ግብጽ የሃያ አንድ ክርስቲያን ዜጎችዋን በአይሲስ መታረድ ዜና እንደሰማች ዝም ብላ አልተቀመጠችም ነበር። ብሄራዊ የሃዘን ቀንም አላወጀችም። እንዲህ ነበር የሆነው። ከመቅጽበት ተዋጊ አውሮፕላኖችዋን አስነስታ ወደ ሊቢያ ላከቻቸው። የአይሲስ አራጆች የተከማቹበትን ደርና የተሰኘ ስፍራ እያከታተለች በቦምብ ቀጠቀጠችው። ብዙ አራጆች በድብደባው አለቁ። እንደ ግብጽ አጀማመር ቢሆን የሊብያው አይሲስ ክንፍ ድሮ-ድሮ ከምድረ-ገጽ ይጠፋ ነበር። ግና አልሆነም። አሜሪካ ጣልቃ ገባች። ግብጽ የአሜሪካን "ጸረ-ሽብር" ዘመቻ በማገዝዋ ምስጋና ማግኘት ሲገባት በተቃራኒው ተወገዘች። ከጥቂት ድብደባ በኋላ ፔንታጎን ግብጽን አስጠነቀቀ[0]። የኦባማ አተዳደርም ደብደባው በአፋጣኝ እንዲቆም ቀጭን መልእክት ላከ። ይህ ድርጊት ከዚህ ቀደም ስለ አይሲስ አፈጣጠር ኤድዋርድ ስኖደን[1] የለቀቀው ምስጢራዊ መረጃ ጋር … [Read more...] about አሜሪካ አይሲስን ለምን ፈጠረችው?
Opinions
“መንግሥት የሌለው እዚህ ብቻ ነው!”
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ስሞኑን በአሸባሪው አይሲስ የተወሰደውን አሰቃቂ ተግባር በማውገዝ በአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ያወጣው መግለጫ እንዲህ ይነበባል:- የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ መግለጫ ባለፈው እሁድ አይሲስ ባሰራጨው ቪዲዮ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች በሁለት የተለያዩ ቦታዎች ሲገደሉ ተመልክተናል። ስለ ቪዲዮው ብዙ ማለት ቢቻልም ወገኖቻችን ከአገራቸው ወጥተው ወደ ተሻለ ኑሮ ፍለጋ መንከራተታቸው ለዚህ ዓይነቱ አሰቃቂ ሞት ዳርጓቸዋል። ከአገራቸው የወጡት እየኖሩ ከመሞት ለመትረፍ ቢሆንም በስደት ደግሞ እጅግ መራራውን የሞት ጽዋ ጠጥተዋል። ይህ የወገኖቻችን ዕልቂት በዓለማችን ላይ በሚገኝ በምንም ዓይነት ቋንቋ፣ አገላለጽ፣ አጻጻፍ፣ እንባ፣ ወዘተ ሊገለጽ የማይችል ነው። ረዳት አልባ ሆነው የተመለከትነው ትዕይንታቸውም በውስጣችን ለዘመናት የማይሽር ቁስል ይዞ … [Read more...] about “መንግሥት የሌለው እዚህ ብቻ ነው!”
የሃዘኑ ድባብ በዱላ ታጅቦ. . .
የሃዘኑ ድባብ ከመብራቱ መቆራረጥ ጋር ተዳምሮ ጨለማውን አብሶታል። የአሁኑ መብራት መቋረጥ ግን ከወትሮ ፈረቃ ለየት ያለ ነው። ሆን ተብሎ የተደረገ ይመስላል። ከጥቂት ስፍራ በስተቀር ሁሉም ቦታ በአንዴ እንዲጠፋ ነው የተደረገው። ከሬድዋን ሁሴን እና ከሃይለማርያም የቴሌቭሽን ዲስኩር በኋላ ሃገሩ ሁሉ ጨለማ እንዲሆን አደረጉ። ይህንን ለማድረግም በቂ ምክንያት ነበራቸው። ሃዘን ያልወጣለት ህዝብ አደባባይ ወጥቶ በአረመኔ ወታደሮች ሲቀጠቀት በማህበራዊ ድረ-ገጽ እንዲታይ አልተፈለገም። ህዝቡ እርስበርስ መረጃ እንዲለዋወጥ መፍቀዱም አደጋ አለው። ስልኩም ጠፋ! ለጥቂት ጉልበተኞች ግን ይህ መብራት ከቶውንም አይጠፋም። ግዜው እስኪደርስ፣ የሚመኩበት ጉልበታቸው እስኪፈታ ድረስ ይበራል። እስከዚያው ብዙሃኑ በጨለማ ይኖራሉ። የአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር ግን ከቴድሮስ አድሃኖም ጋር ትንሽ … [Read more...] about የሃዘኑ ድባብ በዱላ ታጅቦ. . .
CREW Condemns the Massacre of Innocent Ethiopians by Extremists
Center for the Rights of Ethiopian women (CREW) strongly condemns the brutal murder of Ethiopian Christians in Libya and the recent xenophobic attacks of Ethiopians and other African migrants in South Africa. Thirty Ethiopians were brutally murdered by ISIS in Libya. Half of them were beheaded at a Libyan shoreline and the other half were shot dead in southern Libya, hundred miles from the shores. The released video showing the mass brutal killing refers to victims as those “belonging to … [Read more...] about CREW Condemns the Massacre of Innocent Ethiopians by Extremists
ከሰማያዊና ከአንድነት ሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ድርጅቶች ማህበራት የተሠጠ መግለጫ
በዚህ ባሣለፍነው ሣምንት በኢትዮጵያውያን ላይ በሊቢያና ደቡብ አፍሪካ የደረሰው እጅግ በጣም ዘግናኝ ጭካኔ የጅምላ ግድያ ማለትም በሊቢያ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን ወደ ዕስልምና እንዲቀየሩ ጠይቀዋቸው እምቢ ስላሏቸው ብቻ ግማሾቹን በቢላዋ አንገታቸውን አርደዋቸዋል፡፡ ግማሾቹን ደግሞ በጥይት እራሣቸውን በመምታት ሠላሳ(30) ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን በግፍ አይስል (ISIL) ተብሎ በሚጠራው የእስላማዊ አሸባሪ ቡድን ተሰውተዋል፡፡ በደቡብ አፍሪካም እንዲሁ ኢትዮጵያውያን ሰደተኞች ላይ ቤንዚን በማርከፍከፍ ከተሽከርካሪ ጐማ ጋር በማሰር ሦስት ኢትዮጵያውያን በእሣት ተቃጥለው እንዲሞቱ ተደርጓል፡፡ በደቡብ አፍሪካ ኢትዮጵያውን ስደተኞችን በእሣት ያቃጠሉት የደቡብ አፍሪካ ጥቁር ዜጐች ናቸው፡፡ በሁለቱም አገሮች የደረሰው አሠቃቂው የኢትዮጵያውያን ጅምላ ሞት ምከንያት ስር መሠረቱ ቁጥጥር ያጣው … [Read more...] about ከሰማያዊና ከአንድነት ሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ድርጅቶች ማህበራት የተሠጠ መግለጫ
“በሃይማኖት ማስገደድ የለም!”
የፌስቡክ ወዳጃችን Abubeker Siraj ከዚህ በታች ያለውን ጽሁፍ ከመልዕክት ጋር ልከውልናል፤ ሁሉንም እንዳለ አቅርበነዋል፡፡ ለፌስቡክ ወዳጃችን Abubeker Siraj ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ ሰላም እና በረከት ቅኑን መንገድ በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን ጎልግሎች ሆይ! እኔ አንድ አንባቢያቹ ነኝ ከአዲስ አበባ። ፅሁፎቻቹን አነባለው አደንቃለው። ከምንም በላይ አገር ወዳድነታችሁ እና ሚዛናዊነታችሁን ሳላደንቅ አላልፍም። ዛሬ አንዲት ጉዳይ ላወራቹ ፈልጌ ነበር። እሱም አሁን ከዚህ በታች ያለው ሊንክ ላይ የሚገኘው የወንድሜ ኢብኑ ሙነወር (Ibnu Munewor) ፅሁፍ የሚያጠነጥነው ሰሞኑን አይ ኤስ አይ ኤስ በፈፀመው ዘግናኝ ኢ ሰብአዊ ተግባር ላይ ሲሆን በጥቅሉ እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከዚህ አፀያፊ እና ዘግናኝ ተግባር ፍፁም የፀዳን መሆናችንን እና ከክርስቲያን ወገኖቻችን … [Read more...] about “በሃይማኖት ማስገደድ የለም!”
መፍትሔው የአማራ ተራድኦና የዕርቅ ድርጅት አይደለም
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ! … [Read more...] about መፍትሔው የአማራ ተራድኦና የዕርቅ ድርጅት አይደለም
በአሜሪካ የመሸገው የሳሙኤል ዘሚካኤል ደቀ-መዝሙር
"አሜሪካ ይዞን ከሄደ በኋላ በዋሽንግተን ዲሲ አንድ የገበያ አዳራሽ (ሞል) ውስጥ ጥሎን ጠፋ. . . ፖሊስ ሁለት ግዜ ይዞን ነበር. . . በርሃብ ተቀጣን፣ ርሃብ ጸንቶበት ሆስፒታል የገባም ልጅ አለ። . . . በየሬስቶራንቱ እየዞርን ለምነናል።" ይላል አንድ የ 11 አመት ሕጻን ሳይንቲስት። ሂውስተን ቴክሳስ የሚገኘውን ናሳ የጠፈር ምርምር ተቋም ለመጎብኘት ከአዲስ አበባ ሄደው ነው አስሩ ሕጻናት ዲሲ ላይ የሚሰቃዩት። አስሩን ህጻናት በአንድ መኪና(ትራክ) ውስጥ አጭቆ ነበር ወደ ሞሉ የወሰዳቸው። የያዘው መኪና ከአራት ሰው በላይ መጫን አይችልም። እመንገድ ላይ ፖሊስ እንዳያያቸው "ሁላችሁም ጎንበስ በሉ።" ይላቸው እንደነበርም ህጻናቱ አጫውተውኛል። እነዚህ ሕጻናት ሀገሪቱ የምትመካባቸው የነገ ሳይንቲስቶችዋ ናቸው። ከአጠቃላይ ትምህርት ቤቶች ተወዳድረው ከፍተኛ፤ እጅግ ከፍተኛ ውጤት … [Read more...] about በአሜሪካ የመሸገው የሳሙኤል ዘሚካኤል ደቀ-መዝሙር
What do we owe our patriotic mothers and fathers who saved Ethiopia from Colonial Domination?
* What is left from the Victory of Adowa? Introduction To write an article on such a major issue might seem too late. Many have written over the last three or more weeks in memory of the victory of Adowa. Many have tried not only to show the historical importance of the victory of Adowa, but also its political impacts over the liberation movements during the colonial time. The present political, economic social and cultural crisis of our country, however compels us to remember the victory of … [Read more...] about What do we owe our patriotic mothers and fathers who saved Ethiopia from Colonial Domination?
ወያኔ እና የቅድመ-ምርጫ ግምገማው
ወያኔ የአምስት ዓመቱ "የዕድገት እና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ" እንዲሁም የዐባይ ግድብ ግንባታ እንዳልተሳካለት አመነ፣ በመጭው ምርጫም የሚያሰጋኝ የድርጅትም ሆነ የግለሰብም ተወዳዳዳሪ የለኝም አለ የትግሬ-ወያኔ መራሹ ዘረኛ አገር እና ትውልድ አጥፊ ቡድን፣ መጭው የይስሙላ ምርጫ ሊያስከትል የሚችለውን ሕዝባዊ ቁጣ እና እምቢተኝነት በከፍተኛ ደረጃ በመፍራት፣ ሊነሣ የሚችለውን ሕዝባዊ አመፅ በወያኔ ፍላጎት ሥር ለማዋል እንዲቻል፣ አባላቱን በመከፋፈል፣ ሰሞኑን በከፍተኛ ደረጃ የተያዘ ጥብቅ ሚሥጢራዊ ግምገማ እና ውይይት ማድረጉን የታመኑ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ውስጥ-ዐወቅ የመረጃ ምንጮች አረጋግጠዋል። የሕወሓት/ኢሕአዴግ አባል በሆኑ እና ለወያኔ ታማኝ የሆኑ የየድርጅቶቹ አባሎች ተሣታፊ የሆኑበት ለበርካታ ቀኖች በተከታታይ ግምገማ እና ውይይት የተደረገባቸው … [Read more...] about ወያኔ እና የቅድመ-ምርጫ ግምገማው










