• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ላም እሳት ወለደች!

October 18, 2016 03:33 am by Editor Leave a Comment

አጉል ዘመን ገጥሟት በረት ብትከሳ፤
ከብቶች በመዥገሮች አዩ ብዙ አበሳ፡፡
ጡቶቿን አቃጣይ የነበልባል ጥጃ ላም እሳት ወለደች፤
ብ’ተው በማይተዋ ዘልለው ባልጠገቡ ወይፈኖች ነደደች፡፡
የከበረው ባህል ባለጌ ረጋግጦት እንደጨው ቀለለ፤
ወፍ ዘራሾች ነግሠው ባጥለቀለቁት ደም ምድር ተበከለ፡፡

አዎ፣ ላም እሳት ወለደች!
እንደዮዲት ጉዲት እቶኑ የሚፋጅ፤
ዕረፍት በማያ’ቅ ሠይፍ እንደነደርቡሾች እንደግራኝ አህመድ፤
ጭንቅላትን ገምሶ አንገትን ቆራርጦ ዜጎችን የሚያነድ፡፡

“አጥንትና ደሜ ይሄው የናንተው ነው፤
እኔ ከሌለሁኝ እናተም እንዲያው ነው፤
እርቧችሁ ጠግቤ፣ ብድንም ሞታችሁ፤
ማንም ስለሌለ ከኔ ‘ሚለያችሁ፤
እስከመጨረሻው አጅቡኝ ባካችሁ፡፡ ”

እያለ እሳት ጥጃው ሕዝብን ይማጠናል፤
መስሎት የማናውቀው ቁርበት ዘርጉ ይላል፡፡
ክፋትና ተንኮል ተፈጥሮው የሆነ፤
ሕግና ሥርዓትን ባዋጅ ያወደመ፤
የሰው ገላ ችቦ አንድዶ የሞቀ፤
ቆላ ደጋ ሳይል ሰደድ የለቀቀ፤
በገጠር ከተማ ቋያ ያዘነመ፤
ሁሉንም በመዝረፍ ራቁት ያስቀረ፤
መላ ከብትን ሸጦ በረት ያራቆተ፤
በዝረፍ እንዝረፍ የደንቆሮ ስብከት ሞኝን ያጃጃለ፤
ያልበላውን ዕዳ ትውልድ እንዲከፍል ቢል ያስተላለፈ፤
የሶላቶ ውላጅ ምድረ የሹምባሽ ልጅ፤
የባንዳ ጥርቅም የናት አንጀት በጣሽ፤
ላም እሳት ወለደች ታቅፎ የማይሳም ሣጥናኤልን ወራሽ፡፡

አዎ፣ ባንዳ ነገሠና ብዙ ታምር ታዬ፤

ጥላቻ ተዘርቶ ትርምስ በረዬ፤
ፍትህ ዐይኗ ጠፍቶ ዜጋ ተሰቃዬ፡፡
የከርቸሌ በሮች ሌት ተቀን ተከፍተው፤
ፍርድ ተገልብጦ ከሌለው ወዳለው፤
ይሉኝታና ሀፍረት ካድማስ ማዶ ርቀው፤
የ’ውነቱ አንገት ጠፍቶ ማተብ ማስቀመጫው፤
ተኖሮ ተሙቶ  “አለን” እንላለን ላለፍ ላገደመው፡፡

እንጂ፤ ተቸግረን እንጂ እውነት ጠፍታብነ፤
ተሳስረን እንጂ ነው ፍትህ ወድማብነ፡-

ስርቆት ባህል ሆኖ እያስመሰገነ፤
ውሸት ጽድቅ ሆኖ ሃቅ እያስኮነነ፤
ክብር ውርደት ሆኖ ውርደት ሲሆን ክብር፤
መች እናይ ነበረ ፍርድ እየተዛባ ስትፈራርስ ሀገር?

ከደጓ ላም ማኅጸን የተወለደው’ሳት፤
ኦሮሞን ካማራ ትግሬን ከኤርትራ አኙዋኩን ከኑዌር፤
ሊያናቁር ሊያናክስ ሊያደርጋቸው ጠላት፤
ነሰነሰ መርዙን ለሩብ ም’ት ዓመታት፡፡

ስለዚህ ወገኔ ትግራዩ ተነሣ፤
“በቃኝ!” በለውና ባንዴራህን አንሳ፤
ለመብትህ እምቢ በል ትግሉን ተቀላቀል፤
ዮሐንስ ይኩራብህ አሉላም አይፈር፤
የወንድሞችህ ደም ያንተም ደም ነውና፤
በምታውቀው ትግል የአርዮስን አረም ከሥሩ በመንቀል፤
የተሻመንከው ሕዝብ በሃሤት ይፈንድቅ፣ አብሮህ እልል ይበል፡፡

የጋራ ጠላትን በሚጠራርገው የማይቀር ጎርፍ ላይ፤
ምራቅህን ጨምር ታሪክ ተለውጦ እውናዊ ነፃነት በተግባር እንዲታይ፡፡

ትግርኛ ግጥም –  አሰር ኣሉላ ዮሐንስ

ነፃ ትርጉም –  ይነጋል በላቸው (yinegal3@gmail.com)

የግጥሙ ርዕስ  –  ላሕሚ እንታይ ወሊዳ ?

ምንጭ –  ethiomedia.com

ማጠቃለያ

  • የኦሮሞው ደም፣ የአማራው ደም፣ የኮንሶው ደም፣ የጋምቤላው ደም የትግራይ ሕዝብ ደም ነው !
  • ህወሓት ለአሁኒቷ ኢትዮጵያ ችግሮች ተባብሶ መቀጠልና ለውድቀታችን ዋና ተጠያቂ ነው !
  • ህወሓት ሳይውል ሳያድር ከሥልጣን ይወገድ!
  • (ሁሉንም ወገን የሚያሣትፍ) ዴሞክራሲያዊ የሽግግር መንግሥት አሁኑኑ በሀገራችን ይመሥረት!
Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule