• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ክደራና ክየና

August 21, 2014 02:24 am by Editor 1 Comment

አንድ ብልጣብልጥ ባለተራ ፤ ከያኔ ነኝ የሚል ጽፎ

በእሱ ቤት የማላውቅበት ፤ መከደሩን ለንብ ቀፎ

በየሔደበት ያወራል ፤ ጸሐፊያንን ነቃቅፎ

ጋዜጣ መጽሔት ድረ ገጽ ፤ ወደዛ! እያለ ተጸይፎ

አታንብቡ አትስሟቸው ፤ ብሎ ያርቃል አንባቢ

የጌቶቹ ጉድ እንዳይወጣ ፤ እንዳይገለጥ ሸባቢ

እንዴት ምን ነካህ? ለሚሉት ፤ ተገርመው በጭፍን ትችቱ

ችግር መኖሩ መች ጠፋን  ? ይሄ ሀገር የሚሻው በብርቱ

መፍትሔውን ቢነግሩን ነው ፤ ይላል ልሳኑን አስልቶ

መፍትሔው እንዳልተጻፈ ፤ ከችግሮቹ ጋር ጎልቶ፡፡

ይሄው አይደሉ እነሱ? ማደናቆር መተጣጠፍ

ምን እነግራለሁ ለእናንተ ፤ ታውቋቸው የለ ከወደአፍ?

በዐይን የሚታየው በጉልህ ፤ የሚጨበጠው ተይዞ

ካሳበቃቸው ጭራሽ የለም ፤ በቃ የለማ ማን አዞ?

የማይታየው የሌለው ፤ ምናባዊውን ሕልም እንጀራ

ብሉ ጠጡ ጥገቡ ነው ፤ እንዲሁ በባዶ ጉራ

እንዴ! እንዴት ሆኖ? አትሉም ፤ በቃ ይሄ ነዋ ክደራ፡፡

ግድ የለም ይሁን ወዳጀ ፤ ዐይኔ ዐላየም ካልክ መፍትሔ

ተጽፏል ብለህ ያመንከው ፤ ችግሮች ተብሎ ያ ይሄ

ችግርን ማወቅ መረዳት ፤ ያገር ሀብት ከንቱ የሚያስፈጅ

ግማሽ መፍትሔ ነው እንዲሉ ፤ ምዕራባዊያን ሥልጡን ፈረንጅ

ችግሮችህን መንገሩ ፤ ጸሐፊው ውዱን የሀገር ልጅ

ይገባሀል እንጂ ማመስገን ፤ አደግድገህ በመንሣት እጅ

እኮ በል እንዴት ሆኖ ነው? በአንተ ዝርው አፍ በገፈጅ

የሚነቀፍ የሚኮነነው ፤ መስታውቱ ጉድፍ አስወጋጅ ፡፡

የሌለውን አለ ሳልል ፤ ያለውን ግን አውጥቸ

ከነ መፍትሔ መላውም ፤ ጽፌልሐለው አጥርቸ

እኮ በል ልይህ ስትሔደው ፤ በአልኩህ መንገድ ማምለጫ

መፍትሔም አላልክ መድኃኒት? ከችጋር ግፍ አሳር መውጫ

እኮ በል ልይህ አድርገው? ያው እኮ ነገርኩህ ጩሄ

ግፈኞቹ የተውልህን ፤ የቀረህ ብቸኛ መፍትሔ

ደፋኸውሳ አንገትህን ፤ አሄሄ አሄሄ አሄሄ!

ተነቃቅተናል ወዳጀ ፤ ዝም ብለህ ልቀም ከበርሔ

ቡሌ ፍርፋሪህን ፤ የኩሊነትክን ድርሻ

ምን ማዕረግ አለውና ፤ ከዚህ በላይ የደጅ ውሻ?

ከዚያ ውጭ መፍትሔ ካለህ ፤ የሚሆን ያልተሞከረ

በላ ንገረን እንስማው ? ሳንሔድበት የቀረ፡፡

ግን እባክህን ወዳጀ ፤ የምለምንህ በብዙ

ከያኔ ነኝ አትበለን ፤ ቃናውም የለህ ወዙ

እናት ኪነትን ጠይቄያት ፤ ልጅ እንዳላት ብየ እንዳንተ

ኅሊናውን ለሆድ ሸጦ ፤ ቡሌ የሚለቅም የሳተ

እውነትን የሚረጋግጥ ፤ የግፈኛ አገልጋይ ሎሌ

የሞራል(የቅስም) እሴት የሌለው ፤ የማንም ምናምን ኩሊ

ልጀ አይደለም አላውቀውም ፤ እናቴ አይበለኝ አደራ

አደራ አደራ አደራ ፤ ቁጣየ እጅግ ነው መራራ

የእኔ ልጆቸ የታወቁ ፤ የእውነት ጠበቃ ለሐቅ ያደሩ

ኅሊናቸውን አክባሪ ፤ በሕዝብ በሀገር አይቆምሩ

ከዚህች ፈቀቅ የማይሉ ፤ ሞት እንኳን ቢሆን የማይፈሩ

ግፈኞችን ሳይዋጋ ፤ የሰላ ብዕሩን ወድሮ

መራሩን ዋጋ ሳይከፍል ፤ ለእውነት ሲል ወህኒ ተወርውሮ

ወህኒም ባይወርድ ባይጋዝ ፤ ፊት ሳይነፈግ ተገዳድሮ

የግፉአን ልሳን ሆኖ ፤ ለፍትሕ ለእውነት አብሮ

ይሄን ሳያደርግ ሳይተጋ ፤ መንፈሱን እራሱ ሰብሮ

የጨለማው ዓለም መብራቷ ፤ እንደ ድቅድቅ ጨላማ ጠቁሮ

ህዋሳቱን አደንዝዞ ፤ አእምሮውን አደንቁሮ

የጥፋት ኃይሎች ኃይል ሆኖ ፤ የሕዝብን እውነት ቀብሮ

ድንቄም ከያኔ የእኔም ልጅ ፤ የማን ነው ጭንጋፍ ቀበሮ?

ሕዝብና ሀገርን ከድቶ ፤ የእውነት ቀባሪ መደዴ

ይሄ ከያኔ አይደለም ፤ ነው ለሆዱ ያደረ ነጋዴ

ምንም ነገር እንደማያውቁት ፤ ያለሆዳቸው ምንዳ

ወደ እንስሳነት የተቀየረ ፤ ለምን? እንዴት? አይል ዱዳ

ብላሀለችና እናት ኪነት ፤ ደፍረህ ሳታፍር ሳተፈራ

ገጣሚ ደራሲ ሠዓሊ ፤ ተዋናይ ተጫዋች ዳንኪራ

ኪነት የነፍሴ ጥሪ ፤ ብለህ መስሟ እንዳትጠራ!!!

የፈለገኝ ሊያየኝ የሻ ፤ ምንጊዜን ቢሆን አድራሻየ

ከሕዝብ ከእውነት ጋራ ነው ፤ የእኔ መኖሪያ ቦታየ

የተፈጠርኩበት ዓላማ ፤ ሥራና ተግባር ሞያየ

ቃልኪዳኑን ሲያስርልኝ ፤ የጥበብ አምላክ ጌታየ

ሕይዎትን ቀና ማድረግ ነው ፤ ችግር ግፍ አሳር ታግየ

እንጅ ሕይዎትን ለማምረር ፤ አይደለም ለአውሬ ደልየ

ልብ  ያለው ሁሉ ልብ ይበል ፤ ጽኑ ነውና መሐላየ፡፡

ብላለችና ጥበብ ኪነት ፤ መልእክቱ ይድረስ ለሁሉ

የሳተ ቶሎ ይመለስ ፤ ይቅር ይባላል በደሉ፡፡

ነሐሴ 1 2006 ዓ.ም.

መታሰቢያነቷ ለልማታዊ ……በሚሉ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. speaker says

    August 23, 2014 05:20 pm at 5:20 pm

    I am crying.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule