ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለመንግሥት ያቀረባቸው ጥያቄዎች አስፈላጊው ምላሽ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ይህ ካልሆነ ግን ከሦስት ወር በኋላ ተቃዉሞውን ከፍ ባለ ደረጃ እንደሚያቀርብ በመጋለፅ ሰልፉን አጠናቋል፡፡ ለተነሱት ጥያቄዎች የተገኘ ምላሽ ባለመኖሩ ፓርቲው ለሕዝብ በገባዉ ቃል መሠረት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ታላቅ የተቃዉም ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሔድ በመወሰን በሕግም ሆነ በሥራ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማጠናቀቅ እለቱን በመጠበቅ ላይ እያለ ምንም አይነት መለዮ ባልለበሱ ግለሰቦች የሚመራ የፖሊስ መለዮ ለባሽ ታጣቂዎች ከሕግ ውጭ ነሐሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ከምሽቱ 12 ሰዓት አካባቢ የፓርቲውን ቢሮ ጥሰው በመግባት ፓርቲው ይጠቀምባቸው የነበሩ የቅስቀሳ ቁሳቁሶችና ሌሎች የፓርቲውን ንብረቶች ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ … [Read more...] about በመንግስታዊ ውንብድና ትግላችን አይገታም!!!!!
ፖለቲካ ሳይንስ ነው ወይ? ፖለቲካ ምሁራዊነት ያስፈልገዋል ወይ?
መግቢያ በዚህ አርዕስት ላይ ለመጻፍ ከአሰብኩ ረዥም ጊዜ ሆነኝ። እንደሚታወቀው አንድ ጥናታዊ ጽሁፍ ለማቅረብ ቀላል አይደለም። የመንፈስ ርጋታን የሚጠይቅ ብቻ ሳይሆን፣ ለአንባቢ የሚቀርበው ጽሁፍ ከርስ በርስ ቅራኔዎች የተላቀቀና አሳማኝ እንዲሆን አድርጎ ለመጻፍና ለማስነበብ ረዥም ጊዜን ይፈጃል። ብዙ ዕውቀትንና ምርምርን ይጠይቃል። ተመራምሮና የተለያዩ አስተሳሰቦችን አወዳድሮና አመዛዝኖ ለአንባቢ አንድ የሚያረካና እንደመመሪያ ጥናት ለማቅረብ ረዥም ጊዜ ብቻ ሳይሆን ቢያንስ የሶስትና የአራት ሰዎችን የስራ ክፍፍል ይጠይቃል። አንድ ሰው ብቻ የሚጽፍ ከሆነ ደግሞ ቢያንስ የሶስት ወር ዝግጅት ማድረግ አለበት። በተጨማሪም በኢንስቲቱሽንና በገንዘብ የሚደገፍ መሆን አለበት። በተለይም ለአገር ዕድገትና ነፃነት ተብሎ የሚጻፍ ጽሁፍና የፖለቲካ ሀተታ በአቦ ሰጡኝ የሚቀርብ ሳይሆን ብዙ ጥንቃቄን … [Read more...] about ፖለቲካ ሳይንስ ነው ወይ? ፖለቲካ ምሁራዊነት ያስፈልገዋል ወይ?
የኢትዮጵያ መንግሥት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ጥቃት አላደረስኩም ሲል ካደ
በሳምንቱ መጨረሻ ላይ 100 የሚጠጉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንደታሰሩና አንዳንዶቹም ክፉኛ እንደተደበደቡ ፓርቲው ገለጸ:: እሁድ ሊካሄድ ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የተዘጋጁ የድምጽ መሣሪያዎች እንደተወሰዱባቸውና ሰልፉም እንዳይካሄድ እንደተደረገ የፓርቲው ሊቀመንበር ይልቃል ጌታቸው አስታውቀዋል:: የመንግሥት መገናኛ ሚ/ር ሽመልስ ከማል ድርጊቱ አልተፈጸመም ሲሉ የካዱ ሲሆን መንገዱ አክራሪነትን ለመቃወም መንግስት ለጠራው ትዕይንተ ሕዝብ አስቀድሞ ተይዞ እንደነበር መንግሥት አስታውቆዋል:: ኢትዮጵያን የሚገዛው ኢህአዴግ የሕዝቡን ህይወት በተመለከተ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርግ ይታወቃል:: ሰማያዊ ፓርቲ በሰኔ ወር የጠራው ህዝባዊ ተቃውሞ በ1997 ከተደረገውና የመቶዎች ህይወት ከቀጠፈው ሰላማዊ ትዕይንተ ሕዝብ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ነበር:: ያለፈው ተቃውሞው የመብት ተሟጋቾችና … [Read more...] about የኢትዮጵያ መንግሥት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ጥቃት አላደረስኩም ሲል ካደ
መልካም ጅምር፡ ተደጋጋሚ ስህተቶች
የአንድነት ፓርቲ አመራር አካላት በፈረንጅ አቆጣጠር ኦገስት 30 ቀን ከሚድያ አካላት ጋር ያደረጉትን የቴሌ ኮንፈረንስ ውይይት በጥሞና ተከታትያለሁ:: መልካም ጅምር ቢሆንም ተደጋጋሚ ስህተቶች ከመፈጸም ግን የተቆጠብን አይመስልም:: በውይይቱ ላይ ብዙ መልካም ነገሮች ቢሰሙም የሚፈጸሙት ስህተቶች ግን ያው የጥንት የጠዋቱ በመሆኑ ውይይቱ ምን ያህል ወደፊት የሚያራምድ መሆኑ መገመት ይከብዳል:: የተንሸራሸሩት ሀሳቦች አዲስ ፈጽሞ የማናውቃቸው አይደሉም:: የተቃዋሚ ኅይሉ ደጋፊዎች ስጋት የታወቁ ናቸው:: ትልቁ ጥያቄ መልስ በአጥጋቢ ደረጃ ያልተገኘለት ተቃዋሚዎች አንድ ላይ መስራት ለምን ይቸግራቸዋል የሚለው ነው? የተቃዋሚ አመራር አካሎችን አብረው እንዲስሩ ደጋፊ አደራ የሚጥልባቸው ወይም ተጽዕኖ የሚያሳድርባቸው መንገዶች ተድበስብሰው በመታለፋቸው ካለፈው አሁን ምን አሻሸላችሁ … [Read more...] about መልካም ጅምር፡ ተደጋጋሚ ስህተቶች
Jailed: top TPLF warlord Woldesilassie’s kingdom of death and deceit crumbles
He was the dead tyrant Meles Zenawi’s alter ego and docile horse for 21 years and the most feared man in the complex TPLF security cluster. He amassed millions through corrupt practices and managed to build his own kingdom in partnership with equally corrupt former first lady Azeb Mesfin and her daughter Semhal Meles, the two queens of his vast empire. The malevolent warlord was well protected by the Zenawi family for 21 years and well placed in the inner circle of the ruling elite where … [Read more...] about Jailed: top TPLF warlord Woldesilassie’s kingdom of death and deceit crumbles
የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ
* አቶ በእግዚአብሔርና አቶ ምሕረተአብ ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው * ሦስት የባለሥልጣኑ ሠራተኞች በነፃ ተሰናበቱ * የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ስምንት የክስ መዝገቦች አቅርቧል የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በከባድ የሙስና ወንጀል ተሳትፎ በጠረጠራቸውና ከሦስት ወራት በላይ በእስር ላይ ባቆያቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞች፣ ነጋዴዎችና ሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም ክስ መመሥረቱን፣ ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም፣ ተጠርጣሪዎቹ መከሰሳቸውን የሚያሳይ ክስ እንዳልደረሳቸውና የሕግ ሥርዓትን ያልተከተለ መሆኑን በመግለጽ ክሱን ተቃወሙ፡፡ የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራውን አጠናቆ ለኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ማስረከቡን፣ ጊዜ ቀጠሮውን ሲከታተል ለነበረው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ … [Read more...] about የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ
ካሩቱሪ በኪሳራ ለ“በቃኝ” እያቅማማ ነው!
የኢትዮጵያን ለም መሬት ከተቀራመቱት ኢንቨስተሮች መካካል አንዱ የሆነው የህንዱ ካሩቱሪ ከኢትዮጵያ ለቅቆ የሚወጣበት ጊዜ መቃረቡን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ክፍሎች ለጎልጉል አስታወቁ። አበዳሪዎችና ባለ አክሲዮኖች ፊታቸውን እንዳዞሩበትም ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪም በእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ባዶ ዋይታ የሚያሰማው ኢህአዴግ የያዘው አዲስ አቋም ድርጅቱንና ከድርጅቱ ጋር የቀረበ ግንኙነት አላቸው የሚባሉትን ሃሳብ ላይ ጥሏል። በምናምንቴ ዋጋ የኢትዮጵያ ድንግል መሬት ባለቤት የሆነው ካሩቱሪ ለጊዜው በገንዘብ ሊተመን የማይችል የተፈጥሮ ደን ሲያወድም የከለከለው አልነበረም። ለጊዜው ማልማት ከሚችለው አቅም በላይ መሬት ወስዶ የተፈጥሮ ደን የጨፈጨፈው ካሩቱሪ ተቃውሞ የገጠመው ገና ከጅምሩ ነበር። በቦታው ሆነው መረጃ ሲያቀብሉ የነበሩ ወገኖችና ለድርጅቱ ቅርብ የሆኑ እንደሚሉት በጋምቤላ መሬት … [Read more...] about ካሩቱሪ በኪሳራ ለ“በቃኝ” እያቅማማ ነው!
የ“አምላካችሁ ባሮች” የሆናችሁ “ሰላማዊ ሰልፈኞች” ቅድሚ የምትሰጡት ለማን ነው?
እርቅን፣ ሰላምን፣ ፍቅርን፣ መቻቻልን ለማውረድ የሃይማኖት አባቶችና ሽማግሌዎች ቁልፍ ሚና አላቸው። በር ዘግተው ይጸልያሉ። ያስታርቃሉ። ይገስጻሉ። ያስጠነቅቃሉ። እንዲህ አይነት ለሌሎች ብርሃን ለመሆን የሚቃጠሉ የሃይማኖት አባቶች ያሏቸው ምንኛ የታደሉ ናቸው? በተቃራኒው የአምላክ ባሪያዎች፣ የየእምነታቸው ባሪያዎች፣ የምዕመናን መንፈስ መጋቢዎችና ጠባቂዎች፣ ወዘተ አደባባይ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚወጡ በይፋ ተነገረን። "በተገንጣይ ነጻ አውጪ" ስም እየተጠራጠረና እየተጸየፈ አገራችንን ከሚመራ ከሃዲ ድርጅት ጎን ለመቆም የሃይማኖት መሪዎች መነሳታቸው ለፈረደባት ኢትዮጵያና ለህዝቧ ከዚህ በላይ ሃፍረት የለም!! ችግሩ በውስጥም በውጭም ያለውን ይመለከታል። ይህንን ስንል ምክንያታችንን ህዝብ ይረዳዋል ብለን እናምናለን። በሰማያዊውም ሆነ በምድራዊው ዓለም “መተፋት” አለ። የሃይማኖት አባቶችና … [Read more...] about የ“አምላካችሁ ባሮች” የሆናችሁ “ሰላማዊ ሰልፈኞች” ቅድሚ የምትሰጡት ለማን ነው?
ህዝበ-ሙስሊሙን ያለአግባብ በስጋት መፈረጅ፤ ማዋከብና መግደል በአፋጣኝ ይቁም!!
የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት አንቀጽ 11 ቁጥር 3 ”መንግስት በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ ሀይማኖትም በመንግስት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ” ይላል፡፡በሀገራችን ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ በወታደራዊው ደርግ እንዲሁም አሁን ስልጣን ላይ ባለው ወያኔን ጨምሮ ሁሉም ሀይማኖቶች ከመንግስት ጣልቃገብነት ነፃ ሆነው አያውቁም። ፍትህ፣ ነጻነት፣ እኩልነት እና አንድነት ለብዙ ሀይማኖቶች መሰረታዊ እሴቶች ናቸው፡፡ እነዚህ እሴቶች ላለፉት 22 ዓመታት በዘረኛው የወያኔ መንግስት እየተሸረሸሩ እና እየተመናመኑ ዛሬ ከነአካቴውም ለመጥፋት ተቃርበዋል፡፡ ስለመሰረታዊ የሰው ልጅ መብት እና ነጻነት እንዳይወራ የወያኔ የጥይት አፈሙዞች በእያንዳንዱ ሰው እና የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ተደቅኗል፡፡የእምነት ቦታዎችንም ሳይቀር በመድፈር ህዝበ-ምዕመኑ የኔ የራሴ የሚለው የአምልኮ ቦታ እና የአምልኮ ስርዓት … [Read more...] about ህዝበ-ሙስሊሙን ያለአግባብ በስጋት መፈረጅ፤ ማዋከብና መግደል በአፋጣኝ ይቁም!!
ተመስገን እላለሁም ፣ አልልምም !
በሰላም አውሎ ላሳደረኝ ፈጣሪ ስተኛም ሆነ ስነሳ " ተመስገን ፈጣሪየ! " የምትለዋን ምስጋና ከማቅረብ ተቆጥቤ አላውቅም ። ቸርነቱ የማያልቅበት ፈጣሪ አምላኬ አጉድሎብኝ አያውቅም! ጤና ስጠኝ ስለው ጤናውን ፣ ጥበብ መላ ላጣሁለት መላ ስጠኝ ስለው መላ ብልሃቱን ፣ ጉልበቴን አበርታው ስለው ብርታቱን ፣ ቅን ልቦና ስጠኝ ስለው ርህራሔውን እና የፈለግኩትን ሁሉ አያጓድልብኝም! እናም ዘወትር ተመስገን እለዋለሁ ! ገና ከአልጋየ ሳልነሳ ከአፊ ውስጥ አንድ ቃል ይመላለሳል ፣ ቃሉ ወደ አረፍተ ነገር ሺር በሎ ተቀየረ ! በጨለማ የማያይ አይኔን ወደ ድቅድቁ ጨለማ የመኝታ ክፍል ጣራ አፍጥጦ በምናብ አነበንበዋለሁ ... በጀርባየ ተኝቸ ወደ ጣራ ካፈጠጥኩበት ወደ ጎን ግልበጥ እልና እጆቸን ጭንቅላቴ ስር ወሸቅ አድርጌ ከአፊ የማወጣውን አረፍተ ነገር ደጋገምኩ " ተመስገን ተመስገን ተመስገን … [Read more...] about ተመስገን እላለሁም ፣ አልልምም !










