• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኔ ምን አገባኝ?

October 15, 2012 10:46 pm by Editor 10 Comments

እኔ ምን አገባኝ

እኔ ምን አገባኝ የምትሉት ሐረግ

እሱ ነው ሀገሬን ያረዳት እንደ በግ

የሚል ግጥም ልጽፍ

ስሜት አንዘርዝሮኝ ብድግ አልኩኝና

ምን አገባኝ ብየ ቁጭ አልኩ እንደገና::

ግጥሙ የተወሰደው ከኑረዲን ዒሳ ፌስቡክ ነው:: ባለፈው ሌባዬ በሚል ርዕስ ላወጣነው የግጥም ጨዋታ የተሳተፋችሁትን ሁሉ በተለይ ደግሞ Tsinat ፣ Gedion Adenew እና አበበ አዲስ ከልብ እናመሰግናለን:: እስቲ ለዚህኛውም አንድ ሁለት ሁላችንም እንበል!! እንደበፊቱ ሁሉ ምላሹ በግጥም ቢሆን ጨዋታዋን ሞቅ ያደርገዋል::

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. dawit says

    October 16, 2012 12:01 am at 12:01 am

    ጎልጉሎች ቀስ በቀስ የወግ ገበታ ጀመራችሁ እኮ!! ድንቅ ጦማር ናት። ግን ለምን ይዘገያል። ለምን ታሳንሱታላችሁ?

    Reply
    • Editor says

      October 16, 2012 01:41 am at 1:41 am

      ሰላም dawit
      ለመልካሙ አስተያየትዎ ከፍ ያለ ምስጋና እናቀርባለን:: በምክርዎ መሠረት ላለመዘግየት እንሞክራለን::ማነሱን በተመለከተ ምናልባት እንዲናፈቅና እንዲጣፍጥ ብለን ይሆን? 🙂

      አርታኢ/Editor
      ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ/Golgul: the Internet Newspaper
      http://www.goolgule.com
      editor@goolgule.com

      Reply
  2. Tsinat says

    October 16, 2012 12:19 am at 12:19 am

    ግጥሙን እንዳነበብኩ ብእሬን ብድግ አረግኩ
    ስላገር ልነግሮት ልሞግቶት ወሰንኩ
    ግና ምን ያደርጋል አንድ ሃረግ እንደጨረስኩ
    ምን አገባኝ ብዬ እኔም ብእሬን መለስኩ::

    Reply
  3. ሰማኸኝ says

    October 16, 2012 11:10 am at 11:10 am

    በግጥም ጨዋታው ልሳተፍ አልኩና
    ለጨዋታው የሚሆን ስንኞች ቋጥሬ
    ፖስት ላደርግ ብዬ …
    …አንድ ጊዜ …
    … ሞክሬ
    እምቢ ሲለኝ ጊዜ…
    ሃሳቤን ቀይሬ…
    … ምን አገባኝ ብዬ
    ተውኩት እንደገና::

    Reply
  4. yeKanadaw kebede says

    October 16, 2012 07:08 pm at 7:08 pm

    ምን አገባኝ ብለህ የተውከው ቁም-ነገር
    ዉሎ-አድሮ፤ ጎልብቶ መመለሱ ላይቀር
    እረፍት የሚሰጥህ ብትጨርሰው ነበር

    Reply
  5. Gedeon says

    October 16, 2012 10:03 pm at 10:03 pm

    ድፍን አገር ወገን — ‘ምን አገባኝ’ ገብቶት
    ወኔውን ተሰልቦ — ‘ነግ-በኔ’ ን ረስቶት

    ‘ምን አገባኝ?!’ ያለው ‘ያገባው ምን’ ጠፍቶት

    ድህነት ተላምዶ — ጠኔን ቀልዶበት
    በ ሰማኒያ ቆርቦ — ስንፍናን ተጋብቶት
    ‘ምን አገባኝ?!’ ይላል ትዳሩን ረስቶት!

    Reply
  6. dawit says

    October 17, 2012 02:16 am at 2:16 am

    ምን አገባኝ ማለት – ትርጉሙ ምንድነው?
    ለ-ኔ እንደመሰለኝ – ስያሜና ፍቺው
    ምን አገባኝ ማለት የሞት ሁሉ ሞት ነው፤
    ከመሞት መሰንበት ይሻላል ያላችሁ
    ቁሙበት ላዩ ላይ ምን አገባኝን ቀብራችሁ፤

    Reply
  7. yeKanadaw kebede says

    October 17, 2012 10:54 pm at 10:54 pm

    የፉክክር ደጃፍ ሳይዘጋ ቀርቶ
    አውሬውም ሌባውም ይገባል ተዝናንቶ
    ምን አገባኝ ያለው የቤቱ ባለቤት
    ‘ጠጋ በል‘ ተብሎ ይወጣል በመስኮት

    Reply
  8. inkopa says

    October 22, 2012 07:29 pm at 7:29 pm

    “ምን አገባኝ” ብለው
    የዘጉበትን ቤት
    ያገኙታል ኋላ
    ያገባው ገብቶበት!

    Reply
  9. በለው ! says

    December 30, 2012 06:08 pm at 6:08 pm

    እኔ ምን አገባኝ ?
    “እኔ ምን ቸገረኝ
    ፀሐይ ብትወጣ ባትወጣ
    ታበራልኛለች የ—መላጣ”
    በሀገር ብቻ አደለም ሲቀለድ በፀሐይ
    ሁሉን በእየፊናው ችላ ማለቱን ሳይ
    ተጠያቂው ማነው? እየተብከነከንኩ
    ስሜቴ ቢነካም ኮራሁ ንፁህ እንደሆንኩ
    ውጪ ወጣሁና አልኩ ምን አስገባኝ
    ፈገግ አልኩ እጄን ኪሴ ከተትኩ
    ለሀገሬ መታረድ ቢላዋ አልሳልኩኝ
    ኑረዲን ዒሳ አንድ ዜጋ ነው አልኩኝ !!
    ^^^^^^^^^^^^^^^^^
    በለው! ከሀገረ ካናዳ በቸር ይግጠመን

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule