• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር የባንክ ሒሳብ ውስጥ የተገኘው 675 ሚሊዮን ዶላር የማን ነው?

August 10, 2015 10:48 am by Editor Leave a Comment

የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ነጂብ ራዛክ የግል የባንክ ሒሳብ ውስጥ 675 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሆኖ ተገኘ፡፡ ይህም ገንዘብ ከየት እንደተገኘ የአገሪቱ የፀረ ሙስና ኮሚሽን በምርመራ እንዲያጣራ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተፅዕኖ እያደረጉ ናቸው፡፡

ኮሚሽኑ ባለፈው ሰኞ እንደገለጸው፣ 675 ሚሊዮን ዶላር ያህል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ የግል ሒሳብ ተዛውሯል፡፡ ይህም ገንዘብ በዕርዳታ የገባ እንጂ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሚመራው የአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድ የወጣ አለመሆኑን አመልክቷል፡፡

በአገሪቱ ውዝግብ ያስነሳውና የጠቅላይ ሚኒስትሩን መንግሥት ያንቀጠቀጠው ይኼ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ፣ በአገሪቱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን በዕርዳታ የመጣ ነው ቢባልም፣ ኮሚሽኑ ዕርዳታውን የሰጠውንም ሆነ በባንክ አካውንቱ ያስቀመጠውን ግለሰብ ወይም አካል አላሳወቀም፡፡ በመሆኑም ኮሚሽኑ ሊያድበሰብስ የፈለገው ጉዳይ አለ ተብሎ እየተጠረጠረ ነው፡፡

የተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆኑ ሕዝቡ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት የገባው ገንዘብ ከማሌዥያ ኢንቨስትመንት ዴቨሎፕመንት ነው በማለት ቢወነጅሉም፣ ከፈንዱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ምንም ገንዘብ ተሰጥቶም ሆነ በአካውንታቸው ገብቶ እንደማያውቅ የፈንዱ ቢሮ አሳውቋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትሩ እ.ኤ.አ. በ2009 የተመሠረተው የማሌዥያ ኢንቨስትመንት ፈንድ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መሽመድመዱንና ወደ 11 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ብድር እንዳለበት ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ግልጽ አሠራር የለውም እየተባለም ይተቻል፡፡

እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2015 መጀመርያ ላይ የዎል ስትሪት ጆርናል ሪፖርት፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ አካውንት ውስጥ 700 ዶላር ገቢ መሆኑን አትቶ ነበር፡፡

ከዚያ ጊዜ ወዲህ ሚኒስትሩ ለአገሪቱ ልማት የሚውለውን ፈንድ ለግል ጥቅም እንዳላዋሉ፣ በስማቸው የተቀበሉት ገንዘብ እንደሌለና ጆርናሉን በስም ማጥፋት ወንጀል እንደሚከሱ ሲናገሩ ከርመዋል፡፡

ውንጀላው ከተሰነዘረባቸው ጀምሮም በጉዳዩ ዙርያ የሚሞግቷቸውን ሁሉ ከሥልጣን ማስወገድ ይዘዋል፡፡ ባለፈው ሳምንትም የአገሪቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሙሃይዲን ያሲን፣ እንዲሁም ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አብዱል ጋኒን ከሥልጣን አስወግደዋል፡፡

በጠያቂነታቸውና ተሟጋችነታቸው የሚታወቁትን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉን ጨምሮ አራት የካቢኒ አባላት ከሥልጣን ማስወገዳቸውን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫም፣ የካቢኒ አባላት በመሉ በአገሪቱ መከፋፈልን ሊያመጣ የሚችልና ከመንግሥት አጀንዳ የተቃረነ ሐሳብ በግልጽ መወያየት እንደማይችሉ አሳውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጋኒ የማሌዥያ ኢንቨስትመንት ዴቨሎፕመንት ፈንድ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት ገብቶ እንደሆነ ከሚያጣራው ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ ከማሌዥያ ማዕከላዊ ባንክ፣ እንዲሁም ከፖሊስ ጋር እየሠሩ ነበር፡፡ ከሥራ ከመታገዳቸው አስቀድሞም በጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት ውስጥ የገባው ገንዘብ ከአገሪቱ ልማት ፈንድ ጋር ግንኙነት እንደነበረው የሚያስረዳ ዶክመንት ደርሷቸው ነበር፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አራት ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ከሥራ ሲያስወግዱ የሁለት መገናኛ ብዙኃንን የሥራ ፈቃድም አግደዋል፡፡

የአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድ ላይ የተሠራ ሽፍጥ አለ በመባሉ ምክንያት፣ ተከትሎ በማሌዥያ ዋና ከተማ ኳላላምፑር ውጥረት ነግሷል፡፡ የታቃውሞ ሠልፍም ተካሂዷል፡፡ ተቃውሞ አድራጊዎችም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሥራ ይልቀቁ ብለው መጠየቃቸውን ዘ ጋርድያን ዘግቧል፡፡

ከተቃውሞ ሰልፍ ጋር በተያያዘ 29 ሰዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ክስ የተመሠረባቸውም በአገሪቱ እስከ 20 ዓመት እስራት በሚያስፈርደው ያልተፈቀደ ተቃውሞ ላይ በመሳተፍ ተብሎ ነው፡፡

በአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድና በጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት ላይ ምርመራ እየተደረገ ቢሆንም፣ የኮሚሽኑ ውጤት ሚስተር ራዛክን ከጥፋተኝነት የሚያድን ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬን ፈጥሯል፡፡

ከምርመራው ጋር ተያይዞ የዴሞክራቲክ አክሽን ፓርቲ አባልና የፓርላማው መሪ ሚስተር ሊም ኪት ሲያንግ፣ የዚህን ድርጊት ውጤት ማሌዥያውያንና የዓለም ሕዝቦች በትኩረት እየተከታተሉት ነው ብለዋል፡፡

‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ የማሌዥያ መሪ ሆነው ለመቆየት ከፈለጉ ከእንዲህ ዓይነቱ ሙስና የፀዱ ለመሆናቸው ማሌዥያውያንን ማሳመን ይጠበቅባቸዋል፤›› ሲሉም ተደምጠዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለግል ጉዳያቸው ምንም ዓይነት ገንዘብ እንዳልወሰዱ ገልጸው፣ ውንጀላው ከሥልጣናቸው እንዲወርዱ ሆን ተብሎ የተጠነሰሰ ሴራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ባለቤታቸው ሮዝማህ ማንሱር በጣም አባካኝና የተደላደለ የቅንጦት ሕይወት የሚወዱ በመሆናቸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ ጋር ተያይዞ ስማቸው እየተብጠለጠለ ነው፡፡

ሒዩማን ራይት ስዎች የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ሐምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. በኳላላምፑር የሚካሄደውን ስብሰባ ለመሳተፍ መምጣታቸውን አስመልክቶ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ ጋር በጉዳዩና በሰብዓዊ መብት ጉዳይ ላይ እንዲነጋገሩ ጥሪ አቅርቧል፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule