* “አቶ መለስ በጣም ይናፍቁናል” አሸባሪነት በኢትዮጵያ ሊስፋፋ ያልቻለው ሕዝቡ በሙሉ ሰላይ በመሆኑን ዲና ሙፍቲ አስታወቁ፡፡ ከአገር ተሰድደው የሚውጡት አብዛኛዎቹ ገጠሬ ወጣቶች እንደሆኑና ሟቹ መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ህዳሴ አባት በጣም እንደሚናፍቋቸው ተናገሩ፡፡ ቀድሞ በቃል አቀባይነት ሲሰሩ የነበሩት በአሁኑ ወቅት ደግሞ በኬኒያ ተወካይ የሆኑት አቶ ዲና ሙፍቲ ስታንዳርድ ዲጂታል ከተባለ የኬኒያ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ለቀረቡላቸው በርካታ ጥያቄዎች ድርጅታቸውን በመወከል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የአልሸባብና መሰል ታጣቂዎች የአሸባሪነት ተግባር በኢትዮጵያ ለማድረስ ያልቻሉበት ምክንያት ምንድርነው ተብለው ለተጠየቁት ሲመልሱ ሕዝቡ ሰላይ እንዲሆን የሰለጠነ መሆኑን በመጥቀስ ማንኛውንም ተጠርጣሪ ድርጊት ህዝቡ ሲያይ ሪፖርት እንደሚያደር ተናግረዋል፡፡ ሠራዊቱም እስኪበቃው ድረስ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ “ሰላይ” ነው – ዲና ሙፍቲ
News
ምርጫ ቢቀርስ?!
* “በየ5 ዓመቱ ምርጫ እያሉ ህዝብን ከማሰቃየት፣ እንደነ ሰሜን ኮርያ እና ቻይና የአንድ ፓርቲ አገዛዝ ነው ብሎ ማወጁ ይመረጣል” * “ኢህአዴግ ያሸነፈው ወደ ዘረፋ ስለገባ ነው እንጂ ተቃዋሚ ስለተዳከመ አይደለም” * ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች የምርጫ ውጤቱን አንቀበለውም አሉ * ምርጫ ቦርድ የተቃዋሚዎች ውንጀላ መሰረተቢስ ነው ብሏል ባለፈው እሁድ በተከናወነው 5ኛው አገር አቀፍ ምርጫ የተወዳደሩ ዋና ዋናዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣የምርጫውን ፍትሃዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ ግድፈቶችና የህግ ጥሰቶች መፈጸማቸውን ጠቅሰው የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉ አስታወቁ፡፡ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በ442 የምርጫ ክልሎች ኢህአዴግ ሙሉ በሙሉ እንዳሸነፈ መግለጹን ተክትሎ መድረክ፣ ሰማያዊ፣ ኢዴፓና መኢአድ የምርጫውን ውጤት አንቀበለውም ብለዋል፡፡ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግን ተከትሎ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው … [Read more...] about ምርጫ ቢቀርስ?!
ሥልጣን ወደ ህወሃት?!
* “ግምገማ!” የኢህአዴግ ስድብ ሃይማኖት “ምግባረ ብልሹዎች ናችው፤ የሚታፈርባቸው ናቸው። እነሱን ብሆን ራሴን እንዳዋረድኩ ነው የምቆጥረው” ሲሉ የመድረክ ሊቀመንበር በየነ ጴጥሮስ ሃይለማርያምንና “ሌሎችም ቢሆኑ” ሲሉ የገለጹዋቸውን ባለሥልጣናት ምግባር ተቹ። ነጻና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ቢኖር ኢህአዴግ እንደሚሸነፍ ከ፱፭ በመቶ እርግጠኛ መሆናቸውንም አመለከቱ። ተቃዋሚዎችን ሕዝብን ወዳልተፈለግ አቅጣጫ እየመሩ ነው በማለት በመወንጀል የማስጠንቀቂያ መልእክት ያስተላለፉትን አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝን ተከትሎ ቪኦኤ ያነጋገራቸው ዶ/ር በየነ “የሞራል ብቃት የላቸውም” ሲሉ ሃይለማርያምን ክፉኛ ተችተዋቸዋል። “ለፓርላማ” ማብራሪያ ሲሰጡ “አንተ በምትሰጠው ውሳኔ እንገዛለን” በማለት ቃል መግባታቸውን ተከትሎ ሃይለማርያም የሰላ ወቀሳ ደርሶባቸዋል። ባለሙሉ ሥልጣን መሪ ባይሆኑም ኢህአዴግን … [Read more...] about ሥልጣን ወደ ህወሃት?!
በአሜሪካ የንቦች ሞት ቁጥር ጨመረ
በአሜሪካ በብሔራዊ ደረጃ በተደረገ ምርምር የንቦች ቁጥር 40 በመቶ እንደሚቀንስ ተነገረ፡፡ ለንቦቹ መሞት ዋንኛ ምክንያት ንቦቹ በከፍተኛ ሃሳብና ጭንቀት ውስጥ መግባታቸው እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ ሰኞ (ግንቦት 10/ሜይ 18) ዕለት የሜነሶታ የሕዝብ ሬዲዮ (Minnesota Public Radio News) እንደዘገበው በአሜሪካ ውስጥ በአጠቃላይ በተደረገው አዲስ ጥናት 6ሺህ ንብ አርቢዎች መጠይቅ የተደረገላቸው ሲሆን በዚህም መሠረት የሟች ንቦች ቁጥር በተለይ በበጋ ወራት እንደሚጨምር ተገልጾዋል፡፡ በተቃራኒው በክረምት ወራት ቁጥሩ በመጠነኛ ደረጃ እንደሚቀንስ ጥናቱ አመልክቷል፡፡ በአሜሪካ ከሚገኙት ጠቅላይ ግዛቶች በሰሜን በምትገኘው የሜነሶታ ግዛት የሟቾቹ ንቦች ቁጥር ከፍ እንደሚል ዘገባው ጨምሮ አስታውቋል፡፡ በሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪ የሆኑትና ጥናቱን የመሩት ዴኒስ … [Read more...] about በአሜሪካ የንቦች ሞት ቁጥር ጨመረ
መሸነፍን በአሸናፊነት የተቀበሉ መሪዎች
በቅርቡ በሥልጣን ላይ እያሉ በምርጫ መሸነፋቸውን ባመኑበት ጊዜ ሥልጣናቸውን ያስረከቡት የናይጄሪያው ጉድላክ ዮናታን በአፍሪካ የ65 ዓመታት የምርጫ ዴሞክራሲ ጉዞ ከሚጠቀሱ ጥቂቶች መካከል አንዱ ሆነው ሰንብተዋል፡፡ ይህም ተግባራቸው በናይጄሪያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ታላቅ ሥፍራ የሚሰጣቸው የፖለቲካ ሰው አድርጓቸዋል፡፡ በአፍሪካ በተካሄዱ በርካታ ምርጫዎች የሕዝብን ድምጽ በማክበር ሥልጣናቸውን ለተቀናቃኛቸው በማስረከብ የሕዝባቸውን ድምጽ ያከበሩ መሪዎች በጣም ጥቂቶች ናቸው፡፡ ሁሉንም ለአሁኑ ማቅረብ ባንችልም የተወሰኑት ተጠቃሾች እነዚህ ናቸው፡- 1. ኤደን አብዱላ ኦስማን ዳር (ሶማሊያ) - በተለምዶ ኤደን ዳር ተብለው የሚጠሩት እኚህ ፖለቲካኛ የሶማሊያ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ነበሩ፡፡ በሥልጣን በነበሩበት ጊዜ ሶማሊያን እኤአ ከ1960 እስከ 1967 መርተዋል፡፡ (በዚህ ጽሁፍ … [Read more...] about መሸነፍን በአሸናፊነት የተቀበሉ መሪዎች
ምርጫው አዲስ “ጠቅላይ ሚ/ር” አግኝቷል
በሊቢያ ታፍነው የነበሩ ወደ 30 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን በግብጽ ጦር ኃይል ነጻ አውጪነት መለቀቃቸውን የግብጽ መንግሥት አስታወቀ፡፡ የግብጹ ፕሬዚዳንት አልሲሲ የተለቀቁትን ኢትዮጵያውያን አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ በመገኘት አቀባበል አደረጉላቸው፡፡ ኢህአዴግ እንደተለመደው “የተለቀቁት ኢትዮጵውያን መሆናቸውን አጣራለሁ” እንደማይል ተገምቷል፡፡ “ተይዘን የነበረው በሊቢያ የኢሚግሬሽን ባለሥልጣናት ነበር” ከተለቀቁት አንዱ ኢትዮጵያዊ፡፡ በተለያዩ የዓለም መገናኛ ብዙሃን ሐሙስ በተሰራጨው የዜና መረጃ መሠረት በሊቢያ ደርና እና ምስራታ በተባሉ ከተሞች ታፍነው የነበሩ 30 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን በግብጽ ጦር ኃይል እና በሊቢያ ድጋፍ ነጻ መለቀቃቸው ተሰምቷል፡፡ ዜናውን ከካይሮ አውሮፕላን ማረፊያ የግብጽ የዜና አውታሮች በቀጥታ ለአገራቸውና ለዓለም ሕዝብ እንዲሰራጭ አድርገውታል፡፡ … [Read more...] about ምርጫው አዲስ “ጠቅላይ ሚ/ር” አግኝቷል
አልሸባብ አይሲስን ሊቀላቀል ነው
በሶማሊያ የሽብር ተግባራትን በመፈጸም የሚታወቀው አልሸባብ ደመኛና አረመኔውን አይሲስን ሊቀላለቀል መሆኑ ተሰማ፡፡ አገራችንን በተጨማሪ የሽብር ስጋት ውስጥ እነደሚጥላት ተገምቷል፡፡ የሶማሊያን ስፊ ግዛት የሚቆጣጠረው አልሸባብ የማእከላዊ ስልጣኑን ካጣ ወዲህ በደረሰበት ወታደራዊ ኪሳራ የአለም አቀፍ አሸባሪው አልቃይዳ ክንፍ በመሆን እያካሄደ ባለው የደፈጣ ውጊያ ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ርቋት በንጹሃን ደም የታጠበች መንግስት አልባ ጦር ሜዳ ከሆነች ከሁለት ዓስርት አመታት በላይ አስቆጥራለች። ሟቹ አቶ መለስ የቆሰቆሱት የሶማሊያ ችግር እስካሁን አልበረደም፤ የኢትዮጵያን ጦር ጨምሮ ከተለያዩ አፍሪካ ሃገራት የተውጣጡ ወታደሮች የሶማሊያን ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር እያደረጉ ያለው ጥረት መና ቀርቶ የእሳቱ ወላፈን ድንበር ተሻግሮ ለዜጎቻቸው ጦስ እስከ መሆን ርቆ የሄደበት አጋጣሚ የሰላም … [Read more...] about አልሸባብ አይሲስን ሊቀላቀል ነው
ሽብርን በማሸበር!!
* ሕዝብ ዋስትናና መተማመን አጥቷል ረቡዕ ዕለት ኢህአዴግ በጠራው ሰልፍ ዜጎች ስሜታቸውን ሲያንጸባርቁ የተሰጣቸው ምላሽ ሽብርን በአሸባሪነት አመጣጥኖ የመመለስ አይነት እንደሆነ ተጠቆመ፡፡ የሰላማዊ ሰልፉ አጠቃላይ ገጽታና የሕዝብ ስሜት በአገሪቱ የዋስትና ማጣት ስሜት እየገዘፈ መሄዱን የሚያሳይ ሆኗል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ሊታረድ ነው፤ በሰሜን አሜሪካ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ባሉት ይልቃል ላይ እዚያው እንዲቀሩ ተጽዕኖ ይደረጋል ተብሏል፡፡ በአይሲስ የታረዱትና የተረሸኑትን “ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን እያጣራሁ ነኝ” ሲል የነበረው ኢህአዴግ እንዴት እንዳጣራ ለሕዝብ ባያሳውቅም ወዲያው ሕዝባዊ ለመሆን በመመኘት በአገሪቷ ላይ የሐዘን ቀን ከማወጅ በተጨማሪ ሕዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲወጣ ጥሪ አድርጎ ነበር፡፡ አንድ የጎልጉል አስተያየት ሰጪ “ሕዝቡ ለ24 ዓመታት በሐዘን ላይ ነው ሦስት ቀንማ … [Read more...] about ሽብርን በማሸበር!!
ቀላጤ ሬድዋን – ፖሊሶቹ “ኢትዮጵያውያን መሆናቸው” ይጣራልን!
አፈቀላጤ ሬድዋን “ጥቂት” በማለት የጠሯቸው ነገር ግን በዓለምአቀፍ ሚዲያ በብዙ ሺህ ተብሎ የተዘገበው የተቃውሞ ትዕይንት ከቪዲዮ ምስሎች ላይ ያውጣጣነው ፎቶ በዚህ መልኩ አቅርበነዋል፡፡ ቀላጤ ሬድዋን 7ፖሊሶች መደብደባቸውን ሲናገሩ ፖሊሶቹ ስላሸበሩት ሕዝብ ግን ምንም አለማለታቸው “እንዳያስገመግማቸው” ያስፈራል፡፡ ከ“ምርጫው” በኋላ የሚመጣውን የፈሩ ይመስላል ቀላጤ ሬድዋን ኅያዋንን ብቻ ሳይሆን ሰማዕታትንም ዜግነት በመንፈግ ትጋታቸውን ጨምረዋል፡፡ ስለዚህ ደብዳቢ ፖሊሶቹ “ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ያጣሩልን” እንላለን፡፡ ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን … [Read more...] about ቀላጤ ሬድዋን – ፖሊሶቹ “ኢትዮጵያውያን መሆናቸው” ይጣራልን!
“እኛን ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው”
አይሲስ በሊቢያ ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን መያዙን ከአይሲስ ያመለጠው ኢትዮጵያዊ ለቪኦኤ ገለጸ፡፡ እርሱንና ሌሎችን በአይሲስ እንዳይወሰዱ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ማስጣላቸውን ተናገረ፡፡ ይኸው ስሙ እንዳይገለጽ የጠየቀው ወገን እንደተናገረው እኛን ከአይሲሲ ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው፤ በሀገራችን በፍቅር ነው የኖርነው ክርስቲያኖቹን ለይታችሁ አትወስዱም በማለት ሙስሊሞቹ እንደተከራከሩላቸው፤ እንደጮሁላቸው አስረድቷል፡፡ በዚህም ምክንያት እርሱና ሌሎች ላሁኑ ከመሞት ተርፈዋል፤ ከዚህ ወዲህ የሚሆነውን ግን ለመናገር እንደማይችልና ሁሉንም “እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው” በማለት በእምነት እየጠበቁ መሆናቸውን ከተሰወረበት ቦታ ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ ተናግሯል፡፡ ይኸው ከአይሲስ ያመለጠው ኢትዮጵያዊ ከዚህ በፊት ቤንጋዚ ላይ ከሌላ የትግራይ ተወላጅ ጋር ተይዘው በኤሌክትሪክ … [Read more...] about “እኛን ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው”










