• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እኛ”!! እናንተ እነማን ናችሁ? ደረጃ ምደባ!!

November 7, 2014 10:09 pm by Editor 1 Comment

ደረጃ ምደባ ለሸቀጥ ወይም ለአንድ ምርት የሚወጣ ማነጻጸሪያ፣ መለያ፣ መተመኛ፣ የጥራት መጠን መለኪያ … ነው። የደረጃ ምደባ ሲከናወን እንደ አቅሚቲም ቢሆን አስፈላጊ የሚባሉ የመመርመሪያ መሳሪያዎች፣ ቤተ መመርመሪያ፣ መርማሪ ባለሙያና ተመርማሪው ሸቀጥ አስፈላጊ ናቸው። የወጉ አሰራር ካለ ማለት ነው።

“እኛ” ሲባል ባጭሩ ከአንድ በላይ ማለት ነው። በሌላ አነጋገር አንድ ብቻውን “እኛ” ሊባልም ሆነ እኛ ብሎ ራሱን ሊጠራ አይቻለውም። ስለዚህ “እኛ” የወል፣ የስብስብ ወይም የጋራነት መለያ ከሆነ፣ አንድ ሆኖ “እኛ” የሚል ተቀባይነት የለውም። አሁንም ባጭሩ የከሸፈ አስተሳሰብ ነው። የከሸፈ ብቻ ሳይሆን የሚያከሽፍም ነው። በነጠላነት ውስጥ ያለው “እኛ” ነት በርካቶችን አክሽፏል፤ አሸማቋል። አሁን ባለው አያያዝ ጉዳቱ ወደ “ውድቀት ህዳሴ” እያንደረደረ ነው። ግን ፍሬን ሊያዝበትና እንድርድሩ ሊገታ ይችላል።

ኢህአዴግ የሚባለው አገዛዝ፣ አብዛኞች ተቃዋሚዎች “መንግሥት” እያሉ የሚጠሩት፣ እኔ ያላቀድኩት፣ እኔ ያልተለምኩት፣ እኔ ያላወጅኩት ሁሉ “ቀሳፊ ተስቦ ነው” በሚል መስማት ከተሳነው 23 ዓመት ሆኖታል። ጆሮው ስለተዘጋና ልቡናው “ያለ እኔ” በሚል የእብሪት ስብ ስለተደፈነ “ወደብ ያስፈልግሃል” እንኳን ሲባል ላለመስማት ደንቁሮ ነበር። ዛሬ ወደብ ላላቸው አገር ጥሪት እያባከነና ሰግዶ እያሰገደን ያለው ኢህአዴግ እሱ ያላለማው ልማት ውድመት ነው። እሱ ያልተዋጋው ጦርነት ሁሉ ጭፍጨፋ ነው። እሱ ያላቦካው ዳቦና እንጀራ አይሆንም። እሱ እውቅና ያልሰጠው ህዝብ ህዝብ አይደለም። እሱ ያልባረከው ሚዲያ ጸረ ህዝብ ነው። እሱ ያላካለለው ወሰን የአድሃሪያን ትምክህት ነው። ይህ ለእርሱና ለሚያሳድራቸው ቢሆን አይገርምም። የሚያስገርመውና የሚያሳዝነው እሱ የሁሉም ነገር አባት፣ መሪና ፈጣሪ መሆኑንን የመቃወም የልዩነት ተፈጥሮ መብት እንኳን አይፈቅድም። የሚቃወሙት ሁሉ አሸባሪ እንዲባሉ በዲዳው ሸንጎ ማስወሰኑ ሌላው ቅሌት ነው። ግብዓት በሌለበት ደረጃ ምደባ!! ክሽፈት ማለት ይህ ነው።

በተቃዋሚ ሰፈርም ተመሳሳይነት አለ። ያገር ቤቱን እንኳ ብንተወው ነጻነት አለበት በሚባልበት አገር ያለው ሚዲያ መረጃ ለማሰራጨት የሚደረገው ጥረት የሚበረታታና ድጋፍ የሚያሻው ቢሆንም የሚጠበቅበትን እየሰራ ነው ለማለት አይቻልም። እኛን ጨምሮ። ተሸብበናል፤ ፈርተናል። በርካታ የሚያነጋግሩና ህዝብ በነጻነት የሚወያይባቸው ጉዳዮች እያሉ ቀድቶ በመለጠፍ (ኮፒ/ፔስት) ሥራ ተወጥረናል፤ ይህ ለሰው ሥራ ዕውቅና ሳይሰጡ የሚፈጸም ተግባር ሙያዊ ጋዜጠኝነት ሳይሆን “የዘረፋ ጋዜጠኛነት” ነው። ከመርህ አንጻር መደገፍና፣ ለሚደግፉት ሃሳብ ልዩ ትኩረት መስጠት አግባብ ቢሆንም ብዙም የተኬደበት ግን አይደለም። በግል የጎልጉል ድረገጽ ጋዜጣ በመርህ ደረጃ ከሚያራምደው ዓላማ አንጻር በተደጋጋሚ ወቀሳ ደርሶብናል። ይህ የተደረገው በግልጽ ዓላማችንን በማስቀደማችን ለማስጠንቅቅም ጭምር ነው።

ወቀሳዎቹ ከላይ እንዳልነው “እኛ” ሲሉ የዲያስፖራውን ማህበረሰብ የመወከል ስልጣን ለራሳቸው የሰጡ የሚሰነዝሩት ነው። እንደ ኢህአዴግ “ዲዳው ሸንጎ” በስብሰባ ያስወስኑት መቼና የት እንደሆነ በግልጽ ባይታወቅም “እኛ የዲያስፖራው ማኅበረሰብ” በሚል የማግለል አሠራር ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ቅልጥ ያለ ወያኔ ተደርጎ ተወስዷል። ፍትህን ለሚያጎናጽፍ የእርቅ ሃሳብና እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉና በይፋ ድጋፍ መስጠታችን “የወያኔን እድሜ አራዛሚዎች” በሚል እንድንዘለፍ አድርጎናል።

ከመርሃችን አፋፍ ላይ ቆመን ለምናወጣቸው ዘገባዎችም ሆነ በስማቸው ባደባባይ አስተያየት የሚልኩልንን ስናስተናግድ ሃሳቡ ላይ “እኛ” ሳይባል “እኔ እንደሚመስለኝ” በማለት መሟገት ሲቻል፣ ባልተሰጠ ማንነት “እኛ … ዘራፍ” ማለት ዋጋው አይገባንም። ሰዎች ሃሳባቸውን “እኔ” እያሉ ሲገልጹ፣ “እኛ” በማለት መመለስ ለማስፈራራት የሚደረግ ከንቱ ሙከራ ሆኖ ይሰማናል። “እኛ የዲያስፖራው ማህበረሰብ” በማለት በህግም ይሁን ባገር ሽማግሌዎች ባልተሰጠ ሹመት አንድ ሰው ራሱን በራሱ ሹመኛ አድርጎ የአዋጅ ይዘት ያለው አስተያየት ሲሰጥ ያመናል፤ ይዘገንነናል። “እኛ” ሲባል በ“እኛ” ውስጥ ያልተቆጠሩትስ? ለምሳሌ እኛ ራሳችንስ? በዚሁ በፍርሃቻ ተሸብበው እንደ ከሸፈ ባሩድ ያደፈጡት አብዛኞችስ? ብዙ ብዙ … ዎችስ?!!!

ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ማንም ለማንም የሚለግሰው “ቦነስ” ወይም ገድቦ የሚሰጠው አይደለም። ሃሳባችንን አራግፈውና አብጠርጥረው ለሚተቹን፣ ለሚወቅሱን፣ ለሚያስተምሩን … ወዘተ ሁልጊዜም በራችን ክፍት ነው። የሳይበር ሚዲያውን የተቀላቀልነውም ለዚሁ ነው። በጨዋነት ሃሳብ ላይ መከሳከስ ይቻላል ስንል ባልተሰጠ ውክልና “እኛ” በማለት ደረጃ የመመደብ ሃላፊነትን ተላብሰው “ሊሰፍሩን” የሚፈልጉትን ግን “ኦ! ኦ! ወራጅ አለ እንላለን”። ምክንያቱም አካሄዱ የመናገር፣ ሃሳብን የመግለጽ፣ … ብቻ ሳይሆን የማሰብን ነጻነት ይጋፋል፡፡ ሰውን በራሱ ሃሳብ እንዲፈራና እንዲሸማቀቅ የሚያደርግ እርኩስ ነገር ስለሆነ እንጸየፈዋለን፡፡

አሁንም ደግመን ደጋግመን ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የእኛ ሳይሆን የናንተ መሆኑንን እንገልጻለን። ፍትህን ሊያመጣ የሚችል እርቅ አሁንም በመርህ ደረጃ የምንደገፈው፣ ማንም የማይሸልመን፣ ማንም የማይወሰድብን ፈርጥ ሃሳባችን መሆኑንን አበክረን እናስታውቃለን። ማንም በ“እኛ አልደገፍነውም” የማግለያ ማስፈራሪያ ሊነጥቀን የማይችል ዕንቋችን ነው፡፡ ሃሳብን በሃሳብ የመጣላትና የመማማር ልምድ እንዲመጣ እንመኛለን። በሃሳብ መከራከር ጠላትነት እንዳልሆነ ከሚያምኑ ጋር በህብረት እንሰራለን። በሃሳብ ተለያይቶ በመከባበር አብሮ መስራት የሚችል ትውልድ እንዲነሳ የበኩላችንን እናበረክታለን። ከጎናችን ሁኑ። ጻፉ፣ ተናገሩ፣ አስተያየት ስጡ፣ “እኛ” ግን አትበሉ። እኛ ለመሆን ተደራጁና በድርጅት ስም ተንፍሱ!! አለበለዚያ “እናንተ እነማን ናችሁ” ይመጣልና!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ®” አቋም ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. አንተነህ ጌትነት says

    November 11, 2014 07:04 am at 7:04 am

    እነሱ ማን ሆኑና ነው ሌላውን ወያኔ የሚሉ? እርቅ አህዛቡ ወያኔ አይቀበለውም እንጂ ወየው በሆነ!!! የማይቀበለው ኢትዮጵያዊ ይኖራል ብየ አልገምትም ስለዚህ ይቅር መባባል ባህላችን ስለሆን እግዚአብሔር ያድርገው።
    ከሆነ ጎልጉሎች እርቁን መስበካችሁን አታቁሙ።
    አንተነህ ከባድ ሀገር አውስትራሊያ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule