• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይብላኝ ወንድሜ፣ ላንተ ይብላኝ!

December 18, 2019 09:41 pm by Editor 1 Comment

(ወለላዬ ከስዊድን)

ስንቱን ጉድ ይኾን የምታልፈው? ስንቱ ጉድ ይኾን የሚያልፍህ?
ለተነሳህበት ዓላማ፣ ለአንድነት፣ ለመደመር፣ ለብልጽግና የሰላም ጉዞህ።
ስንት ውትብትብ ይኾን የምትፈታው
ተናግረህ ምታሳምን – ተሻግረህ ምታሻግረው
እየሠራህ ላለኸው ላንተ ይቅርና ለእኔ ደከመኝ ያንተ ጣር፣
እንዴት ይኾን? የአንድ ቀን ውሎህ? እንዴት ይኾን? የአንድ ቀንህ አዳር
ለዘመናት የተቆለለ የአገር ጉድ አንተ ላይ ወድቆ ተከምሮ
ውሎ ሲያድር ሸክምህን እየጨመረው ከሮ
አላሠራ ቢልህም አላረፍክ – ይኸው ሥራህ ጎልቶ ወጣ
አዳዲስ ነገር ይዞ ነፍሰ ሥጋ ጨብጦ መጣ
ግን ይብላኝልህ ወንድሜ አይችሉ መቻል ለወደቀብህ
ሐሜት፣ ጥርጣሬ፣ ተንኮል፣ ምቀኝነት፣ ክዳትና መሰሪነት ላከሰለህ
እኔማ ምን ልረዳህ ከመብሰልሰል ከማሰብ በላይ አቅም የለኝ
ስደት አርቆ ያሰረኝ
ሐሳብ አመንምኖ ያኖረኝ
አንድ ብኩን አልሞት ባይ ነኝ።
አሁንማ ተስፋ ቆረጥኩ
በጽሞና ልኖር አሰብኩ
ፖለቲካው ተምታታብኝ
አካሔዱ ጠጠረብኝ
የሰው ሥራው ራቀብኝ
አመስግኘው ጨርሼ፣ አድሬ ሳልመጣ
ቃሌ በክህደት ቀርሽቶ ምርቃቴ እፌቴ ሲገረጣ
ስንት ግዜ አየሁ ስንት ግዜ ትዝብት ዋጠኝ
ስንት ጊዜ አሳቀቀኝ ስንት ግዜ አሳፈረኝ
ወንድምዬ ይብላኝ ላንተ፣ ላንተ ይብላኝ
እንደው ግን ለነገሩ የሰው ልጅ እንዲህ ነው ወይ ለካ
ሥልጣን የማይበቃው በተደረገለት የማይረካ
በቀለለለት ቁጥር ተጨመረብኝ ብሎ የሚያማርር
መሪውን በቁልቢጥ የሚሰፍር
ወንድሙን ለዕለት ውሎ የሚገድል
እንዲህ ነው እንዴ የኢትዮጵያዊነት የማስተሳሰሪያው ውል
ይኼን ነው እንዴ ከዘር ግንዱ የወረሰው
ይኼን ነው እንዴ ዓይቶ ሰምቶ ያደገው
ይሄን ሳስብ ያንተ ብርታት ሁሉን አስንቆኝ
እንደገና ነፍስ ዘርቶ አስነስቶኝ
ተስፋ ሠጥቶ ያውለኛል
ያንተ ነገር ግን ያሳሳኛል
የጉድ አገር ገንፎ እያደር ይፋጃል እንዲሉ
የኛም ጣጣ በረደ ስንል መጋሉ
ያሳስበኛል ላንተና ለአገር
ውጥንህ ተበላሽቶ መና ሆኖ እንዳይቀር
ይኼው ኢትዮጵያን ከዳበስካት ከመጣህላት ጀምሮ
እውነትና ውሸት ተስፋና ፍርሃት – አንድ ላይ ተከምሮ
በአስመሳዩ አዋሻኪው አሾክሻኪው
በአውደልዳዩ አጎብዳጁ ወሬ ነፊው
በሥልጣን ጥም በናወዘው
የዘር ልክፍት ባሳበደው
አገር እየተናጠች እየተላጋች ብታድርም
ያንተ ሥራ አልነጠፈም
ቀን በቀን እየተቃጠልክ እየከሰልክ
ስንቱን ፈውሰህ ስንቱን አዳንክ
ስንቱን ለምነህ እርቅ አወረድክ
ስንት ከቤቱ አግብተህ አሳደርክ
ያም ሆኖ ይብላኝልህ ላንተ፣ ነጋ ስትል ለሚጋርድህ ጭለማ
አለኝ ያልከው ለሚርቅህ ለሚጠነሰስብህ አድማ
ግን ማን ይመንህ በእጅህ ሰይፍ ሳትጨብጥ – ግዳይ ጥለህ ሳታቅራራ
አገር የለመደበትን አስጥተህ መች እሺ ይልሃል ስለ ፍቅር ብታወራ
ሰላም ፍቅርና ተስፋ፣ ለካ አያምርብንም ጃን
ይኼው ደም የለመደው እጃችን
እያጋደለ፣ እያጫረሰ ያውለናል
መተማመንና አንድነትን ነስቶናል
ያንተም እድልህ አልቀና አለ፣ መከራው ችግሩ እያደር ባሰ
ለሰላም ያልከው ለጥላቻ፣ ለፍቅር ያልከው ለጸብ ተነሳሳ፣
እርስ በእርስ ተጫረሰ
ከጎሬው ወጥቶ ስንቱ ደነፋ ስንቱ ዱላ ቀሰረ
ስንቱ በጠራራ ፀሐይ አበደ ስንቱ ቀን ለቀን ሰከረ
ስንቱ በተኛበት ተገደለ
ስንቱ ከኖረበት ተፈናቀለ
ይኼን ሁሉ መከራ እላይህ ላይ ተሸክመህ
ያላሰብከው ተፈጽሞ ሆኖ እያየህ
እንዴት ይኾን ውሎህ፣ እንዴት ይኾን እኮ አዳርህ
መቼ ይኾን ባፍህ ‘ሚዞር የለት ጉርስህ
ወንድምዬ! ይብላኝ ላንተ ይብላኝልህ
ሐውልት ብታቆም መርገምት፣
አንድነት ብትፈጥር ውግዘት፣
አገር ብታጸዳ ሹፈት፣
እርቅ ብታወርድ ቅጥፈት፣
ሆኖ ሲወራብህ መልኩን ለውጦ ሲቀርብልህ
ወንድምዬ ምን ተሰማህ?
የዘመናትን ግፍና በደል
በአንድ ግዜ ነቃቅለህ ለመጣል
አገር እንድታድግ ነፃነት ከአጥናፍ አጥናፍ እንድታበራ
ሕዝብ በአንድነት ተደምሮ እንዲሠራ
ያ’ረከውን ምንም እኛ ባንመሰክር ባናወራ
ከአገር አልፎ ዓለም ሰምቶት
ጥበብህን አውቆ አድንቆት
ስምህን ከአድማስ አድማስ እየጠራ አጉልቶ እያየህ
ከትልልቆቹ ተርታ አሰልፎ ሽልማት አሸከመህ
ያም ሆኖ ወንድምዬ ስንት ይኾን ገና የሚቀርህ
ለተነሳህበት ዓላማ የከፈልከው ገና ደግሞ ‘ሚያስከፍልህ
ብዬ እያሰብኩ የአገሬና ያንተ ነገር የሚጨንቀኝ
አንድ አንተኑ የምከተል ሥራህ ጉዞህ የሚገባኝ
ከሩቅ ኾኜ የምታዘብ ስደት ውጪ የጠፈረኝ
ለፍቶ ሠሪ ማስኖ አዳሪ የአገር ልጅ ነኝ
አንተ ግና የስንቱ ዐመል የጠበሰህ፣ ሸክሙ ከብዶ የተጫነህ
ትልቅ ሐሳብ እቅድ ያለህ የአገር ጉዳይ የሚያበርህ
ወጀብ ጎርፉ የሚንጥህ፣ ወዲያ ወዲህ የሚያላጋህ
ብዙ ገና ገና ብዙ የሚቀርህ፣
እረፍት የለሽ ውድ ወንድሜ፣ ይብላኝ ላንተ ይብላኝልህ!

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Akalu Tadesse says

    December 27, 2019 11:19 pm at 11:19 pm

    Thank you for speaking out my feelings about the very challenging and demanding environment in which Dr. Abiy is leaving each second. We need to pray to god to give him energy , patience and moreover guide him more. Thank you again Wolelaye. I always liked your poems.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule