• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወልቃይትን በኢትዮጵያዊነት መነፅር

August 19, 2016 12:14 am by Editor 4 Comments

ምሁርን መተቸት ይቻላል? ይቻላል እንደምትሉ በማመን መቀጠሌ ነው። አዎ ደሞም የሚቻል ይመስለኛል። በኛ ሀገር ነውር ሆኖ የሚያስቀጣው መንግስትን መተቸት እንጂ በሌላው ማንኛውም ሰው ሃሳብ ላይ ሃሳብ ቢሰጡ ክፋት የለውም። እርግጥ ከፖለቲካ ውጭም ቢሆን መተቻቸት የለመድነው ባህል ስላልሆነ ሲተች የሚወድ ብዙ ሰው የለም። ለነገሩማ የብልሹ ፖለቲካ ባህላችን ምንጭ ይኼው አሳዛኝ ማህበራዊ አስተሳሰባችን አይደል? ብቻ ፕሮፌሰር በክርክር የሚያምኑ በሳል ምሁር እንደሆኑ ስለማምን ያለስጋት በሃሳባቸው ላይ ሃሳብ ልሰነዝር ደፈርኩ።

ፕሮፌሰር፥ወልቃይት የማነው? የማይረባ ጥያቄ፥ በሚል ርእስ በብሎጋቸው ያወጡትን በጎልጉል ድረገፅ ላይ ካነበብኩ በኋላ የሚደገፍም የሚነቀፍም ነጥብ አገኘሁበት። በአንድ በኩል ጥያቄው በዘር ሳይሆን ባገር መነፅር ሊታይ ይገባል። ወልቃይት የትግራይም ያማራም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው ማለት በተለይ የጎሰኝነትን መርዘኛ ፖለቲካ ለምንፀየፍ ሰዎች ምቾት ይሰጣል። ምናልባትም ለ25 አመታት ከዘረኝነት ሸሽቶ ግን ደግሞ የዘረኝነት ጦስ ሰለባ በመሆን ፍዳውን ሲቆጥር የኖረውን ያማራ ህዝብ በቁጭትና በንዴት ዘረኞች ባዘጋጁለት የዘረኝነት ወጥመድ እንዳይገባ ለመከላከል ይጠቅም ይሆናል። እኔም ብሆን ወልቃይትን ሱዳኖች ወሰዱት እስካላሉኝ ድረስ አማራ ሰፈረበትም ትግሬ, ዖሮሞ ያዘውም ጉራጌ አያሳስበኝም።

ወልቃይት በትግራይ አስተዳደር ስር እንዲሆን የተፈለገበት ምክንያት አስተዳደራዊ ሳይሆን ጎሰኝነት መሆኑ ሲታሰብ ግን ወልቃይት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ያማራም ነው ለማለት ያስገድዳል። ዘረኛው መንግስት ወልቃይት ወደትግራይ ቢጠቃለል ላስተዳደር ያመቻል ቢለን ይገባን ነበር። ወልቃይቶች ትግርዎች ናቸው፦ ስለዚህ ወልቃይት የትግራይ ነው ሲል ግን ራሱ በቆረጠው ዱላ ከመከላከል ሌላ አማራጭ የሚኖር አይመስለኝም። ከዚህም ሌላ ክርክሩ ወልቃይት የትግራይ ነው ወይስ የኢትዮጵያ የሚል አይደለም። በተግባር የቀረበው ጥያቄ አካባቢው ያማራ ክልል ነው ወይስ የትግራይ የሚል ነው። ወልቃይት ያማራም የትግሬም ሳይሆን የኢትዮጵያ ነው የሚል ክርክር ማቅረብ ምርጫ ውስጥ የሌለ መልስ ነው። ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ መስጠት ደግሞ ነጥብ ስለማያሰጥ በዚህ ክርክር ላይ ለፕሮፌሰር ነጥብ አልሰጠኋቸውም። እርሳቸውም ቢሆኑ በመምህርነት ዘመናቸው ምርጫው ውስጥ የሌለ መልስ ለሰጠ ተማሪ ነጥብ የሰጡ አይመስለኝምና በዳኝነቴ አይቀየሙም።

በመጨረሻም በወቅቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለሁ ከአቶ መለስ ጋር ያደረጋችሁትን ያማራ አለ የለም ክርክር ሰምቼ በሃሳብቆ ተስማምቼ ነበር። ምክንያቱም በኔም የትውልድ አካባቢ ?አማራ? የሚለው ቃል የሃይማኖት እንጂ የዘር ወይም የጎሳ መጠሪያ ስላልነበረ ነው። ከ25 አመታት በኋላ ግን ሃሳብዎን ያለመለወጥዎን ስረዳ አቶ መለስን አመሰገንሁት። ምክንያቱም እሱ አማራን በፈጠረበት ዘመን አማራ እንደአማራ ያልነበረ ቢሆንም ከ25 አመታት የግፍና ጭፍጨፋ ዘመን በኋላ ግን አማራ ሳይወድ በግዱ የራሱን ማንነት ፈጥሯል። ኢትዮጵያዊነት ብቻውን ከሞት እንዳላዳነው ሲረዳ ለራሱ ተጨማሪ ስም ለማውጣት ተገዷል። እናም ዛሬ አማራ አለ። አማራ ባይኖር ኖሮ አማራ አይሞትም ነበር። በገዢው መንግስት ፊታውራሪነት በየክልሉ ያለቀው ኢትዮጵያዊ ብቻ ሳይሆን አማራም ነበር። እናም አማራ ዛሬ ሲጠሩት ወይ ለማለት ተገዷል። ሌሎች በስሙ እየጠሩ አለህ ሲሉት ለኢትዮጵያ ሲል ብቻ የለሁም ቢል አንድ እግሩን ጅብ እየበላው አጠገቡ የተኛውን ጓደኛውን፥ እባክህ አትንቀሳቀስ፤ ጅብ ታስበላኛለህ፥ ያለውን ፈሪ ያስመስላል። እና ፕሮፌሰር ይቅርታ ያድርጉልኝ እንጂ በጠንካራ ያንድነት ስሜትዎ ባደንቀዎትም በዚህ ክርክር ላይ ግን አላሳመኑኝም። ረጅም እድሜ እመኛለሁ።

ህሩይ ደምሴ

zobar2006@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Endale KETEFO says

    August 20, 2016 01:46 pm at 1:46 pm

    Politely expressed critiques. I like that. This is a good material to teach people how critiques should be forwarded. Critiques should be directed to the idea not the person.

    Reply
  2. rasdejen says

    August 24, 2016 05:33 pm at 5:33 pm

    Heruy, my complements for your careful yet accurate arguments. I believe prof. won’t refuse your point of view. It is not only due to the enforcement of accepting the identity but because TPLF’s sustained goal is to weaken or if possible wipe it out massacre take over its land area and establish a new country, greater Tigray. In that case Wolkait, etc will not be part of Ethiopia.

    Thus, we need to accept the identify at least for 2 strategic overlapping reasons:
    – to hold on our (Ethiopian) resources
    – and to eradicate TPLF.

    Reply
  3. Benyam says

    August 26, 2016 04:48 am at 4:48 am

    Bravoo! I missed such critiques pro. Hope pro. will give you nice replay. In the near we should involved.
    God bless Ethiopia and it’s people.

    Benyam/TX

    Reply
  4. Bereket Tolosa says

    August 28, 2016 10:42 am at 10:42 am

    I think prof mesfin says the quation itself is wrong , we better think about our country border line not intetnal boundaries unforunatly this government did big mistake , thinking ethinically is not big problem for the last century pepoles are moving and mixing themaelves , what is our future pepoles dont have ethink or biher mix of oromo amhara tigray somale and others

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule