እንዴትሀገር (ህዝብ) ይጥፋ? ያለመተማመን ስለዘራን ዘር እንሰበስባለን የማያልቅ ‘መከር’። ‘’መግዛት’’ እውቀት ሆኖ፣ ገንዘብና ሀይል አቋራጭ ጎዳናው ‘መቦልተክ’ ሆኗል። ሃይማኖት ተንቃ ስትሆን መቀለጃ የእግዚአበሄርም ቃል ሆነ ምነገጃ። ሳይሰሩ ያገኙት ሀብት፣ ክብር - ዝና ያስከብር ጀመረ መናቁ ቀረና። ፈረሀ - እግዚአብሄር ከልባችን ወ’ቶ ህገ - አውሬ ይገዛናል ሰው-ከሰው አባልቶ። ለመሾም - መሸለም፣ መክዳት - መከዳዳት ምግባራችን ሆኗል ዋናው ሀይማኖት። እያለን የሌለን ስለሆን ተመፅዋች መጠሪያችን ሆነ እናንተ ለማኞች። እውነት ተገንዞ ስለተቀበረ ውሸት ገዥ ሆነና ሰው ለ’ሱው አደረ። ፍቅርና ሰላም ፈላጊ ስለአጡ ተባረው ሄደዋል በአገር እንዳይመጡ። በሌሎች ደም - እምባ፣ ንዋይ … [Read more...] about እንዴት ሀገር (ህዝብ) ይጥፋ?
በአሜሪካ የ፳፮ ሕፃናትና መምህራን ግድያና ግንዛቤዬ
የምኖረው አሜሪካ ነው። አርብ ዕለት በከነቲከት ስቴት፣ ኒውታውን በምትባል ከተማ፤ ሳንዲ ሁክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ፤ ፳ የስድስትና የሰባት ዓመት የአንደኛ ክፍል ተማሪ ሕፃናትና ስድስት መምህርቶቻቸው በትምህርት ቤታቸው ተገደሉ። የተገደሉት የእናቱን መሣሪያዎች አንግቶ፤ መጀመሪያ እናቱን ከተኛችበት ገድሎ፣ የትምህርት ቤቱን መጠበቂያ ጥሶ በገባ የሃያ ዓመት ጎረምሣ ደጋግሞ በረፈረፈባቸው ጥይቶች ነበር። አሜሪካ ከላይ እስከ ታች በዚህ ኢሰብዓዊ ተግባር ተርገበገበች። ከዩጋንዳ ለሐዘኑ መልዕክትና ማስታወሻ ተላከ። ከቦዝንያ፣ ከአውስትራሊያ፣ በጠቅላላው ከዓለም ዙሪያ የሀዘን መግለጫዎች ጎረፉ። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት በቦታው በመገኘት የስነ ሥርዓቱ ተካፋይ ሆነው፤ የሀገሪቱን አጠቃላይ የሀዘን ትብብር ለሙታን ወላጆችና ለከተማው ነዋሪዎች አቀረቡ። እኔም የዚሁ ሀገር ነዋሪ ሆኜ ጉዳዩን … [Read more...] about በአሜሪካ የ፳፮ ሕፃናትና መምህራን ግድያና ግንዛቤዬ
ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ መገንባት ጀመረች
በጅቡቲ አዲስ የሚገነባው ወደብ ወጪ በኢትዮጵያ እንደሚሸፈን ተገለጸ። ወደቡ በቀጥታ ከትግራይ ከሚነሳው አዲሱ የባቡር መስመር ጋር እንደሚገናኝም ታውቋል። እያደር ይፋ በመሆን ላይ ያሉት ፕሮጀክቶች አቶ ሃይለማርያም አስመራ ድረስ ለመሄድ ያሳዩትን ፈቃደኛነት “ለኢሳያስ የቀረበ የፖለቲካ አይስክሬም” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተናገሩ፡፡ ባለፈው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የመሰረት ድንጋይ ለማስቀመጥ ጅቡቲ መጓዛቸውን የዘገቡት ያገር ውስጥ መገናኛዎች ያድበሰበሱት ጉዳይ ይፋ የሆነው ዲሰምበር 18/2012 ለአሜሪካ ሬዲዮ መግለጫ የሰጡት በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝና የታሪክ ምሁር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር አየለ በከሬ ናቸው። ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋ እያደገ በመሄዱ ተጨማሪ ወደቦች እንደሚያስፈልጓት የጠቆሙት እኚሁ ምሁር በጅቡቲ የሚሰራው አዲሱ የታጁራ ወደብ … [Read more...] about ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ መገንባት ጀመረች
“እስክንድር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈታ”
አስራ ስድስት የአውሮፓ ፓርላማ አባላት የተፈራረሙበት የተላዘበ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ልከዋል። ደብዳቤው ጋዜጠኛ፣ አሳታሚና ጸሃፊ እስክንድር ነጋ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ባስቸኳይ እንዲፈታ የሚጠይቅም የሚያሳስብም ነው። ደብዳቤውን አስመልክቶ በዓለም ዙሪያ ላሉ የህሊና እስረኞች ጥብቅና የሚቆመው “የፍሪደም ናው” ነገረ ፈጅ ፓትሪክ ግሪፍተዝ ለቪኦኤ እንደተናገሩት እስክንድር ነጋ እንዲፈታ በመጠየቅ የተጀመረው ስራ እስክንድርን በማስፈታት እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፡፡ እስክንድር ነጋ በየትኛውም መስፈርት ከሽብር ጋር የሚያገናኘው ጉዳይ እንደሌለ ማረጋገጣቸውን አስታውቀዋል። ህጉ የጋዜጠኞችን አፍ ለማዘጋት የተፈበረከ መሆኑንም አስታውቀዋል። አስራ ስድስቱ ፈራሚዎች በላኩት ደብዳቤ የእስክንድር ነጋን ቤት ለመውረስ ስለተጀመረው ሩጫ መረጃ እንዳላቸው አስታውሰው … [Read more...] about “እስክንድር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈታ”
MEPs demanded “unconditional release of (Eskinder) Nega”
16 Members of the European Parliament Call for the Release of Imprisoned Ethiopian Journalist Eskinder Nega Washington, D.C.: Today, 16 members of the European Parliament issued a public letter to Ethiopian Prime Minster Hailemariam Desalegn expressing their grave concern regarding the continued detention of imprisoned journalist and blogger Eskinder Nega. Arrested in 2011 and detained without access to an attorney for nearly two months, Mr. Nega was sentenced to 18 years in prison under the … [Read more...] about MEPs demanded “unconditional release of (Eskinder) Nega”
መስፍን ኢንጂነሪንግ 30ሚሊዮን ዶላር አተርፋለሁ አለ
በኤፈርት ስር ከታቀፉት የህወሃት የንግድ ተቋሞች መካከል አንዱ የሆነው መስፍን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪያል በመጪዎቹ ሁለት ዓመታት ሰላሳ ሚሊዮን ዶላር ለማትረፍ እንደሚሰራ አስታወቀ። ለሶስት ስኳር ፋብሪካዎች የአገዳ መቀቀያ ገንዳ (ቦይሊንግ ሃውስ) ለመስራት የሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ስምምነት አደረገ። የአማራ ክልል በብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል ድምቀት ላሳየው “ቁርጠኛነት” ተደነቀ፣ ጣና ሃይቅና አካባቢውን የወረረውን አደገኛ አረም ለማጥፋት የአንድ ለአምስት የጥርነፋ አደረጃጀት ማከናወኑ የአካባቢውን አርሶ አደሮች እንዳስደሰተ ተጠቆመ። ኢቲቪ ትላንት ይፋ እንዳደረገው ከተቋቋመ አስራ ዘጠኝ ዓመት የሞላው መስፍን ኢንጂነሪንግ ከስኳር ፋብሪካዎቹ ጋር የገባውን ውል በአስራ አንድ ወራት ውስጥ ለማስረከብ ሃያ አምስት ቶን ብረት ከውጪ አስገብቷል። ስራውን አስመልክቶ መግለጫ … [Read more...] about መስፍን ኢንጂነሪንግ 30ሚሊዮን ዶላር አተርፋለሁ አለ
ሥጋን ከሚግጡ መቅኒን ወደሚመጡ
ማሳሰቢያ፡- ማንም ይሁን ማን የደም ግፊት ካለበት፣ በቀላሉ የሚናደድ ወይ የሚበሳጭ ከሆነ፣ የኢትዮጵያዊነት ስሜቱ የሚያይልበትና ዘወትር የሚያስጨንቀው ከሆነ… ይህን ጽሑፍ በጭራሽ ባያነብ ይመረጣል፡፡ ይህ መጣጥፍ በተቻለ መጠን ከተሞክሮና ከሕዝባዊ ብሶቶች በመነሣት በስፋት የሚስተዋሉ እውነታዎችን እንዳለ የሚያቀርብ እንጂ በተለመደው የይሉኝታና የመለሳለስ ባህል ተዋዝቶ አንድን ወገን ለማስደሰት ወይ ሌላን ወገን ለማስከፋት ያልታለመበት በመሆኑ አንባቢ ከየትኛውም የስሜት ጫፍ በራቀ ሁኔታ እንዲያነብብ ይመከራል፡፡ መልካም ንባብ! (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ሥጋን ከሚግጡ መቅኒን ወደሚመጡ
It is TIME to sit down and assess what we struggle for
As individuals and being in a group, in any and every step one takes, there is always time to know where one is, where one wants to go to and how one wants to go about to get there. I am going to take this moment in this platform to state my stand on what is going on. As a movement, the Ethiopian political opposition has a few issues it has not sorted out yet. We have to sort these out first before any success is to be counted. The reason for this being many, I will just point out its … [Read more...] about It is TIME to sit down and assess what we struggle for
የጎልጉል ቅምሻ
ካውያ እንደ ስልክ ባለቤቱን በርካታ ሥራዎችን በአንድ ጊዜ መሥራት እንደሚችል በማሳየት ለማስደሰት ቆርጦ የተነሳው ፖላንዳዊው ባል እንዳሰበው አልሆነለትም፡፡ ባለቤቱ ከሥራ ስትመጣ ማከናወን የሚገባውን ሥራዎች በተገቢው ሁኔታ ሳይፈጽም መቅረቱ ሁልጊዜ የሚያሳስበው ባል ቴሌቪዥኑን ለኩሶ ከጎኑ ቢራውን እየተጎነጨ ልብስ መተኮስ ጀመረ፡፡ በመካከል ስልኩ ሲያንቃጭል እጁ ላይ ያለው የጋለ ካውያ ስልክ የመሰለው አባወራ ካውያውን ጆሮው ላይ በመደገን ባደረሰው ጉዳት አሁን በአንድ ጊዜ በርካታ ሥራዎችን ማከናወን በተመለከተ ከሴቶች ይልቅ ወንዶች እጅግ ደካማ እንደሆኑ አስመስክሯል፡፡ ከእንግዲህ ወደቤት ሥራ እንደማይመለስ የተናገረው ባል ጉዳዩ ሲያት ቀላል እንደሚመስል ከዚህ በኋላ ግን ለባለቤቱ ተገቢውን ክብር እየሰጠ አርፎ እንደሚቀመጥ ተናግሯል፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ አራት ጊዜ ቃለመሃላ … [Read more...] about የጎልጉል ቅምሻ
“ከኢትዮጵያ ስለመጣችሁ ታሰራችሁ”
አገር ቤት ያሉትን ወገኖች ለጊዜው መታደግ ካልተቻለ ቢያንስ ከማንም ተጽዕኖ ወጪ በስደት የሚኖሩትን ኢትዮጵያዊያኖች ለመርዳት ለሚቀርብ ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ የሚያሳዝን እንደሆነ አቶ ሳሙኤል አለባቸው በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር ሊቀመንበር ገለጹ። አቶ ኦባንግ ሜቶን ማህበሩ በተለይ መጋበዙን አስታወቁ። ከሚያሳዝን መከራ ተርፈው እስራኤል ከደረሱ በኋላ እስር ቤት እንዲቆዩ የተደረጉት ታዳጊዎች መፈታታቸውን አስመልክቶ መግለጫ ያሰራጩት አቶ ሳሙኤል በተለይ ለጎልጉል እንደተናገሩት “በተለያዩ አገራት መከራ እየተቀበሉ ያሉትን ወገኖች መታደግ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቋማትና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ጠቅሰው፣ በተግባር ግን ይህንን ማየት” እንዳልቻሉ ተናግረዋል። በእስራኤል እየደረሰ ያለውን የወገኖች ስቃይ አስመልክቶ ለቀረበ ጥሪ ምላሽ ለመስጠት … [Read more...] about “ከኢትዮጵያ ስለመጣችሁ ታሰራችሁ”








