• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ

January 22, 2013 06:30 am by Editor 4 Comments

በየከተማው በየገጠሩ

በየጥሻው በየቆንጥሩ

በለጋ ሕይወታችሁ

ገና ፀሐይ ሳትመታችሁ፤

“ነፃነት ነፃነት የምትሹ

ተዋጉለት አትሸሹ።”

እያላችሁ

ቆማችሁ፤

አባራሪ ግንባር

ሆናችሁ

ቀንዲል ብርሃን

ተነስታችሁ፤

ፀሐይዋ በዕርጋታ

በሀገራችን ወጥታ ገብታ፤

ጨለማው ፈርቶ ሸሽቶ

ብርሃን ባገር ሞልቶ

የማይታሰበውና ደረቁ ሀቅ

በውጥረትና በጭንቅ

ሴትና ወንድ ወጣቶች

ሕፃናትና ሽማግሎች፤

የመኖር ሕይወት ትርጉሙን

ለሌሎች ሕይወት መቆምን

አስተምራችሁን ያለፋችሁ

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ።

እሁድ ጥር ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓመተ ምህረት

(ስዕል: የገጣሚው)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 24, 2013 12:56 am at 12:56 am

    —————————–
    የጥቁር ደመና ድሃ ቤት ላይ ከባ
    ከደሰሳው ጎጆ ውስጥ እየፈራ እየተባ
    የጥቁር ዓይን ዳሩ በነጭ ተከቦ
    አይኑን አፍጥጦ ያነባል በደቦ!
    እናንት ህልመኞች እራሳችሁን የሰዋችሁ
    ከቆሙት በታች ቀና ብላችሁ ባያችሁ
    በእርግጥ ይህ ነበርን ራዕያችሁ ?
    ቋሚን ይድላው ብላችሁ መሞታችሁ
    እናንተንስ መሬት ያዛችሁ ተመቻችሁ
    ደግመው አፍርሰው አውጥተው ከጣሏችሁ
    ግፍ ነው ሁለተኛ ሞት መች ደላችሁና ቆማችሁ?
    ክብር ለዜጋው በለው!
    ++++++++++++++++

    Reply
  2. ዱባለ says

    January 24, 2013 08:47 pm at 8:47 pm

    ያሰበው ያለመው በጋርዮሽ መኖር
    የሰው ጸባይን ነው ያልተረዳው ነገር
    መኖር የሚችለው ሌላውን በመቅበር
    የሞተው ይሻላል የሰውን ጉድ ሳያይ
    በቁም ለሞተ ነው የዘላለም ስቃይ::

    Reply
  3. YeKanadaw Kebede says

    February 1, 2013 12:26 am at 12:26 am

    ተው እንጂ ወንድም ዓለም
    ለጀግና አይታዘንም
    በታሪካችን ተዘክሮ
    በወስጣችን ተቀብሮ
    ስለ’ሚኖር ዘ’ላለም
    የጀግና ሞት፤ ሞት አይደለም
    ከትንሽ ውሎ ማነሱን
    ከርካሾች ጋር መርከሱን
    ስልተጠየፈ ነው
    እንደከብት እየተነዳ
    ሰበእናው እየተጎዳ
    አለመኖርን የመረጠው
    እና..ወንድም ዓለሜ..
    የሚታዘነው…..ለኛ ነው
    ተምረን ለደነቆርነው
    እያየን ለታወርነው
    ቃላችንን ለበላነው
    ዕምነታችንን ለረሳነው
    ጓዱና ጓዲትማ…
    ጥፍራቸው በጉጥ ሲነቀል
    ሥጋቸው በዘይት ሲቀቀል
    ወፌ-ይላላ ሲገረፉ
    ባፋቸው ደም እየተፉ
    ለጠላት ደስ እንዳይለው፤ ወኔያቸው ሳይደፈር
    ወደ መቃብር የሄዱት እየዘፈኑ ነበር
    እና…ወንድም ዓለሜ…
    አገራችን ለተወሰደው
    ክብራችን ለተዋረደው
    በቁማችን ለሞትነው
    የሚታዘነው…ለኛ ነው

    Jan.2013

    Reply
  4. እስከመቼ says

    February 2, 2013 12:51 am at 12:51 am

    ጎረበጠኝ አልኩኝ እንጂ
    ቆረቆረኝ ዕረፍት ነሳኝ፣
    አቅሌን ሳበው አልኩኝ እንጂ
    ቀን ተሌሊት ሰላም ነፍጎኝ፤
    ሰንደቃቸውን አወሳለሁ
    እላፊያቸውን አደንቃለሁ፤
    አልኩኝ እንጂ በኩራቴ
    ግብራቸውን ተሸክሜ በደረቴ፤
    ሕይወታቸው በውስጤ አድሮ
    ከኔ ሕይወት ተዳምሮ፤
    ተነስ ብሎ ቆጠቆጠኝ
    አልኩኝ እንጂ ቆረቆረኝ፤
    የምን ማዘን በየት አልፎ?
    ተደማምሮ በጣም ገዝፎ
    ማጣቴነው ተሰልፎ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule