• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ማነው ተጠያቂው?

December 4, 2012 06:54 pm by Editor Leave a Comment

ማነው ተጠያቂው?

ለኅሊናችን፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

ጥቂቶች በቡድን፣ ብዙሀኑን ገፍተው

የሰውን ስብዕና፣ ማንነቱን ገፈው፤

በጥይትም ይሁን፣ በታንክ ደፍጥጠው

እነሱ እንዲገዙ … ማነው የፈቀደው?

ሰለኅሊናችን፣ ስለ እውነት በሀቅ

ሰው – ለራሱ ብሎ፣ ‘ራሱን ይጠይቅ።

ብዙ በልተው – ብዙ ‘ለማበት’

ብዙ ተግተው – ብዙ ለመሽናት፤

…ለጮማ – ቅርናታቸው…

…ለውስኪ – ቅርሻታቸው…

…ለእኩይ – ምግባራቸው፤…

እንደ አንድ ሰው ሆነው፣ሲቆሙ በአንድነት

ለክቡር አላማ፣ ሌላው ሲሆን “ኩበት’’፤

እነሱ ምን ያ’ርጉት?… ምንስ ያቅርቡለት…?

ሰው ነኝ የሚል ዜጋ፣ ከተነዳ እንደ ከብት።

ሀገርን አፍርሰው፣ ትውልደን አጥፈተው

እንድ ቅርጫ ስጋ፣ ህዝብንም ከፋፍለው

እጃቸውን በደም፣ በህዝብ አምባ ታጥበው፤

“ታላቁ ፍጡር፣ የዘመኑ ጀግና፣ ክቡር …” ከተባሉ

ገዥዎች ምን ያርጉ…?፣ ለምን አይፏልሉ…?

“ለምን እድሜ በቃህ’’ እንገዛለን አይሉ…?

ሰለ እውነት –  በእውነት ፣ ስለ እውነት በሀቅ

ሰው ለራሱ ብሎ፣ ‘ራሱን ይጠይቅ።

የኪነ – ጥበብ ሰው፣ ‘ልሂቅ’ የተባለ

ማንነቱን ከዶ፣ ሞያውን አርክሶ፣ በከርሱ እየማለ፤

“…ሳይጠሩት – አቤት…!’’

“…ሳይልኩት – ወዴት…!’’

ጭራውን ከቆላ፣ “ውሾ!” እየተባለ

ከግራቸው ስር ልሁን፣ ልነጠፍ እያለ

ለገዠዎች እድሜ፣ ሱባኤ ካደረ፣ ሰበካ ከዋለ፤

ማነው ተጠታቄው? … በማን ላይ ይፈረድ?

“ከሀዲን’’ አንግሶ፣ ፍትህ አይወለድ፡፡

ለኅሊናችን ፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

እየተራብ – እያጠገባቸው

እየታረዘ – እያስጌጣቸው፤

እየደህየ – እያከበራቸው

እያዋረዱት – እየተዋረደላቸው፤

እየዘረፉት – እያሞካሻቸው

እየገደሉት – እያኖራቸው፤

በስሙ – በሀብቱ፣ ሲደለልበት

እንደ እቃ ሲቆጠር፣ ሲነገድበት፤

“ዜጋ’’ ነኝ ሲላቸው፣ እየሳቁበት

የ’ኔ እሚለው ሀገር – ቤቱን  ሲያሳጡት፤

“እኔ ምን ቸገረኝ፣ አለልኝ ‘ስደት”

ህሊና ተርቦ፣ ‘ከርስ’ እሚሞላበት

“አደናቅፎኝ ነው፣ የእናቴ መቀነት”

“ሆድ ይፍጀው’’ እያለ፣ ከጠበቀ ምፅ’ት፤

ገዥዎች ምን ያርጉ?…. ምን ይፈይዱለት?

ለመምራት አይደለም፣ ወይም ለመመራት

ለመግዛት እኮ ነው፣  “ገዳይ” ነን ያሉት።

ለኅሊናችን ፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

ፊልጶስ ፊልጶስ
philiposmw@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule