• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአሜሪካ የ፳፮ ሕፃናትና መምህራን ግድያና ግንዛቤዬ

December 20, 2012 04:38 am by Editor Leave a Comment

የምኖረው አሜሪካ ነው። አርብ ዕለት በከነቲከት ስቴት፣ ኒውታውን በምትባል ከተማ፤ ሳንዲ ሁክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ፤ ፳ የስድስትና የሰባት ዓመት የአንደኛ ክፍል ተማሪ ሕፃናትና ስድስት መምህርቶቻቸው በትምህርት ቤታቸው ተገደሉ። የተገደሉት የእናቱን መሣሪያዎች አንግቶ፤ መጀመሪያ እናቱን ከተኛችበት ገድሎ፣ የትምህርት ቤቱን መጠበቂያ ጥሶ በገባ የሃያ ዓመት ጎረምሣ ደጋግሞ በረፈረፈባቸው ጥይቶች ነበር። አሜሪካ ከላይ እስከ ታች በዚህ ኢሰብዓዊ ተግባር ተርገበገበች። ከዩጋንዳ ለሐዘኑ መልዕክትና ማስታወሻ ተላከ። ከቦዝንያ፣ ከአውስትራሊያ፣ በጠቅላላው ከዓለም ዙሪያ የሀዘን መግለጫዎች ጎረፉ። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት በቦታው በመገኘት የስነ ሥርዓቱ ተካፋይ ሆነው፤ የሀገሪቱን አጠቃላይ የሀዘን ትብብር ለሙታን ወላጆችና ለከተማው ነዋሪዎች አቀረቡ። እኔም የዚሁ ሀገር ነዋሪ ሆኜ ጉዳዩን በቅርብ ስከታተል፤ ሀዘኑ አጥንቴ ገባ። የሁለት ልጆች አባትም በመሆኔ፤ ውስጤ ተርገበገበ። ሁለተኛዋ ልጄ በሟቾቹ ተመሣሣይ ዕድሜ ያለች በመሆኗ፤ ሀዘኑን አቀረበብኝ። በሀዘኔ መካከል አዕምሮዬ አጥረ ሰፊ ነውና የሀገሬን ድቅድቅ የፖለቲካ ጨለማ ጥሶ መንከራተት ያዘ።

ጎንደር ከተማ መላኩ ተፈራ የጨፈጨፋቸው ለሰላማዊ ሠልፍ የወጡ ወጣቶች፤ ከፊቴ ተደቀኑ። በዓለም የሠራተኞች ቀን መከበሪያ (ሜይ ደይ) ምሽት፤ ፲ ፱ ፻ ፷ ፱ ዓመተ ምህረት አዲስ አበባ ውስጥ፤ በመንግሥቱ ኃይለ ማርያም ትዕዛዝ ሶስት ሽህ ወጣቶች ሲታረዱ ነበርኩና ልቤ ተንሰፈሰፈ። ወያኔ የሕዝቡን ድምፅ ለመቀማት፤ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ፤ በግንቦት ፲ ፭ ቀን ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ ዓመተ ምህረት ማግሥት የገደላቸዉ ፻ ፺ ፪ ወጣቶች አዕምሮን አጣበቡት። አሁን ካጋጠመኝ ሀዘን ጋር ሳመዛዝነው፤ ሁለት የሚዛን ሠፈሮች ጎልተው ወጡ። በኢትዮጵያ፤ በሥልጣን ላይ የሚወጡ፤ ሥልጣናቸውን ለመጠበቅ፤ ያርዳሉ፣ ያስራሉ፣ ያሳድዳሉ፤ እንዳሻቸው ያደርጋሉ። በዚህ ሀገር ደግሞ፤ የሀገሪቱ መሪዎች፤ ሰው ሲሞት፤ የሟቾችን ዕልፈት በመጠቀም፤ ተቀባይነታቸውን ለማሳደግ፤ በቀብራቸው ስነ ሥርዓት በአካል በመገኘት አብረው የሕዝቡን ሀዘን ይካፈላሉ።

ይኼ እንዴት ነው? የኢትዮጵያዊ ሕይወት በሚዛኑ ሲቀመጥ ሚዛኑ ስለሚቀል ነው? ለምን? መላኩ ተፈራ፣ መለሰ ዜናዊ፣ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም የግል ሕይወታቸውን ለማሣመር፤ ለሥልጣን ባላቸው ጥማት፤ “እኔ ብቻ ነኝ ትክክለኛው።” “ለሀገሪቱ እኔ አውቃለሁ።” “የምነግራችሁን ስሙ፤ የማዛችሁን ፊፅሙ።” እያሉ በሽዎች የሚቆጠሩ ሕፃናትን፣ ወጣቶችን፣ በመካከለኛ ዕድሜ ያሉትንና አዛውንትን ማረዳቸው ምን ይባላል? ይህ ከፖለቲካ አመለካከት በላይ ነው። ሌሎችን ገዳዮች ቀርቶ፤ እኔም ሰብዕናዬ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ኢትዮጵያዊ ከመሆኔ በላይ፤ ሰው ነኝ። ሰው በመሆኔም፤ ይህ አሜሪካ ውስጥ፤ በትንሽ ከተማ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የተደረገው አረመኔያዊ ተግባር፤ ዓይኔን በእንባ ልቤን በስስት ሞላው። ይኼ እንዳይደገም እፈልጋለሁ። ከሞላ ጎደል አሜሪካዊያን በሙሉ ይኼ እንዳይደገም ይፈልጋሉ። ከሞላ ጎደል በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች፤ ይኼ እንዳይደገም ይፈልጋሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ የደርግና የወያኔ ዘመን እንዳይደገም እፈልጋለሁ። ወያኔ ግን አሁንም አለ። ግድያውን፣ ማሠሩን፣ ማሳደዱን እየገፋበት ነው። ሰብዕናችንን የምናከብር ሁሉ፤ በቃ ልንል ይገባል። ወያኔ መወገድ አለበት።

ለሥልጣን ጥማት የተደረጉት ጦርነቶች ለምጥ፤ ሀገራችንን አጥለቅልቋታል። ለምጡ እያገረሸ፤ ተጨማሪ በደሎች ተጨማሪ ጦርነችን እያስከተሉ፤ የተከተሉት ጦርነቶች አዳዲስ ጠባሳዎችን እየፈጠሩ፤ ማለቂያ የሌለው እሽክርክሪት ውስጥ ገብተን እየዳከርን ነው። ለትናንቱ ግፍ፤ ዛሬና ነገ በዱቤ ተይዘው፤ አንገታቸውን ሰብረው እዳ ከፋይ ሆነዋል። እስከመቼ?

ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከኋላው ለማሠለፍ፤ ትግራይን የተለየችና ነፃ መዉጣት ያለባት አድርጎ አቀረበ። ለዚህም ይረዳው ዘንድ “እኛ” እና “ሌሎች” የሚል ፈጠረ። እናም “ወርቃሞቹን ትግሬዎች” ለማሰባሰብ፤ ጠላት አዘጋጀ። “አማራ ገዢ በመሆኑ፤ ትግሬዎች ተበደልን” አለ። ስለዚህ “ጠላታችን አማራ ነው” አለ። በገዥዎችና ተገዥዎች መካከል ያለውን በደል ተመርኩዞ የሚነሳውን ትክክለኛ ሕዝባዊ አመፅ፤ ወያኔ ባነገተው አቆማዳ ጠቅልሎ፤ ደደቢት ውስጥ ቀበረው። ይኼ ያልበገራቸው ጥሩ ኢትዮጵያዊያን አሉ። ትግሬ በመሆናቸው ወያኔን ከመደገፍ ይልቅ፤ ኢትዮጵያዊነታቸው ያየለባቸውና የወያኔን ምንነት ከማንም የበለጠ ያወቁ አሉ። አብዛኞቹ ትግሬዎች ግን፤ በአንድ ምክንያት ወይንም በሌላ፤ የወያኔ ሥርዓት ጠበቃ ሆነዋል። በምንም መንገድ ቢሆን ግን፤ ትግሬዎችን ጠቅልሎ ከወያኔ ጉያ መክተት፤ ፀረ አንድነት ነው። በአንፃሩ ልንገነዘበው የሚገባው፤ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ሲዳማ፣ ወይንም ሶማሌ ሆነው፤ ከወያኔ ለሚወረወርላቸው ትራፊ፤ የሀገራቸውን ሕልውና “ገደል ይግባ” ብለው የተሠለፉ ሆድ አደር ወያኔዎች መኖራቸውን ነው።

አንድ ነገር እንደገና በደንብ ግልፅ መሆን አለበት። በኛ ሀገርም ሆነ በሌሎች ሀገሮች፤ በጨቋኝና በተጨቋኞች መካከል ባለው ሀቅ፤ ተፃራሪ የሆኑ አቋሞችን በያዙ ክፍሎች መካከል ትግሎች ተደርገዋል፤ ይደረጋሉም። የመጨረሻው መለከት ሲነፋ፤ ወደ ፊት የሚመለከተው ወገን፤ ወደ ኋላ የሚመለከተውን ወገን አቸንፎ ይወጣል። ለትክክለኛ ፍትኅ፣ ለእውነት፣ ለእኩልነትና ለአንድነት የቆመ ወገን ያቸንፋል። ይህ በያንዳንዱ ዉጊያ የተመዘገበ አይደለም፤ በማጠቃለያው ጦርነት እንጂ። በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ያለው ትግል፤ ወደ ፊት በሚመለከተው የአንድነት ክፍሉና ወደ ኋላ በሚመለከተው ሀገር በታኙ መካከል ነው። ለሥልጣናቸው ሲሉ ሀገሪቱን ለመበታተን የሚያቀነቅኑት ይቸነፋሉ። የወደ ፊቱ የአንድነት ነው።

ታህሣሥ ፲ ቀን ፳ ፻ ፭ ዓመተ ምህረት

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule