• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሠራተኛውን ማን አቃጠለው?

October 14, 2015 07:29 pm by Editor 2 Comments

የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) ከጥቂት ቀናት በፊት በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ ኤሊ ውሃ ከተማ ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም ስለተፈጸመው ግድያ መረጃ ልከውልናል፡፡

ከመረጃ አቀባያችን ጋር በተደጋጋሚ በተላላክነውና ባቀረብነው በርካታ ጥያቄዎች መሠረት ያገኘነው መረጃ ይህንን ይመስላል፡-

እጅግ ዘግናኝ የሚባለው ግድያ የተፈጸመው ከላይ በተጠቀሰው ሥፍራ በሚገኘው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት እየተባለ በሚጠራው ግቢ ውስጥ ነው፡፡ የእማኝ ዘጋቢው በራሳቸው አገላለጽ እንዲህ ዘግበውታል፡- (የላኩልን የእንግሊዝኛ ፊደላትን በመጠቀም ሲሆን ወዳማርኛው እንዲህ መልሰነዋል)

“ወንጀሉ የተፈጸመው ቅዳሜ መስከረም 22፤2008 ዓም በአፋር ክልል ሃዳር ወረዳ በኤሊውሃ ከተማ ግቢ ተብሎ በሚጠራው የቻይና መንገድ ሥራ ፕሮጀክት ውስጥ ነው፡፡ የተቃጠለው ልጅ ወልዱ ይባላል፡፡ በ(ፕሮጀክቱ) የላቦራቶሪ ሠራተኛ ነበር፡፡ ሟች ወጣት ወልዱ በላቦራቶሪ ክላስ ውስጥ ቤንዚን እየቀዳ ነበር፡፡ ብዛት ያላቸው የቤንዚን ጄሪካኖች ነበሩ፤ አለቃው ቻይናዊ ይመጣና ሲጋራ ወደ ቤንዚኑ ይወረውራል፤ ከዚያ በኋላ ምን እንደተከሰተ ግልጽ ነው፤ ሙሉ ቤቱ ነደደ፡፡ ቻይናዊው እየሮጠ ወጥቶ ቤቱን አውጭ ዘጋው፤ በቃ ወጣት ወልዱ አይሞቱ ሞት ሞተ፤ እርር፣ ክስል ብሎ በቁሙ ዓይኑ እያየ አንዳች እርዳታ ሳያገኝ ተቃጥሎ ሞተ፡፡ ከዚህ በኋላ ሬሳውን ይዘው ምርመራ ቤተሰብ ፍለጋ እያሉ ለ4 ቀን ካንከራተቱት በኋላ መልሰው እዚያው ኤሊ ውሃ ከተማ ቤተሰቦች በሌሉበት ተቀበረ፤ ወንጀሉን የፈጸመው ቻይናዊ ግን እስካሁን ለፍርድ አልቀረበም፡፡ ምክንያቱም የወረዳው መንግሥት ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡”

ይህ ከደረሰን በኋላ የእማኝ ዘጋቢውን ተጨማሪ ዝርዝር ለማግኘት ጥያቄዎችን አንስተን ነበር፡፡ በጥያቄያችን መሠረትም የሟችን የተቃጠለ ምስልና ከመሞቱ በፊት ያለውን ምስሉን የሚያሳይ ሁለት ፎቶዎች ልከውልናል፡፡ የተቃጠለው ሬሣ እጅግ ዘግናኝ ከመሆኑ ባሻገር ማንነቱ ጠፍቶ ለመለየት በሚያስቸግርበት ሁኔታ ከሌላ ወገን ማረጋገጥ የሚቻል ባለመሆኑ ከሁሉ በላይ ግን መሞቱ በቤተሰቡ ዘንድ የታወቀ ባለመሆኑ ይፋ ከማድረግ ተቆጥበናል፡፡ ሆኖም አሁንም ይህ መረጃ አቀባዩ በራሳቸው አነሳሽነት የላኩት የእማኝ ዘገባ በመሆኑ ላቀረብናቸው ተጨማሪ ጥያቄዎች የላኩት ምላሽ በአጭሩ ይህንን ይመስላል፡-

“ወጣት ወልዱ የተባለው ሟች የአፋር አፈር (soil) ላቦራቶሪ ሠራተኛ ነው፡፡ ለላቦራቶሪ ሥራ የሚጠቀምበትን ማሽን የሚያንቀሳቅስው ቤንዚን በመጠቀም ነው፤ እሱን በዚህ ሥራ የተሰማሩ ባለሙያዎች የበለጠ ማብራሪያ መጠየቅ ይቻላል፤ እናም ለዚህ ሥራ የሚጠቀምበት የሚበቃውን ያህል ለመቅዳት በቤንዚን ክፍል ውስጥ እያለ ነው ይህ አረመኔ ቻይናዊ ወደሱ መጥቶ ወደ ውስጥ በመግባት ሲያጨስ የነበረውን ሲጋራ በመወርወር አደጋው የተፈጠረው፡፡ የቤተሰቡን ጉዳይ እስካሁን ለማወቅ አልተቻለም፤ የትግራይ ክልል ተወላጅ እንደሆነ ብቻ ነው የሚታወቀው፡፡ እናም ሬሣውን እስከ መቀሌ ከተማ ድረስ ወስደው ለማጣራት ሙከራ አድርገናል ነው የሚሉት ግቢው ውስጥ የሚገኙ የፌዴራል ፖሊሶች፡፡ ግን መሞቱን ለማሳወቅ ያደረጉት እንቅስቃሴ በጣም አነስተኛ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ከቻይናዎች አንድ ኤሌክትሮኒክስ ዕቃ ሲጠፋቸው (ፖሊሶቹ) አሳድደው አዲስ አበባ ውስጥ ሊያዝ ችሏል፤ እና ይህንንም ጉዳይ ቢያስቡበት ቤተሰቦቹ ማግኘት ይችላሉ ብዬ እገምታለሁ፡፡”

ወንጀሉን የፈጸመው አለቃው ስም ማን እንደሆነ የእማኝ ዘጋቢው ሲናገሩ በራሳቸው አገላለጽ “wenjelun yefetsemew aleqaw yehoneaw Mr Waan yetebale chinawi neaw” (“ወንጀሉን የፈጸመው አለቃው ሆነው ሚስተር ዋን የተባለ ቻይናዊ ነው፡፡”) በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ይህ የእማኝ ዘጋቢው መረጃ ሲሆን ጎልጉል በሥፍራው ዘጋቢ ስለሌለው በቦታው የሚገኙትን ባለሥልጣናት በግምባር ለማነጋገር አልቻለም፡፡ ሆኖም ግን ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተውን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ምላሽ እንዲሰጥ ሞክረን ስልኩ ሳይነሳ በመቅረቱ መረጃ ለማግኘት አልተቻለም።

ሞተ የተባለውን ወጣት የሚያውቁ ቤተሰቦችም ሆኑ የቅርብ ወዳጆች በዚህ ጉዳይ ላይ ምላሽ እንዲሰጡ እንጠይቃለን፡፡ እንደሚዲያ እኛ ከእማኝ ዘጋቢ ያገኘነውን አቅርበናል፤ ዜናው የመረጃ አቀባዩ ነው፤ ሆኖም ግን በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሠሩ ድርጅቶች እና የሕዝብ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሁኔታውን ማጣራትና ዳር ማድረስ ይጠበቅባቸዋል፡፡ አሠሪ የተባለው መሥሪያቤትም ይህንን የመመርመርና የተባለው ቻይናዊ ወንጀለኛ ከሆነ ለፍርድ የማቅረብ ከፍተኛ ኃላፊነት አለበት፡፡ “ዕድገት እና ትራንስፎርሜሽን” የዜጎችንም ህይወት የሚመለከት ይመስለናል፡፡

ጎልጉል የእማኝ ሪፖርተሮች ያሉት ሲሆን በነዚሁ ምንጮቹ አማካይነት መረጃ ለህዝብ ሲያቀርብ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ለዚህም ነው “ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ ነው” የምንለው፡፡ ይህ ዜና ክዘግናኝነቱ ባሻገር ከጀርባው ልዩ ሚስጥር እንደሚኖረው ስለሚታመን ዜናው የሚመለከታችሁ ወገኖች ምላሽም ይሁን ማስተባበያ እንዲሰጡ እንማጸናለን።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Opinions, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Abe says

    October 18, 2015 06:31 pm at 6:31 pm

    This is so shocking and terrifying news beyond one’s human absorb and imagination to live with. Never such type of crime committed in Ethiopia before except by the then Fascist Italy during its Colonial Invasion Attempt in 1935-1940. Are the Chinese our modern day colonizers and have the right to decide on our living and life beyond their economic involvement? Its great shame to our country, people, and above all, to our “Government”. How can a bilateral relationship with China continues while this type of atrocity is going on our citizens? What is the value of so called “Development” while you are exposing your people to such horrendous acts and dreadful situations.
    After all, the Chinese are not investing nor providing relief or development aid to Ethiopia. They are simply loaners of their surplus with steep interest rate and labour contract (hiring their citizens) attached to it.
    We have to rise, stand up , fight and speak louder for our rights (at least for our natural rights). We need to make and force our leaders to be accountable and responsible. Otherwise, we keep on living in such abominable situation and lead undignified life and death. We also lose our country slowly to “Chinese Imperialism”to use the words of Alberto Acosta, former Ecuador Energy Minister.

    Reply
  2. Belhu says

    November 29, 2015 07:39 pm at 7:39 pm

    በቤንሻንጉል ክልል በሐሰት የትምሕርት ማስረጃ በመያዝ (በተለየ ከሰሜን ኢትዮጲያ የመጡ) URRAP በሚባል የገጠር መንገድ ስራ ፕሮጀክቶች በመደራጀት ኢንጅነር በመባል ሚሊዮኖችን እየዘረፉ ይገኛሉ:: መረጃውን ለሚመለከተው አድርሱልን::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule