• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢኮኖሚው [እንዳወራነው] አላደገም!

October 20, 2015 08:12 pm by Editor Leave a Comment

በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት ሰሞኑን ዕቅድ ብሎ ባወጣው ዘገባ ላይ ለዓመታት ሲወራለት የነበረው የድርብ አኃዝ ዕድገት እንደተደሰኮረለት እንዳልሆነ እንዲያውም ኢኮኖሚው ውድቀት ላይ መሆኑን የሥራ አጥነት ሁኔታ አሳሳቢ ከመሆኑ የተነሳ በከተማዎች ብቻ ሳይሆን በገጠርም ችግር እየሆነ መምጣቱን ለራሱ ባመነበት የኢኮኖሚ ፕላን ላይ አትቷል፡፡ ነገረ ኢትዮጵያ/Negere Ethiopia በፌስቡክ ገጹ ላይ ያወጣው ዘገባ ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

መንግስት ኢኮኖሚው ውድቀት ላይ መሆኑን አመነ

• የኢኮኖሚ መዋቅሩ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራትም ያነሰ ነው

• የወጪ ንግድ ገቢ እና የገቢ ንግድ ክፍተት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል

• ለውጭ ገበያ የቀረበው አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ ሰሊጥና የጥራጥሬ ሰብሎች መጠን በእቅዱ ከተያዘው በእጅጉ ያነሰ ነው

• ለውጭ ይቀርባል ተብሎ ከታቀደው ቡና የቀረበው ሩቡ ብቻ ነው

• መስራት የሚቻለውን ያህል የልማት ሥራ ሳይሰራ ቀርቷል

• ሥራ አጥነት በከተማ ብቻ ሳይሆን በገጠር አካባቢዎችም ሰፊ ችግር ሆኗል

ላለፉት 10 አመታት ኢትዮጵያ 11.2 በመቶ በማደግ በዓለም ፈጣን እድገት እያሳዩ ከሚገኙ ጥቂት ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነችና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት ጋር ልትመደብ እንደሆነ ሲናገር የነበረው ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የኢኮኖሚ ውድቀት እንዳጋጠመው አመነ፡፡ የብሔራዊ የፕላን ኮሚሽን በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም የሁለተኛውን አምስት አመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ (ከ2008-2012 ዓ.ም) ላይ ለመወያየት ያዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ እንደሚያሳየው በተለይም መንግስት ለኢኮኖሚው አንቀሳቃሽ ሞተር ነው የሚለው የግብርና ዘርፍ፣ የውጭ ንግድና የማኑፋክቼሪንግ ኢንዱስትሪው ውድቀት አጋጥሞታል፡፡plan

“በአጠቃላይ በተጠናቀቀው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን የተመዘገበው የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ከሚጠበቀው አንፃር ዝቅተኛ ነው፡፡ የኢኮኖሚው መዋቅር ለውጥ ከማረጋገጥ አንፃር የተመዘገበው አፈፃፀም ዝቅተኛ ነው” ያለው ሰነዱ የኢኮኖሚ መዋቅሩ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራትም ያነሰ እና በጣም ዝቅተኛ መሆኑን አስምሮበታል፡፡ በኢኮኖሚው ችግር ምክንያትም ስራ አጥነት ከከተሞች አልፎ በገጠረ አካባቢዎችም ሰፊ ችግር እንደሆነም ተመልክቷል፡፡

ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ይገኛል ተብሎ የተገመተው ገቢ በ2006 ዓ.ም ከነበረውም ያልተለየ፣ ከዚህ ገቢ የተገኘው የገቢ ንግድ (import) ወጪን የመሸፈን አቅሙም በ2007 ዓ.ም ከአለፈው ጊዜ ያነሰ ነው ያለው ሰነዱ፤ በወጪ ንግድ ገቢ (export) ወጪ እና በገቢ ንግድ ((import) ወጪ ያለው ክፍተትና ጉድለት እየሰፋ መጥቶ በ2007 ዓ.ም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል፡፡ የታየው ደካማ የውጭ ንግድ አፈፃፀም አስተማማኝ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት ኢኮኖሚውን ለማሳደግ፣ ከውጭ ብድርና እርዳታ ጥገኝነት ለመላቀቅ ለሚደረገው ጥረት ማነቆ እንደሆነ በሰነዱ ላይ ሰፍሯል፡፡

የውጭ ንግድ መዳከም የውጭ ምንዛሬ ለሚፈልጉትና አቀድኳቸው ላላቸው የመሰረተ ልማት፣ የኢንዱስትሪና የማህበራዊ ልማት እንዳይሳኩ እየፈጠረው ያለው እንቅፋት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል፡፡ ለውጭ ገቢ ንግድ መዳከም በዋነኛነት የማምረት አቅም አለማደግ፣ የማኑፋክቸሪንግና የግብርና ሸቀጦች በመጠን፣ በአይነትም፣ በጥራት ማምረት አለመቻሉ እንደሆነ በሰነዱ ላይ ተገልፆአል፡፡

eprdfs economic policyበትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መጨረሻ ለውጭ ገበያ ይቀርባል ተብሎ የነበረው ቡና ሩብ ያህሉን እንኳን ማቅረብ አልተቻለም ያለው ሰነዱ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መጨረሻ ለውጭ ገበያ ይቀርባሉ ተብሎ የነበሩት የአበባ፣ የጨርቃጨርቅና የቆዳ ምርቶችም በቡና ገበያ ላይ ከታየውም በላይ ክፍተት እንደነበረበት በዝርዝር አስቀምጧል፡፡

ሰነዱም “በግብርና ዘርፍ የኤክስፖርት ሰብሎች የሆኑት አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ ሰሊጥና የጥራጥሬ ሰብሎች ሲሆኑ ለውጭ ገበያ የቀረበው መጠን ይደረጋል ተብሎ ከታቀደው በእጅጉ ያነሰና በማኑፋክቼሪንግ ነባር ኢንዳስትሪዎችና በከፍተኛ አቅማቸውና በጥራት እንዲያመርቱ፣ በተጨማሪም አዳዲስ ኢንቨስትመንትን በስፋትና በጥራት መልምሎ ወደ ሥራ ማስገባት በታቀደው ልክ ሊፈፀም ባለመቻሉ ለወጪ ንግድ የማምረት አቅማችን ዝቅተኛ መሆኑን ዋና ምክንያቶች ነበሩ” ብሏል፡፡

መንግስት በታክስ አሰባሰብም ትልቅ ክፍተት እንዳለበት ያመነው ሰነዱ “ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት አማካይ አፈፃፀም ለመድረስ በታክስ አስተዳደርና አሰባሰብ ተጨማሪ ጥረት ማደረግ እንዳለብን ያመለክታል፡፡ መሰብሰብ የሚችለው የታክስ ገቢ አለመሰብሰቡ መስራት የሚቻለውን ያህል የልማት ሥራ በዛው ልክ ሳይሰራ ቀርቷል ማለት እንደሆ ከልብ ሊጤን ይገባዋል” ብሏል፡፡


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule