ጠንቋይና ፖለቲከኛ የሚያመሳስላቸው አንድ ነገር አለ። ሁለቱም ተገልጋያቸውን ለማምታታት የትኩረት አቅጣጫ ማስቀየርን ተክነውበታል። ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህኛው - የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ - ገለጻቸው ራሳቸውን ሳይቀይሩ ሌላውን ለመቀየር የተነሱ ግብዝ ነው የሆኑት። ይህ "ቃለ-ምልልስም" አንድ አላማ አለው። አላማውን ለማወቅ ቃላቶችን መሰንጠቅም አያስፈልግም። ግልጽ ነው። 'ብዙ ስላልተሰራበት' መልዕክቱ የተጠበቀውን አላማ የመታ አይመስልም። ቃለ-ምልልሱ የተደረገበት ወቅት፣ የተመረጠበት ሰዓት የሚሰጠን ግልጽ የሆነ ግን የተለየ ትርጉም አለ። ጠያቂዎቹ በሻዕቢያ ላይ የነበራቸው የፖለቲካ አቋም ከመቅጽበት መቀየሩ በራሱ የሂደቱን ግራጫ ምስል ያሳየናል። "ሁሉን ቢናገሩ ሆድ ባዶ ይቀራል" ይላሉ አበው። እነዚህ ጉዳዮች ውስጥ ገብቶ መላ-ምቶችን መዘርዘሩ አስፈላጊ ባይሆንም (አንዱ መላ ምት … [Read more...] about ከኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ-ምልልስ በስተጀርባ
Kidane Alemayehu, My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia
The journey which author Ato Kidane Alemayehu chronicles in his new book takes him through Lesotho, Tanzania, Uganda, United Arab Emirates and the Horn of Africa as a representative of the United Nations, and ultimately to establish an organization dedicated to confronting “Fascist Italy and the Vatican.” His book contributes valuable information to the history of East Africa, the United Arab Emirates, and to the rationale behind Ethiopia’s struggle to win recompense from Italy for crimes … [Read more...] about Kidane Alemayehu, My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia
«ችግሩን ለማስወገድ፣ ግለሰብ ወይም ቡድን መወገድ አለበት» ዐባይ ፀሐዬ
የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) አጠቃላይ ግብ፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማጥፋት ነው። የዚህ ግብ መዳረሻ ደግሞ በኢትዮጵያዊነታቸው በጽኑ የሚያምኑ ኢትዮጵያውያን እና ከሁሉም በላይ፣ የዐማራውን ነገድ ማጥፋት ሲቻል እንደሆነ በማመኑ፣ ላለፉት 43 ዓመታት የኢትዮጵያዊነት የወል ዕሴቶችን፣ ነባር ሃይማኖቶችን፣ የአገራዊነት መገለጫ የሆነችውን ሰንደቅ ዓላማችንን፣ በሕዝቡ መሀል የአንድነት መገለጫ የሆኑ ተቋሞችንና አሠራሮችን፣ ግንኙነቶችን በአዋጅ አጥፍቷል። በዐማራው ነገድ ላይ የተቀነባበረ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ፈጽሟል። የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በወያኔ ዘረኛ አገዛዝ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዐማሮች ከምድረ-ገጽ እንዲጠፉ ተደርጓል። የትግሬ-ወያኔ ለዚህ ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና የዐማራውን ነገድ ለማጥፋት ላለመው ዓላማው ወደ ግቡ መዳረስ … [Read more...] about «ችግሩን ለማስወገድ፣ ግለሰብ ወይም ቡድን መወገድ አለበት» ዐባይ ፀሐዬ
ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ የፖለቲካ ትግል፤ ወይንስ የተበታተነ ተቃውሞ?
የያዝነውን እናጢን! ምን እያደረግን ነው? የትግሬዎቹ ገዢ ቡድን በሚያደርገው የዕለት ተዕለት አውዳሚ ተግባሩ በመቆጣት፤ ለተቃውሞ መነሳትና፤ ይህን አካል በተግባሩ ወንጅሎ፤ በደሎቹን መዘርዘሩ አንድ ነገር ነው። ይህ ተቃውሞ ነው። በመቃወምና ይህ መደረግ የለበትም ብሎ በመጮህ፤ የተወሰነ ግብን ማስገኘት ይቻላል። ተግባሩ ግን ይቀጥላል። ቢበዛ ቢበዛ፤ በተግባሩ ሂደት ላይ ትንሽ ማስተካከያ ማስከተል ይቻላል። ከዚያ በተረፈ ግን፤ ይህ በመፈጸም ያለ በደል፤ በድጋሚ እንዳይከሰት የሚያቆመው ነገር የለም። ይሄን በማድረግ የሚረካ ሊኖር ይችላል። እንደገና፤ ይህ ተቃውሞ ነው። በታቃራኒው ደግሞ፤ የተፈጸሙትና በመፈጸም ላይ ያሉት በደሎች፤“መደረግ የለባቸውም!” ብሎ መነሳት ብቻ ሳይሆን፤ “የዚህ ሁሉ ምንጩ፤ አንድ አካል ነው። ይህ አካል መንግሥታዊ ሥልጣኑን ባንድ መንገድ ወይንም በሌላ፤ በጁ … [Read more...] about ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ የፖለቲካ ትግል፤ ወይንስ የተበታተነ ተቃውሞ?
“ኢጂኣኦ” – የቻይናና አህያ ፍቅር – ቻይና በዓመት 4 ሚሊዮን የአህያ ሌጦ ትፈልጋለች
“አህያ ሲጠፋ እህል ማን ሊሸከም ነው? ሴት?!” የአህያ ሥጋና ቆዳ ንግድ እንደ ህገወጡ የአውራሪስ ቀንድ ንግድ እንዳይሆን ተሰግቷል “አህያ ልባችን ነው። አህያ ህልውናችን ነው። አህያ ቤተሰባችን ነው። አህያ ውለታውና ተግባሩ ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም። ገዢዎቻችንም ቢሆኑ የአህያን ጥቅም በአግባቡ ያውቁታል። በበረሃ ሁሉን ችሎ እዚህ ያደረሳቸው አህያ ነው። እናም ጉዳዩ ከወሬ በላይ ነውና በሰከነ መልኩ ለማሰብ ፍላጎቱ ካለ ጊዜው ገናነው” ሲሉ የቱሉ ቦሎው ነዋሪ ይናገራሉ። የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ያናገራቸው የቱሉ ቦሎ ነዋሪ እህል ነጋዴ ናቸው። እንደ ምሳሌ የሚያነሱት ጉዳይ የሚደመደመው በጥያቄ ነው። እንዲህ ይላሉ “አህያ ሲመናመን ከገጠር ማን ተሸክሞ ወደ ገበያ ያመጣ? ያው የፈረደባት ሴት በወገቧ ልትሸከም?” ለወትሮው “ሴት፣ የሴቶች መብት፣ የሴቶች የህግ … [Read more...] about “ኢጂኣኦ” – የቻይናና አህያ ፍቅር – ቻይና በዓመት 4 ሚሊዮን የአህያ ሌጦ ትፈልጋለች
ተራዛሚው የኦሮሚያ ድርቅ እና ያዘለው አደጋ!
በኦሮሚያ በሦስት ዞኖች ብቻ 241 ት/ቤቶች ተዘግተዋል፤ 114,751 ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል! በቦረናና በጉጂ ዞኖች 127,010 ከብቶች በዘንድሮው ድርቅ ሞተዋል! ድርቅ ከፍ ሲልም ችጋርና ረሃብ ለኢትዮጵያ ተጠባቂ የስጋት ምንጭ ሆነው እንደቀጠሉ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ በተለይም ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ካሳለፍነው አስከፊ የርስ በርስ እና ከጐረቤት አገራት ጋር ከተደረጉ ጦርነቶች ጐን ለጐን ድርቅ፣ ችጋር፣ ረሃብ ሌላኛው የኢትዮጵያ አስከፊ የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በቀደሙት ጊዜያት በየአስር ዓመታት ልዩነት ኢትዮጵያን በሰፊው ይጐበኛት የነበረው ድርቅ፤ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት አገሪቱን ደጋግሞ ሲያጠቃና የከፋ ማኅበራዊ ቀውስ ሲያስከትል ታይቷል፡፡ በተራዛሚው ጦርነት ፍፃሜ ማግስት በአገሪቱ የተከሰተው የ1988 ዓም ድርቅ የአማራ፣ የሶማሌ፣ የአፋር እና … [Read more...] about ተራዛሚው የኦሮሚያ ድርቅ እና ያዘለው አደጋ!
በሁዳዴ ጾም የአህያ ልኳንዳ!
አህያን ጅብ ብቻ ሲበላው ነው የምናውቀው! "ደሳለኝ" ተብሎ ስለሚጠራው አህያ፤ በወያኔ ሚዲያ የተተረከልን ታሪክ መሳጭ ነው። እነሱ ጫካ ውስጥ በነበሩበት ወቅት፣ አስገደ ገብረስላሴ በ45 ብር ገዝቶ ለወያኔ ማጓጓዣ ይሆን ዘንድ አበረከተ። ይህ "ደሳለኝ" የሚባለው አህያ ከባድ ጭነት እየተሸከመ ያገለግላቸው ነበር። በአንድ ወቅት በጦርነት ተሸነፉና ይዘውት የነበረውን ስፍራ ለቅቀው ተበታተኑ። ከቀናት በኋላ አንዳንዶቹ ወደቀድሞ ምሽጋቸው ተመልሰው ለመምጣት እንኳን ሲቸገሩ ደሳለኝ ግን መንገዱን ሳይስት እዚያው ስፍራ ይጠብቃቸው ነበር። በመጨረሻም የአህዮች አለቃ ተባለና "ብፃይ" (ጓድ) የሚል የማዕርግ ሹመትን አገኘ። አሁን ደሳለኝ በህይወት የለም። ወያኔዎች ግን በበኩር ልጁ እየተጽናኑ እንደሆነ ይናገራሉ። አባቱ አብሮን ብዙ ተጉዟል ሲሉ፣ "ለልጁ" የጠቅላይ ሚኒስትርነትን ሹመት … [Read more...] about በሁዳዴ ጾም የአህያ ልኳንዳ!
Horrifying Testimony of Torture in TPLF Prison: Ethiopia
Note: Ethiopia is a current non-permanent member of UN security council and a member of UN human rights council VOA Interview: Part-1 (23 March 2017) + Part-2 (25 March 2017): Habtamu Ayalew: Former spokesman of Andenet Party (Ethiopia) VOA Introducer, Alula Kebede: Today’s guest for democracy in action program is Mr. Habtamu Ayalew, former spokesperson of the opposition, Andenet Party (unity party) in Ethiopia. Mr. Habtamu was subjected to two years of imprisonment, waiting for trial after … [Read more...] about Horrifying Testimony of Torture in TPLF Prison: Ethiopia
ከቆሻሻ ኑሮና ሞት ለመላቀቅ ቆሻሻውን ስርዐት ማስወገድ
ነገሩ ሁሉ ከድጡ ወደማጡ በሆነባት ሀገራችን በየጊዜው የሚፈራረቁት ሰቆቃዎች ልብን በሀዘን ካራ ማድማታቸውን እንደቀጠሉ ነው። ባለፈው አንድ ዓመት ብቻ ከደረሱብን መዓቶች ጥቂቱን ብናነሳ፤ በረኃብ አለንጋ እየተገረፉ ደጃፋቸው ላይ ድፍት ብለው የቀሩትን፣ መብታቸውን ለመጠየቅ ሲጮሁ የጥይት ራት የሆኑትን፣ የኢሬቻን በዓል ለማክበር አምረው ደምቀው እንደወጡ ገደል ሰብስቦ ያስቀራቸውን፣ እንዲሁም በቅርቡ በቆሻሻ ናዳ ታፍነው እስከወዲያኛው ያንቀላፉትን ወገኖቻችንን በቁጭትና በመሪር ሀዘን እናስባለን። እነዚህን አደጋዎች ይበልጥ አሳዛኝና አስከፊ የሚያደርጋቸው ደግሞ በሀገሪቱ የተንሰራፉት አምባገነንነት፣ ዘረኝነት፣ ምዝበራ፣ ራስወዳድነትና ግድየለሽነት ውጤት መሆናቸው ነው። በአስራዎች በመቶ እድገት ሽምጥ ስለሚጋልበው ኢኮኖሚዋ ነጋ ጠባ የሚዘመርላት የወያኔዋ ኢትዮጵያ ዘራፊዎቿ ከቪላ ቪላ … [Read more...] about ከቆሻሻ ኑሮና ሞት ለመላቀቅ ቆሻሻውን ስርዐት ማስወገድ
የብአዴን መክዳትና የ“በቀል” ፍርሃት የወለደው “የኢኮኖሚ አብዮት” በኦሮሚያ፤
“ህወሃት የፈጸመው ግፍ በየትኛውም ዘመን የሚረሳ አይሆንም” በህወሃት ገደብ የለሽ የሥልጣን ፍቅርና የቁስ ሰቀቀን ውልቅልቋ እየወጣ ያለችው ኢትዮጵያ ከፍታው ርቋት የቁልቁለቱን ጉዞ ተያይዛዋለች። ለወጣበት ዘውግ ልዕልና የሚተጋው ህወሃት ህግና ሞራል በማይዳኘው ድርጅታዊ ቀኖናው እየተመራ ኢትዮጵያን ማድማቱን ቀጥሎበታል። እስር፣ ቶርቸር፣ ስቃይ፣ ስደት፣ ሞትና የግዞት ኑሮ ከህወሃት ዘውግ ጥላ ውጪ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እድል ፈንታ ሆኗል። ከነዚህ በመከራ ከሚዳክረው የኢትዮጵያ ሕዝብ መካከል አንዱ የኦሮሞ ሕዝብ ነው። እውነታው ግን ሰፊና ለም የሆነ መሬት ላይ የሰፈረው የኦሮሞ ሕዝብ በቁመቱ ልክ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ ሊከበርለት እንዳልቻለ ወራሪው ህወሃት ራሱ ለፖለቲካ ፍጆታም ቢሆን ያመነውና ማንም ሊከደው የማይችል የአደባባይ ሃቅ ነው። በአገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይ … [Read more...] about የብአዴን መክዳትና የ“በቀል” ፍርሃት የወለደው “የኢኮኖሚ አብዮት” በኦሮሚያ፤










