• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተማሪዎች ዓመጽና የየአካባቢው አጫጭር መረጃዎች

December 12, 2017 08:44 pm by Editor Leave a Comment

አክሱም ዩኒቨርሲቲ

አክሱም ዩኒቨርሲቲ በየግማሽ ቀኑ ሲነሳና ሲበርድ ነው የሰነበተው። በካፌ ሰዓት ብዙ ጊዜ ድንጋይ ይወረወራል። ማምሻውን በራት ሰዓት በተፈጠረው ብጥብጥ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትና መውጣት አይቻልም ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠው ወደ ቤተሰቦቻቸው ቢሔዱም እስካሁን መውጣት የሚፈልጉ ከሁለት ሺህ በላይ የዐማራ ተማሪዎች አሉ።


አዲግራት ዩኒቨርሲቲ

ዛሬ ጠዋት በነበረው ብጥብጥ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትና መውጣት አይቻልም ነበር። በአዲግራት እስካሁን የተረጋገጠ 9 ያክል ተማሪዎች ሕይወት ጠፍቷል፣ በርካቶች ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል። ወደ 30 የሚጠጉ የአማራ ተወላጆች በአዲግራት የተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች ታስረው ቶርች ተደርገዋል፤ እስካሁንም አልተፈቱም። ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመሔድ ቢፈልጉም አልተቻለም። ገዳም እንገባለን ብለው የወጡ ተማሪዎችም የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል።


መቀሌ ዩኒቨርሲቲ

በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ግቢ ማምሻው ግጭት እንደተፈጠረ መረጃዎች ቢወጡም ዝርዝር ማግኘት አልተቻለም። ዘግይቶ በመጣ መረጃ ደግሞ ግቢው ውስጥ ከፍተኛ ፍንዳታ ደርሶ መብራት ጠፍቶ የተማሪዎች ጩኸትና ለቅሦ እንደሚሰማ ነው የገለጹልን።

(ተጨማሪ፤ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሳይንስ ግቢ ማምሻውን እንዳልከው ከባድ የፍንዳታ ድምፅ ተሠምቶ መብራት ተማሪዎቹ መጮህ እንደጀመሩና ወዲያው የፌዴራል ፖሊሥ ጊቢው ውስጥ መግባቱን ዶርማቸው ውስጥ ሆነው ያዩ ልጆች ነግረውኛል። ይሄንን ስፅፍ በድጋሚ በሜሴጅ በላኩልኝ መልእክት መብራቱ አልመጣም ግቢው ግን መረጋጋቱን ነግረውኛል ። Abate Azagae)


ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

ትናንት በማራኪ ካምፓስ ተማሪዎች ሰላማዊ ተቃውሞ ጀምረው ነበር፤ “አዲግራት ያሉ ወንድሞቻችን ላይ የሚደርሰው ጭፍጨፋ ይቁም!” “የዐማራ ደም መፍሰስ ይቁም!” ወዘተ የሚሉ ተቃውሞዎች በማራኪና ቴዎድሮስ ካምፓሶች ቀጥለው ከሕዝብ ጋር ሊደባለቁ ሲል በአጋዚ ከግቢ እንዳይወጡ ተደርገዋል። ዛሬም ከሆስፒታሉ ውጭ በሁሉም ካምፓሶች ተቃውሞዎች ቀጥለው ነበር፤ ነገር ግን የጠዳው ግቢ የአጋዚ ወታደሮች ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል። በጥይት የተገደሉ ተማሪዎች ሁሉ እንዳሉ ነው የተገለጸው።


ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ

ትናንት ሌሊት በአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የነበረውን የዐማራ ጭፍጨፋ በማውገዝ የተጀመረው ተቃውሞ የትምህርት መማር ማስተማር ሒደቱን ሙሉ በሙሉ አቋርጦታል። ከአዲግራት የተገደለ አንድ ልጅ አስከሬን የሚመጣ አለ መባሉ የበለጠ ችግሩን አባብሶታል። አጋዚ ወደ ግቢው መግባቱንም ሰምተናል።


ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ

ጠዋት ዘንዘሊማ ኮሌጅ የጀመረው ተቃውሞ ግማሽ ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ፖሊን፣ ፔዳንና ይባብ ኮሌጆችን ጭምር አዳርሷል። የትግራይ ተማሪዎች አዲስ ዓምባ የተባለ ባለሦስት ኮከብ ሆቴል ውስጥ ገብተው ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገላቸው ሲሆን የፌደራል ፖሊስና አጋዚ ቀሪ ተማሪዎችን እያሰረ ነው። ምሽት ላይ ፖሊ ግቢ መጠነኛ ቃጠሎ ደርሶ ወዲያውኑ ጠፍቷል።


ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

በደብረ ማርቆስ ማምሻውን ነው የተማሪዎች ተቃውሞ የጀመረው። ሆኖም በዝግጅት ሲጠባበቅ የነበረው የፌደራል ፖሊስና አጋዚ በተማሪዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል ተብሏል።


ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ

በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረው ተቃውሞ እስካሁን አልበረደም። የትግራይ ተማሪዎች በወልዲያ ስታዲየም ጥበቃ እየተደረገላቸው ነው፤ ከዩኒቨርሲቲው በመከላከያና ፌደራል ፖሊስ ነው ተመርጠው የወጡት። ሌሊት አንድ ሕንጻ በእሳት ጉዳት ደርሶበታል። በወልዲያ ትምህርት ቤቶችም ዝግ ሆነው ውለዋል።

ዛሬ ደግሞ በዩኒቨርሲቲው መርሣ ካምፓስ አዲስ ተቃውሞ ጀምሯል።


ውጫሌ ውርጌሳ

በውጫሌና ውርጌሳ የተጀመረው ተቃውሞ ትናንት ነው። “ልጆቻችን ሳይመለሱ ወደ መሀል አገር ወይም ከመሀል አገር ወደ ትግራይ የሚሔድ መኪና መኖር የለበትም” በሚል ነው ተቃውሞው የተነሳው። አንድ ልጅ ከአዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተገደለ አለ መባሉ የበለጠ ጉዳዩን አወሳስቦታል። ጥቂት መኪናዎች ተቃጥለዋል። የሰላም ባስ ተሰባብሯል።

ትምህርት ቤቶች ዝግ ሆነው ውለዋል።

ሙሉቀን ተስፋው (Muluken Tesfaw)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule