ዓ.ም በኋላ በተግባር ሊታይ የሚችል የፖለቲካ እንቅስቃሴ የታየበት አመት ነው ብል የተሳሳትኩ አይመስለኝም ፡፡ በተለይ በግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ፣ም የሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ምንአልባትም ወደኋላ ይጓዝ የነበረውን የሀገር ውስጥ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከማስቆም በዘለለ ወደፊት እንዲጓዝ ያደረገው ይመስለኛል፡፡ ከዚህ እለት በኋላ ባሉት ቀናቶች ውስጥ በርካታ ፓርቲዎች ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ለማድረግ በዝግጅት ላይ ይገኛሉ። በተለይ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ለዚህ ማሳያ ነው፡፡ ድርጅቱ በደሴና በጎንደር የተሳኩ ሁለት ሰልፎችን በአንድ ቀን አድርጓል፡፡

ለዛሬ ይህን እንድጽፍ ያነሳሳኝ ግን ይህን እንቅስቃሴ ተከትሎ እየተነሱ ያሉት እንዳንድ አሉታዎችን ለማየትና የራሴን ምልከታ ለመጠቆም ያህል ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ያለው የፕሬስ እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ማለት በሚቻልበት ሁኔታ አለ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም (ያ ጉምቱ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እየያዘ ከሚመጣቸው መጽሄትና ጋዜጦች በቀር፤ እነሱንም አንብበን ሳናጣጥም እና በጽሁፎቹ ዙርያ ሳንወያይ ያው የስርአቱ ጡጫ ያርፍባቸዋል) ታዲያ በዚህ ክፍተት ውስጥ ትልቅ የመነጋገሪያና የመያያ መድረክ እየሆኑ የመጡት ማህበራዊ ገጾች እና ድረ ገጾች ናቸው፡፡ እነዚህ ሚዲያዎች ይህንን ክፍተት በመሙላት ደረጃ ትልቅ እተዋጽኦ እያበረከቱ የመሆናቸውን ያህል ሰዎችንም ወደ ተሳሳተ መንገድ እና አመለካከትም የመምራት እድል አላቸው፡፡

ሰሞኑን እየተደረጉ ካሉት የፖለቲካ እንቅስቃሴ ጎን ለጎን በነዚህ ማህበራዊ ድረ ገጾች አንዳንድ ግለሰቦችና ግሩፖች በተለይ የሰማያዊ ፓርቲና የአንድነት ፓርቲ በተናጥል እያደረጉ ያሉትን እንቅስቃሴ ወደ ፉክክር መንፈስ በመውሰድ አላስፈላጊ ቃላቶችንና በመጠቀም ድርጅቶችን ወይም ግለሰቦችን ሌብል እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ ድርጅቶቹን ወደ ተለመደው “ተባበሩ ወይም ተሰባበሩ” የሚል አሰልች ዝማሪያቸው የተመለሱም በብዛት አሉ፡፡

ለመሆኑ ህብረት ወይም ትብብር ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ያልተሞከረ ነውን? የኢትዮጵያንስ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የጎዳው ህብረት አለመኖሩ ነውን? እነዚህ ጥያቄዎች ምንም እንኳ ጥልቅ ጥናት የሚፈልጉ ቢሆኑም ለኔ በደፋናው አይመስሉኝም (ከተሳሳትኩ ለመታረም ዝግጁ ነኝ) በኢትየጵያ ፖለቲካ ከፓርቲዎች ብዛት እኩል ለቁጥር አሰልቺ የሆኑ ህብረቶችና ጥምረቶችን ሀገር ወስጥ ባሉም ከሀገር ውጭ ባሉም ድርጅቶች መካከል አይተናል፡፡ አንዳቸውም ግን መሰረታዊ ለውጥ ሲያመጡ አልታዩም ወይም የተጣመሩበትን ግብ እስኪመቱ እንኳ መቆየት አላቻሉም፡፡ እንደኔ በኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ ፓርቲ እንዳይኖር ካደረጉት ምክንያቶች እንዱ ይህ “የህብረት” መንፈስ ይመስለኛል፡፡ አንድ ድርጅት ጠንክሮ የመውጣት አዝማሚያ ሲያሳይ ደካሞች የሚጠፉ ወይም የለመዱትን ጥቅማጥቅም የሚያጡ ስለሚመስላቸው ያንን ድርጅት ከነሱ ቁመት እንዳይበልጥ ወይም እራሳቸውን ከነችግራቸው እና ከነድክመቶቻቸው ካለ እነሱ እንዳይጓዝ ለማድረግ ሁሌ በኋላ ኪሳቸው የሚያስቀምጧትን ካርዳቸውን ይመዛሉ “ህብረት” ከዛም የጥፋት ዘራቸውን ይበትናሉ፡፡

መጀመሪያ ወደ ተነሳሁበት እና ወቅታዊ ወደ ሆነው ጉዳይ ስመለስ በተለይ በቅርቡ እየተካሄዱ ባሉት ሰልፎች ዙርያ የተጀመረው ሰማያዊንና አንድነት ፓርቲን (ሶሊ እንዳለችው “ለትልቅ አላማ ሲባል”) ተባብራችሁ አንድ ላይ ስሩ ጥሪ ጊዜውን የጠበቀ አለመሆኑን ጉዳትም እንዳለው በግርድፉ ለማሳየት እሞክራለሁ፡፡

የመጀመሪያው ከትግል ስትራቴጂ አንጻር እንየው፡፡ የሁለቱ ተቋማት በተናጥል ትግል ማድረጋቸው በተወሰነም ደረጃ ድርጅቶቹ ላይ ስርአቱ የሚሰነዝርባቸውን ዱላ ወይም ውንጀላ ይቀንሰዋል፡፡ ትላንት ሰማያዊ ፓርቲ ባደረገው ሰልፍ የስርአቱ አጋፋሪዎች እስኪነጋ አላደርስ ብሏቸው የዛኑ እለት ድርጅቱን ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር መድበውት እንደነበርና በአመራሮቹም ላይ ክስ ለመመስረት በዝግጅት ላይ እንደነበሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ ሰማያዊ ፓርቲ በ3 ወር ውስጥ መንግስት መልስ ካልሰጠ ከፍ ባለ ደረጃ ሰልፍ ለመጥራት ቃል መግባቱን ተያይዞ መንግስት ትኩረቱ ሁሉ በሰማያዊ ላይ ያደረገ ይመስል ነበር፡፡ ሆኖም ይህንን ህዝባዊ ንቅናቄ አንድነት በፍጥነት በመቀላቀሉ መንግስትን ክፍኛ ስላስደነገጠው የትኩረነት አቅጣጫውን በተወሰነ ደረጃ ከሰማያዊ ፓርቲ ወደ አንድነት አዙሯል ለማለት ይቻላል፡፡ ነገር ግን እንዚህ ድርጅቶች በጋራ እንቅስቀቃሴ ቢያደርጉ የስርአቱን አቅጣጫ እና ሀይል በአንድ መሰመር ስለሚያደርገው የእንቅስቃሲያቸውን እድሜ የማጠሩ እድል ከማስፋቱም በዘለለ መንግስት በአንዱ ተቋም ላይ እርምጃ ቢወስድ ሌላው ጥያቄዎቹን አንስቶ የመቀጠል እድሉን ያጠበዋል፡፡

ሁለተኛው አንድነት አሁን የሚገኝበት ሁነት በመነሳት ሰማያዊ ብቻውን ቢጓዝ በግሌ እመርጣለሁ፡፡ አንድት አሁን ያለበት ሁነት ስል ድርጅቱ ከመድረክ ጋር የጀመረው እንቅስቃሴ (የመድረከ ግንባር አባል ነው) በተለያዩ ሚዲያዎች እንደምናየው ገና እልባት ያላገኘና በፓርቲው የውስጥ ስነስርአትና መዋቅር ውይይቶችና ጥናቶች እየተካሄዱ በመሆናቸው እንዲሁም ከ33 የፓርቲዎች ህብረትም ጋር የጋር የትግል እንቅስቃሴ እየነደፉ ስለሚገኙ፤ ሰማያዊ ደግሞ በወጣቶች የተመሰረተና ገና አዲስ ድርጅት እንደመሆኑ እንደዚህ ያሉ የማይመለከቱት እና አላስፈላጊ የውስጥ ፖለቲካ ንትርኮች ውስጥ ገብቶ እድሜውን እንዳያሳጥር ስለምሰጋ በጀመሩት ጠንካራ የፖለቲካ ባህል ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ፍጹም በመከባበር ትግላቸውን ወደፊት ቢቀጥሉ እመርጣለሁ፡፡ ለረጅም አመታት የቆሰልንበት የውስጥ ፖለቲካ ሽኩቻ ሰለባ እንዳይሆን ከመስጋቴ የተነሳ እንደሆን ተረዱልኝ፡፡

ሶስተኛው ምክንያቴ በሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ ያሉት አንዳንድ ወጣቶች ከዚህ ቀደም በአንድነት ፓርቲ ውስጥ የነበሩና በድርጅቱ ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባት “ዝም አንልም” በሚል ከፓርቲው የወጡ እንደመሆናቸው ከአንድነት ፓርቲ ጋር በአሁኑ ወቅት ያለው መልካም ግንኘነትን በጥንቃቄ መያዝና ይህንንም ግንኘነት ወደፊት አጠንክሮ ማስቀጥል ከተፈለገ ነገሮች በእርጋታ እና ለተጨማሪ ንግግሮችና የጎንዮሽ ግንኙነቶች ጊዜ መስጠት በጣሙን አስፈላጊ ነው ብዬ ስለማምን ይህንን ጊዜውን ያልጠበቀ “ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ” ድርጅቶቹ በራሳቸው ጊዜ እያሻሻሉት ያለውን ግንኙነት አጉል ተቆርቋሪ ነኝ በሚል ያለወቅቱ በማንሳት የተጀመረውን ጠናካራ ሀገራዊ ንቅናቄ ወደኋላ ከመጎተት ውጭ ጥቅም ይኖረዋል ብዬ አላምንም፡፡

በአጠቃላይ በፓርቲዎች መካካል የሚደረጉ ህብረቶች ወይም ጥምረቶች በድርጅቶቹ በራሳቸው ግንኙነት እና እምነት ጊዜውን ጠብቆ መምጣት ይኖርበታል፡፡ አለበለዚያ ከዚህ በፊት እንደለመድነው “ለትልቅ አላማ”  በሚል በግድ በሙጫ ለማጣበቅ የሚደረግ ጥረት ነገ በትንሽ ንቅናቄ እንደሚገነጠል ጥርጥር የለኝም፡፡

አርአያ ጌታቸው
አርአያ ጌታቸው

ደግሜ እላችኋለሁ መተባበር ባንችል አንጠላለፍ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

(ይህ ጽሁፍ የአርአያ ጌታቸውን አቋም ብቻ የሚያንጸባርቅ ነው፡፡  እንዲሁም ይህን እንድጽፍ ያነሳሳኘ “በስመ ተቃዋሚ ተቃቅፎ መሳሳም” – ለትልቁ ዓላማ? በሚል በሶሊያና ሽመል የተፃፈውን ካነበብኩ በኋላ ነው )

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule