• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ጋዜጣዊ መግለጫቸው

October 6, 2013 09:48 am by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ ከአካላዊ እንቅስቃሴያቸው እና ድምፀታቸው ጀምሮ እስከ ሚቀልዷቸው ቀልዶች እና የሚያስተላልፏቸው መልዕክቶች በሙሉ የቀድሞውን ሟች ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሚያስታውስ መልኩ ያካሄዱት ጋዜጣዊ መግለጫ ባብዛኛው ተቃርኖ የበዛበት ነው፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም በጋዜጣዊ መግለጫቸው ከጥያቄ እና መልሱ አስቀድመው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መንግስት ያለውን መረጃ የተናገሩ ሲሆን እንዲሁ በደፈናው አሃዝ ሳይጠቅሱ የሃገሪቱ ምጣኔሃብት እያደገ መሆኑን፤ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ዘርፉ ካለፈው አመት የተሻለ መሆኑን እና በሰላም እና ጸጥታ ጉዳዮች ዙሪያ ከጎረቤት ሃገራት ጋር ኢትዮጵያ ያላትን ግንኙነት ለማብራራት ሞክረዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ከኤርትራ በስተቀር ከሌሎች ጎረቤት ሃገራት ጋር ያላት ግንኙነት ስትራቴጂካዊ መሆኑን ጠቅሰው፤ በተለይ የኢትዮጵያ መንግስት ከሶማሊያ መንግስት ጋር ያለውን ግንኙነት ዘርዝረዋል፡፡

እንደ እርሳቸው አገላለጽ የኢትዮጵያ መንግስት የሶማሊያ የፌዴራል መንግስት ከሃገሩ የክልል አስተዳደሮች ጋር ተስማምቶ እንዲሰራ ኢትዮጵያ የማደራደር ሚና እየተጫወተች እንደሆነ እና አልሸባብ የተባለውን አሸባሪ ሃይል ለማጥፋት በሶማሊያ ከሰፈረው የአፍሪካ ሰላም አስከባሪ ጦር ጋር በመተባበር ጥረት በማድግ ላይ ናት በማለት ሃገሪቱ በሶማሊያ ያላትን ዘርፈብዙ ጣልቃገብነት በሚያሳብቅ መልኩ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ሃይለማሪያም እንዳሉት በኢትዮጵያ ብሎም ባጠቃላዩ ምስራቅ አፍሪካ ቀጠና የደህንነት ችግር አለ፤ ነገርግን የእርሳቸው አስተዳደር በሶማሊያ የሚያደርገው ጣልቃ ገብነት ለድህንነት ችግሩ መባባስ አንዱ ምክንያት እንደሆነ ማመን የፈለጉ አይመስልም፡፡

ኤርትራን በተመለከተ በተለይ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቄ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል የመግዛት እቅድ አለን ማለታቸውን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ የኢትዮጵያ መንግስት ከዘጠኝ ዓመት በፊት ጀምሮ በሁለቱ ሃገራት መካከል ሰላም እንዲፈጠር ጽኑ አቋም እንደ ያዘ እና ጥረት እያደረገ ነው ያሉ ሲሆን፤ በኤርትራ በኩል ግን ይህ ዝግጁነት የለም ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ መብራት ከኢትዮጵያ እንገዛለን ማለታቸውን አስመልክቶ የራሳቸው ብቻ ፍላጎት ነው ያሉ ሲሆን፣ ምናልባትም አጣብቂኝ ውስጥ ስለሚገኝ ኑዛዜ ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ መንግስት ጋር ሰላም መፍጠር ይፈልጋል ብለው በተናገሩበት አንደበታቸው ጠቅላሚኒስትሩ የኤርትራ መንግስት ለራሱ ሳይሆን ሌሎችን ለመርዳት እየጣረ ይገኛል በሚል ለራሷ ክንፏ ተሰብሮ ሌላ ለመደገፍ እንደምትሄድ አሞራ መስለውታል፡፡

ሃገር ቤት ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች የሚያካሂዱትን የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተም ለቀረበላቸው ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስላቅ የተቀላቀለበት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ እንደ ሃይለማሪያም ንግግር ሃገር ውስጥ የሚገኙ የተቃዋሚ ሃይሎች በየሳምቱ በሚያደርጓቸው ሰላማዊ ሰልፎች ተደጋጋሚ ጥያቄ ነው የሚያነሱት፡፡  እርሳቸው እንዳሉ ለጥያቄዎቹ መንግስት ቀደም ብሎ መልስ የሰጠባቸው ስለሆነ ተጨማሪ ከመንግስት የሚመጣ ነገር የለም፡፡

ሰልፎቹ በዚህ ሁኔታ የሚቀጥሉ ከሆነም የሆነ ግዜ መንግስት ሊያስቆመው እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሃገርቤት ተቃዋሚዎች የሚያሰሟቸው ጥያቄዎች የራሳቸው እንዳልሆኑ እና እንደ እርሳቸው አባባል በተለያዩ ሃገሮች ያሉ ሌሎች ሃይሎች የሰጧቸው የቤት ስራዎች ናቸው፡፡

በዚህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር፤ ለምሳሌ ሰማያዊ ፓርቲ እና አንድነት ፓርቲ የታሰሩ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞች እንዲፈቱ፣ መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ላይ ጣልቃ እንዳይገባ፣ የኑሮ ውድነት የመሳሰሉት ጉዳዮች እንዲሻሻሉ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች መልስ አያገኙም ማለት ነው፡፡

በውጭ ካሉ የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ በተመለከተ ግንቦት ሰባት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ባጭሩ ህልም ነው፤ ማለም ይችላሉ ያሉ ሲሆን በፓርቲያቸው ውስጥ መሰንጠቅ ስለመኖሩም ለተነሳው ጥያቄ ምኞት ነው መመኘት ትችላላችሁ የሚል ድፍን ያለ መልስ ሰጥተዋል፡፡

ሌላው በተቃርኖ የታጀበው የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልስ ሙስና እና ኢንቨስትመንትን በተመለከተ የቀረበላቸው ሲሆን መንግስታቸው የሙስና ቀዳዳን እያጠፋ ተወዳዳሪነት የሰፈነበት አንቨስትመንት እንዲኖር ያበረታታል ብለው የተናገሩ ሲሆን፡፡

ሙስና ውስጥ የገቡ ባለሃብቶችን መንግስት እየተከታተለ እንደሆነ እና ሙስና ጋር ያልተነካኩ ባለሃብቶች ይህ ሊያሰጋቸው እንደማይገባ የገለፁ ቢሆንም በመቀጠል ደግሞ እስካሁን ስርቆት የፈፀሙ ባለሃብቶች ካሁን በኋላ ቢያቆሙ ጥሩ ነው በማለት ከዚህ ቀደም ለተፈጸሙ ዝርፊያዎች እውቅና ሰጥተዋል፡፡

እንዲሁም የቁጠባ ቤቶችን በተመለከተ የወጣው መመሪያ የቁጠባ ቤት ተመዝጋቢዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ ነው መቆጠብ የሚችሉት መባሉ የሌሎች የግል ባንኮችን ተወዳዳሪነት ይቀንሳል መባሉ የተሳሳተ ትንተና የተካሄደበት ትችት ነው ያሉ ሲሆን ባንኩ ሰዎች ከሚቆጥቡት 20 በመቶ ገንዘብ ላይ 80 በመቶ ጨምሮ ስለሚያበድራቸው  ተጎጂ እንደሆነ ለማብራራት ሙከራ አድርገዋል፡፡

ነገርግን በዚህ መልሳቸው ባንኩ 80 በመቶ ብድር ሲሰጥ ጎን ለጎን በብቸኝነት ኢንቨስትመንት እያካሄደ ስለመሆኑ የሰጠውን ብድር መልሶ ከወለድ ጋር እንደሚያገኘው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘነጉት ይመስላል፡፡

በመሰረተ ልማት ላይ ስለሚገኙ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ለተጠየቁት ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ከፖለቲካዊ ችሎታቸው ይልቅ የምህንድስና ሙያ እውቀታቸውን ተጠቅመው ለማብራራት ሙከራ ያደረጉ ሲሆን እዚህም ላይ ግራ አጋቢ መልሶች እና ማብራሪያዎች ሰጥተዋል፡፡

የተፋሰስ ችግር በመኖሩ የአስፋልት መንገዶችን እያበላሻቸው መሆኑን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀድሞ ነገር መንገዶቹ ሲሰሩ ተፋሰሱንም አብሮ መስራት ለምን እንዳልተቻለ አልጠቆሙም፡፡

በተመሳሳይ መልኩ የመብራት ችግር በተለይ በመኖሪያ አካባቢዎች መብራት የሚቋረጠው አዳዲስ ማሽን ቤቶች በብዛት ስለሚከፈቱ እና በየአካባቢው ያሉ ማከፋፋያዎች ለእነዚህ የሚሆን ሃይል የመሸከም አቅም ስለሌላቸው ነው በሚል ቴክኒካል መልስ የሰጡ ሲሆን እንደ ቃሊት አካባቢ ለሚገኙ የኢንዱስትሪ አካባቢ የሚባሉ አካባቢዎችም ችግሩ ተመሳሳይ እንደሆነ ነው ያብራሩት፡፡

የሞባይል ኔትዎርክ መጣበብ ችግርም ተጠቃሚ ከታቀደው በላይ ስለበዛ ነው ያሉ ሲሆን ይህ የእቅድ እና ነባራዊ ሁኔታ አለመጣጣም እንዲሁም በተደጋጋሚ የሚያነሱት የአፈጻፀም ችግር በቀድሞውም ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሰጥ የነበረ ሲሆን ይህ የማቀድ እና የማስፈጸም ችግር ከመንግስት ብቃት ማነስ ጋር ስለመያያዙ ማንሳት የፈለጉ አይመስሉም፡፡

ባጠቃላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ  አስተዳደራቸውን ምዕሉ በኩለሄ አይነት አድርገው የሳሉት ሲሆን ለተፈጠሩ ችግሮች ሁሉ ሰበብ አስባብ ከመደርደር የዘለለ መልስ አልሰጡም፡፡

ከአጠቃላይ መግለጫው ግን አንድ ነገር በእርግጠኝነት እንድንገነዘብ አድርገውናል፤ ኢህአዴግ ሌላው ቢቀር የአቀራረብ ለውጥ እንኳ እንደማይኖረው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule